Netsanet: እነ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ በሀሰት እየተመሰከረባቸው እንደሆነ ገለፁ • (በጌታቸው ሺፈራው)

Mittwoch, 9. August 2017

እነ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ በሀሰት እየተመሰከረባቸው እንደሆነ ገለፁ • (በጌታቸው ሺፈራው)

እነ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ በሀሰት እየተመሰከረባቸው እንደሆነ ገለፁ • ‹‹ህዝብ እውነታውን እንዲረዳልን እንፈልጋለን›› መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ (በጌታቸው ሺፈራው) ቂሊንጦ እስር ቤትን አቃጥላችኋል፣ ንብረት አውድማችኋል እንዲሁም የሰው ህይወት አጥፍታችኋል በሚል የሽብር ክስ የተመሰረተባቸው እነ ማስረሻ ሰጤ ነሃሴ 2/2009 ዓ.ም ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት በሀሰት እየተመሰከረባቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በትናንትናው ዕለት ሁለት ምስክሮች የቀረቡ ሲሆን አንደኛው ምስክር በ13 ተከሳሾች ላይ ምስክርነት ሰጥቷል፡፡ ምስክሩ እነ ማስረሻ ሰጤ፣ ሰይፈ ግርማ እና ፍቅረማርያም አስማማው የአማራ ብሄር ተወላጆችን እየሰበሰቡ ለግንቦት ሰባት በአባልነት ይመለምሉ እንደነበር ሲገልፅ፣ ወልዴ ሞቱማ፣ አበበ ኡርጌሳና ሌሎች ተከሳሾች የኦሮሞ ብሄር ተወላጆችን በመሰብሰብ ለኦነግ ይመለምሉ ነበር ብሎ መስክሯል፡፡ ሆኖም ምስክሮቹ የአማራና የኦሮሞ ብሄር ተወላጆችን ለግንቦት ሰባትና ኦነግ ይመለምሉ ነበር የተባሉት ተከሳሾች ከየትኛው ብሄር እንደሆኑ ሲጠየቁ አናውቅም ብለዋል፡፡ ምስክሮቹ የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በቃጠሎው ወቅት የሞቱትን እስረኞች ፎቶ ቀድሞ በማሳየት ለምስክርነት ያዘጋጃቸው መሆኑን ለችሎቱ የገለፁ ሲሆን ተከሳሾቹም በሀሰት እየተመሰከረባቸው እንደሆነ ለፍርድ ቤቱ አስታውቀዋል፡፡ 1ኛ ተከሳሽ ማስረሻ ሰጤ በበኩሉ በሀሰት እየተመሰከረባቸው መሆኑን በመግለፅ ‹‹በተቋም ደረጃ የሀሰት ምስክርነት እየተሰጠ ነው፡፡ ህዝብ እውነታውን እንዲረዳልን እንፈልጋለን›› ብሏል፡፡ ሌሎች ተከሳሾችም በሀሰት እየተመሰከረባቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ዛሬ ነሃሴ 3/2009 ዓ.ም ሁለት ተጨማሪ የአቃቤ ህግ ምስክሮች የተሰሙ ሲሆን የምስክር መስማት ሂደቱ እስከ ነሃሴ 12/2009 ዓ.ም ይቀጥላል ተብሏል፡፡ ምስክሮቹ ነሃሴ 28/ 2008 ዓ.ም ተኩስ እንደነበር፣ በጥይት የተገደሉና የቆሰሉ እስረኞች እንዳዩ እንዲሁም ወደ እስረኛው የጭስ ቦንብ እንደተወረወረ ገልፀዋል፡፡ ለቃጠሎው መንስኤ የአስተዳደር ችግር፣ ምግብ መከልከሉና በመታሰር የተፈጠረ ብሶትም እንዳለበትም ተገልጾአል፡፡ ቶፊቅ ሽኩር፣ ሸቡዲን ነስረዲን፣ ኡመር ሁሴን፣ ሸምሱ ሰይድ፣ ከድር ታደለ፣ ተመስገን ማርቆስ፣ አሸናፊ መለስ፣ ሚስባህ ከድር፣ አግባው ሰጠኝ፣ ምትኩ ደበላ፣ ካሳ መሃመድ፣ ከበደ ጨመዳ፣ ጌታቸር እሸቴና ፍጹም ጌታቸው በሁለቱ ቀን የፍርድ ቤት ውሎ ምስክር ተሰምቶባቸዋል፡፡

https://netsanetlegna.wordpress.com/2017/08/09/%e1%8a%a5%e1%8a%90-%e1%88%98%e1%89%b6-%e1%8a%a0%e1%88%88%e1%89%83-%e1%88%9b%e1%88%b5%e1%88%a8%e1%88%bb-%e1%88%b0%e1%8c%a4-%e1%89%a0%e1%88%80%e1%88%b0%e1%89%b5-%e1%8a%a5%e1%8b%a8%e1%89%b0%e1%88%98/

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen