Netsanet

Mittwoch, 15. November 2017

የብሄራዊ ደህንነት ዕቅድ ወይስ የህወሀት የስንብት ደብዳቤ? ( ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን)

የብሄራዊ ደህንነት ዕቅድ ወይስ የህወሀት የስንብት ደብዳቤ?
መቀሌ
ይህን ጽሁፍ በማዘጋጅበት ሰዓት መቀሌና ሀራሬ ሁነኛ የፖለቲካ ክስተት ተፈጥሯል። የመቀሌው ይፋ የወጣ አይደለም። በህወሀት አፍቃሪያን ድረገጾች የተተነፈሰ ወሬ ነው። ወ/ሮ አዜብ መስፍን የመቀሌውን ህንፍሽፍሽ ረግጠው ወጡ የሚለው ከውስጥ አዋቂ ያፈተለከው ዜና በቀላሉ የሚታይ አይደለም። በትክክል ከሆነ የሀራሬው ዓይነት መፈንቅለ መንግስት ልናይ የምንችልበት እድል ሰፊ ነው። የጄነራል/ፕሮፌሰር ሳሞራ የኑስ ቡድን በመቀሌው ስብሰባ ከተሸነፈ እጁን አጣጥፎ የሚቀመጥ አይሆንም። በአቶ ስብሃት ነጋ የሚመራው የአዲስ አበባው ህወሀት በአንዳች ተአምር መከላከያውን ከሳሞራ የኑስ እጅ ፈልቅቆ ካልወሰደ በቀር የወ/ሮ አዜብ መስፍን ኩርፊያና ረግጦ መውጣት የሚያስከትለው መዘዝ ለህወሀት ፍጻሜው ሊሆን ይችላል።
ትያትሩን አድፍጦ መከታተሉ ጥሩ ነው። ያም መጣ፡ ይሄም ሄደ ልዩነት የለውም። ለኢትዮጵያ ህዝብ የትኛውም የህወሀት አንጃ አይበጀውም። ህወህት ቢከፈልም፡ ቢሰነጣጠቅም ያው ህወሀት ነው። ከነስሩ ተመንግሎ፡ ተጠራርጎ መወገድ ያለበት እንጂ ክፋዩ፡ ስንጣቂው ቢተርፍና በስልጣን ላይ ቢቆይ ለኢትዮጵያና ህዝቧ ተውሳክ፡ ነቀርሳ መሆኑ የማይቀር ነው።

ሀራሬ
የዙምቧቡዌ ሰማይ ያልተለመደ አየር ነፍሶበታል። የ40 ዓመቱ የሙጋቤ ስዩመ እግዚያብሄር አገዛዝ ፍጻሜውን አግኝቷል። በስልጣን ላይ በመቆየት የዓለምን ክብረወሰን የጨበጡት ሽማግሌው ሙጋቤ ከነሚስታቸው በወታደሩ ክፍል ለጊዜው በማቆያ ይገኛሉ። ብሄራዊው ቴሌቪዥን ላይ የዚምቧቡዌ ጦር መሪዎች መግለጫ እየሰጡ ነው። በአጭሩ መፈንቅለ መንግስት ተካሂዷል። ለዚምቧቡዌ አዲስ ታሪክ ተመዝግቧል። ሰውዬው በአጥንታቸው ሳይቀር ጨምድደው እየገዟት ያለችው ሀገር በአዲስ የታሪክ ምዕራፍ ላይ ወጥታለች። ሁኔታዎች በፍጥነት በሚለዋወጡባት ዚምቧቡዌ የሚሆነው ነገር አይታወቅም። ታሪክ ግን ተቀይሯል።
ዚምቧቡዌ በአንድ ስልጣኑን እስከመቃብሩ ድረስ ላለመልቀቅ በወሰነ ሽማግሌ የስንግ ተይዛ ለ40 ዓመታት ቆይታለች። ኢትዮጵያ በዘርና ጎሳ በተቧደኑ፡ በዘረፋና ሌብነት ሀገሪቱን ለመጋጥ በተሰለፉ የአንድ መንደር ልጆች ከሩብ ክፍለዘመን በላይ ደሟ እየተመጠጠ ያለች ሀገር ናት። የዚምቧቡዌ ጦር የዚምቧቡዌ ነው። የኢትዮጵያ ጦር የኢትዮጵያ አይደለም። በዚምቧቡዌ መፈንቅለ መንግስት ቢካሄድ አዲስ ስርዓት በተስፋ ይጠበቃል። በኢትዮጵያ ግን መፈንቅለ መንግስት የህወሀትን አገዛዝ በመሳሪያ ሃይል የሚያስጠብቅ ሌላ የጨለማ ዘመን የሚያመጣ እንጂ ለውጥ አይኖረውም።
ዕቅድ ወይስ ስንብት?
ለአዲስ ስታንዳርድ በቅድሚያ ምስጋና ይገባዋል። ይህ ሰነድ ወይም ዕቅድ ወይም ኑዛዜ ወይም የስንብት ደብዳቤ ይደርሰን ዘንድ የአዲስ ስታንዳርድ ውለታው ላቅ ያለ ነው። ሰነዱ በጣም ጠቃሚ ነው። በጣምም ወሳኝ ነው። ለነጻነትና ዲሞክራሲያዊ ስርዓት መምጣት ለሚዋደቁ ሃይሎች በተለይም በለውጥ ምጥ ላይ ላለው የኢትዮጵያ ህዝብ ይህ ዕቅድ ተስፋን የሚያለመልም ነው። በእስከአሁኑ በዚህ ደረጃ የህወሀት መንግስት ውድቀቱን ያመነበት ሰነድ አላየሁም። የጠቃሚነቱን፡ የወሳኝነቱን ያህል ግን ትኩረት አልተሰጠውም። ኢትዮጵያ እንደዚምቧቡዌ ያረጀውንና፡ የጃጀውን ስርዓት ልትገላገለው በዋዜማው ላይ መሆኗን የሚያበስር ዕቅድ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።
ዝርዝር ዕቅዱ የህወሀትን የወቅቱን ቁመና የሚያሳይ ነው። ውስጣዊ ሁኔታዎች በሚል በ10 ነጥቦች የተዘረዘሩትን ከወሰድን ከአንድ ድምዳሜ ላይ እንደርሳለን። የህወሀት መንግስት በእርግጥም አብቅቶለታል። በተቃራኒው ያለው የለውጥ ሃይል ጠንካራ ባለመሆኑ፡ ወይም፡ በአንድነት ባለመሰለፉ ወይም በሁለቱም ምክንያቶች የተነሳ እየፈራረሰ ያለውን የህወሀት ስርዓት ወደመቃብሩ መውሰድ ባለመቻሉ ህወሀት ለጥቂት ጊዜያትም ቢሆን እድሜው እንዲቀጥል እየሆነ ነው። የህወሀትን ኑዛዜ ዋና ዋና ክፍሎችን እንመልከተው።
ህዝብ ተስፋ ቆርጦብኛል
ህውሀት አልደበቀም። እንደሁልጊዜውም የህዝብ ተስፋ ነኝ የሚል ባዶ ኩሸት መደለቅ አልፈለገም። በዕቅዱ ላይ እንደተናዘዘው ህዝቡ ተስፋ ቆርጦበታል። ህዝብ በህይወት የመኖር ተስፋው እየቀነሰ፡ እየጨለመ መምጣቱን፡ በስርዓቱ ላይ ተስፋ የመቁረጥና ይህ ስርዓት ይቀጥል ይሆን የሚል ብዥታ ውስጥ መግባቱን ይገልጻል። ህዝቡ የሰላም ዋስትና ማጣቱንም ህወሀት አምኗል። ስጋት ውስጥ የተዘፈቀ፡ በስልጣን ላይ ባለው ስርዓት ላይ እምነት አጥቶ ውዥንብር ውስጥ የገባ ህዝብ ሲልም ያስቀምጣል። ህዝቡ ብቻ ሳይሆን ሰራዊቱም ተስፋ እንደቆረጠበት ተናዟል። ለህወሀት ትልቁ አደጋ ይሄ ነው። የጸጥታ ሃይሉ ሰላም የማስከበር አቅሙ መጎዳቱን፡ በመንግስት መቆየት ላይ ጥርጣሬ ውስጥ መግባቱን፡ በአጠቃላይ መሰላቸትና ተስፋ መቁረጥ በሰራዊቱ ውስጥ መከሰቱን አትቷል።
ጸረ-ሰላም ሃይሎች(የለውጥ ሃይሎች)
ይህን ዕቅድ ላነበበ አንድ ነገር ግልጽ ይሆንለታል። በኢትዮጵያ ውስጥ የህወሀትን ስርዓት ገንድሶ ለመጣል የተስለፉ ሃይሎች እግር አውጥተው ረጅም ርቀት እየተጓዙ ለመሆናቸው ትልቅ ማስረጃ የሚሆን ሰነድ ነው። ተቃዋሚዎች የታላችሁ? መሳሪያ የታጠቀ ቡድን ኢትዮጵያ ውስጥ አለ ወይ? ለሚሉ ሰዎች የህወሀት ዕቅድ አጥጋቢ መልስ ይሰጣል። በዕቅዱ ላይ እንደተገለጸው አርበኞች ግንቦት ሰባትና የኦሮሞ ነጻነት ግንባር በሀገሪቱ እንደፈለጉ በመፈንጨት ላይ ናቸው። እነዚህ ሃይሎች በፕሮፖጋንዳው ጭምር እንደበለጡትም አምኗል። ሃይላቸው ተጠናክሯል። ህዝብን ከጎናቸው እያሰለፉ ነው። ለጦርነት የሚሆን ከፍተኛ ገንዘብ እየሰበሰቡ ነው። መሳሪያ ግዢው ተጧጡፏል። እነዚህ ሃይሎች መንግስት ተዳክሟል፡ ሀገር ለመምራት አይችልም ከሚል ድምዳሜ ደርሰው ስርዓቱን ሊያፈራርሱ እየተረባረቡ ነው ሲል ህወሀት የመጣበትን አደጋ በግልጽ አስቀምጧል።
ጸረ ሰላም(የለውጥ) ሃይሎች ውስጡን እንደቦረቦሩት ህወሀት በገደምዳሜም ቢሆን ገልጿል። አመራሩ በተለይም መካከለኛውና የታችኛው አመራር በእነዚህ ሃይሎች ፕሮፖጋንዳ ታጥቦ ተወስዷል የሚለው ህወሀት በሀገሪቱ ለተከሰተው አጠቃላይ ቀውስም የራሱ መዋቅር ላይ ጣቱን ቀስሯል። አርበኞች ግንቦት ሰባትና ኦነግ የብአዴን፡ ኦህዴድንና ደኢህዴንን መዋቅር ሰብረው መግባታቸውን በመግለጽ በተለያዩ ጊዜያት ለሚወጡ ጥሬ መረጃዎች ማረጋገጫ የሚሰጥ ኑዛዜ ነው። ህወሀት በዚህ ዕቅዱ የተቃዋሚዎች(የጸረ ሰላም ሃይሎች) መጠናከርን የህዝብ ስጋት የፈጠረ ሲል ይገልጸዋል። በእርግጥ ተቃዋሚዎች በዚህ ደረጃ ማንሰራራትና መጠናከር መቻላቸው ለህዝብ ስጋት አይሆንም። መርዶም አይደለም። ተስፋ እንጂ። ተቃዋሚዎችን ፍለጋ በየሰፈርና መንደሩ የሚሰማውን የኢትዮጵያ ህዝብ ጥያቄ የሚመልስ የወቅቱ ታላቅ የምስራች እንጂ።
ኢኮኖሚው አደጋ ላይ ነው
የህወሀት ኑዛዜ በኢኮኖሚው ላይ ያስቀመጣቸው እውነቶች በተለያዩ የነጻነትና የዲሞክራሲ ደጋፊ ሚዲያዎች ሲባል የነበረውን የሚያረጋግጥ ነው። ህወሀት ግብር መሰብሰብ እንዳልቻለ ገልጿል። መንግስት የለም፡ ግብር አትክፈሉ የሚል ቅስቀሳ እየተካሄደ ነው ብሏል። በኢኮኖሚው ላይ ከፍተኛ ሳቦታጅ( ዶ/ር ታደሰ ብሩ አሻጥር ይለዋል) እየተፈጸመ መሆኑን አትቷል። ህዝቡን ለልማት ከማሰማራት ይልቅ የጦርነት ነጋሪት እየተጎሰመ ለግጭትና ለሰላም መደፍረስ ሚና እንዲጫወት እየተደረገ ነው ያለው ህወሀት በዚህም ምክንያት ኢኮኖሚው ክፉኛ መጎዳቱን አስታውቋል። የውጭ ኢንቨስትመንት ተዳክሟል። የቱሪስት ፍሰት ቀንሷል። የውጭ እርዳታ በከፍተኛ መጠን ወርዷል።
የህወሀት ዕቅድ ላይ እንደተገለጸው ባለሀብቶችና ኢንቨስተሮች ሀብትና ገንዘብ በከፍተኛ ደረጃ ከሀገር እያሸሹ ናቸው። እነማን እንደሆኑ በእርግጥ አልተገለጸም። መረጃዎች የሚያመለክቱት የህወሀት ባለስልጣናትና በዘር መስመር ሀብት ያፈሩ የትግራይ ተወላጆች በዋናነት ሀብት እያሸሹ መሆናቸውን ነው። በነገራችን ላይ ማክሰኞ አንድ ሪፖርት ወጥቷል። የአውሮፓ ህብረት ኢትዮጵያን ከ10ሩ ገንዘብና ሀብት ከሚሸሽባቸው የዓለም ሀገራት ውስጥ አስገብቷታል። በዚህም ምክንያት ከኢትዮጵያ በሚሸሸው ሀብትና ገንዘብ ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ሊያደርግ ነው። ለ28ቱ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ሰርኩላር ተበትኗል። የህወሀት ባለስልጣናት አንዱ የሀብት ማሸሺያ መስመር አሁን ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ ታስሯል። የሼህ አላሙዲን መታሰር በህወሀት መንደር ሽብር የፈጠረው ያለምክንያት አይደለም። እናም ህወሀቶች ለጡረታቸው ያሸሹት ሀብትና ገንዘብ ወጥመድ ውስጥ ገብቷል።
ጄኖሳይድ
የዚህ ዕቅድ አስደንጋጩ ክፍል ይሄው ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የጅምላ ግድያ መፈጸሙን ህወሀት ገልጿል። በሶማሌና በኦሮሚያ ክልሎች መሃል በተፈጠረው ግጭት ጄኖሳይድ ተፈጽሟል ያለው የህወሀት የደህንነት ዕቅድ እነማን እንደፈጸሙ፡ ምን ያህል ሰዎ እንዳለቀ በዝርዝር አያስቀምጥም። የፖለቲካ ተንታኞች ህወሀት ሌሎችን ለማጥመድ የስነቀራት ምክንያት ልትሆን ትችላለች የሚል ሀሳብ ያቀርባሉ። በተለይም የሁለቱን ክልሎች በዋናነትም የኦሮሚያ ክልል መሪዎችን ለማስበርገግ ሊሆን እንደሚችልም ይገልጻሉ። ሆኖም ህወሀት ሳያስበው ራሱ ላይ ጥይቱን አቀባብሏል የሚሉ ወገኖችም አሉ። ህወሀት በሚቆጣጠራት ሀገር ጄኖሳይድ ተፈጽሞ ከሆነ ይህን የምድረግ አቅም ያለው የህወሀት ጦር በመሆኑ በቀጥታ ተጠያቂ የሚሆነው የህወሀት መንግስት ነው። ለዓለም ዓቀፍ ተቋማትና ለመንግስታቱ ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጥሩ ዱላ ነው። ሌሎች በኢትዮጵያ የተፈጸሙና የተደበቁ የጅምላ ግድያዎች የሚነሱበትና ተጠያቂዎች ለፍርድ የሚቀርቡበትን ሁኔታ የሚቀሰቅስ ሊሆን ይገባዋል። በኦጋዴናን በአኝዋክ ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጽሙትን ጄኖሳይዶች ማን ይረሳቸዋል?
የጦስ ዶሮ
ህወሀት በኢትዮጵያ ውስጥ ለተፈጠሩ ቀውሶች ራሱን ተጠያቂ ከማድረግ ተቆጥቧል። ሶስት አካላት ላይ ጣቱተቀስሯል። ግብጽና ኤርትራ በረጅም እጃቸው ኢትዮጵያን እየበጠበጡ ነው የሚል ክስ በህወሀት ቀርቧል። አርበኞች ግንቦት ሰባትና ኦነግ ሀገሪቱን በማመስ ተወንጅለዋል። የስርዓቱ አመራሮች ለቀውስ የተመቸ ሜዳ በመፍጠር ጥርስ ተነክሶባቸዋል። በዕቅዱ ላይ አንድም ቦታ ህወሀት ሃላፊነት አልወሰደም። አሁንም ለኢትዮጵያ ህዝብ መላዕክ መሆኑን ይገልጻል። የጦስ ዶሮዎች እየተፈለጉ ነው። በተለይ በስርዓቱ ውስጥ ያኮረፉት ላይ እርምጃ ሊወሰድ ይችላል። መጠነ ሰፊ እስሮች ከፊት እንደሚኖሩ ይጠበቃል። የዕቅዱ አንድም ግብ እነዚህን አመራሮች ልክ ማስገባት ነው።
የዕቅዱ ግብ ሌሎች ተግባራትንም ያከናውናል። ሰልፎች ታግደዋል። በአስቸኳይ አዋጁ ገደብ የተጣለባቸው መብቶች በተዘዋዋሪ በዚህኛው ዕቅድም ተግባራዊ ይሆናሉ። ዕቅዱ በስም እንጂ በይዘት ከአስቸኳይ አዋጁ ጋር አንድ ነው። የዕቅዱ ሌሎች ግቦች ከፉከራ ያለፉ አይደሉም። መሳሪያ መንጠቅ፡ ጸረ ሰላም ሃይሎችን መደምሰስ እና የመሳሰሉት ግቦች አሁን ህወሀት ካለበት ቁመና አንጻር የሚሳኩ አይመስሉም።
ማጠቃለያ
የመቀሌው ስብሰባ አልተጠናቀቀም። ህወሀት ሪፎርም ማድረጉንና ከስልጣን የሚያሰናብታቸው አመራሮች እንደሚኖሩ እየተነገረ ነው። It is too late. ምን ዓይነት ሪፎርም? ህወሀት አፈጣጠሩ ለዚህ የሚፈቅድለት አይደለም። ያረጠ ድርጅት ነው። ከተቸነከረበት የስታሊን መስመር ዝንፍ ካለ መጥፊያው ነው። ደግሞም 11ኛው ሰዓት ላይ ሪፎርም አያድነውም። የኢትዮጵያ ህዝብ ህወሀትን ሊሰናበት ተዘጋጅቷል። ይህ ዕቅድም የስንብት እንጂ የሪፎርም አይደለም። ከመቀሌ የሚጠበቅ ለውጥ አይኖርም። ህወሀት በዕቅዱ እንዳስቀመጠው ህዝቡ መንግስት ይቀጥላል ብሎ አያምንም። ተስፋ ቆርጧል። ስለዚህ ዕቅዱን የስንብት ደብዳቤ ነው ቢባል ያስኬዳል። ኑዛዜም ነው። ይህን ተቀብሎ የማሰናበትና ህወሀትን ከነጥቁር ገጽታው

Freitag, 1. September 2017

ጊዜው "የእምቢ አልገዛም! " "የእምቢ አልከፍልም! " ነው። (በ ዶ/ር ታደሰ ብሩ)

ህወሓት፣ በቀን ገቢ ግምት ግብር ከፋዮች ላይ  ያሰበው መጠነ ሰፊ ዘረፋ ላይ በደረሰበት ሰፊ ተቃውሞ ሳቢያ ቀላል የማይባል ኪሳራ ደርሶበታል። በዚህም ምክንያት የማፈግፈግ ምልክቶችን አሳይቷል። ማፈግፈግ የሥርዓቱ ጊዜዓዊ ማምለጫ ነው፤ ሁኔታዎች ሲረጋጉ ተመልሶ መምጣቱ አይቀርም። እንዲያውም ሌሎች ተጨማሪ የዝርፊያ መስሮችን መክፈቱን የማይቀር ነው። 

አሁን ተግባራዊ መሆን የጀመረ ድሆችን ይበልጥ የማደህያ አንድ መጠነ ሰፊ ፕሮጀክት እነሆ። በወሊሶ ከተማ የቀበሌ ቤቶች ኪራይ በአንድ ጊዜ ከ 40  - 50 ጊዜ እጥፍ መጨመሩ ኢሳት ገልፆ ነበር።

እንዲህ ዓይቱ ጭማሪ በወሊሶ ብቻ ሳይሆን በሁሉም የኦሮሚያ ከተሞች ወስጥ ተግባራዊ እንዲደረግ ተወስኗል።. ለምሳል፣ በወር 10 ብር ይከፈልበት የነበረ ዛኒጋባ ብር 500 እንዲከፈልበት፤ መክፈል  የማይችሉ ቤቶቹን እንዲለቁ እንዲደረግ ተወስኗል።

ይህ ውሳኔ በኦሮሚያ ላይ ተወስኖ የሚቀር አይደለም፤ የኦሮሚያው አፈፃፀም ታይቶ ወደሌሎች ክልሎችም መዛመቱ የማይቀር ነው። ስለሆነም ካሁኑ ተቃውሞዓችን አገራዊ መሆን ይኖርበታል።

መጪው 2010 "ለማይወክለን አገዛዝ ግብር ብቻ ሳይሆን ማናቸውንም ክፍያ አንፈፅምም" የሚባልበት ዓመት መሆን ይኖርበታል።

መምህራን፣ ተማሪዎች፣ የመንግሥት ሠራተኞች፣ ወታደሮችና ፓሊሶች "አንገዛም፣ አንታዘዝም፣ አንከፍልም፣ አንሠራም……" ለማለት ይዘጋጁ።

ጊዜው "የእምቢ አልገዛም! " "የእምቢ አልከፍልም! " ነው።

Freitag, 18. August 2017

የእነ አቶ በቀለ ገርባ መከላከያ የመስማት ሂደት አቃቤ ህጉ እርቦኛል በማለቱ ምክንያት ተቋርጧል። በ ( ጌታቸው ሽፈራው)

የእነ አቶ በቀለ ገርባ መከላከያ የመስማት ሂደት አቃቤ ህጉ እርቦኛል በማለቱ ምክንያት ተቋርጧል።

አቃቤ ህግ ለሚያቀርበው ጥያቄ ተደጋጋሚ መቃወሚያ የቀረበበት ሲሆን መሃል ላይ "አርብ እንደመሆኑ እኛ ለምሳ  መውጣት ያለብን 5:30 ላይ ነው። የምሳ ሰዓታችን ይከበር" ብሎ ባቀረበው ጥያቄ  መሰረት መጠነኛ ክርክር ተደርጓል። ሌላ አቃቤ ህግ ስለነበር ፍርድ ቤቱ ሌላኛው አቃቤ ህግ ራበኝ ያለውን ተክቶ የሚሰራበት አጋጣሚ ስለመኖሩ ቢጠይቅም ራበኝ ያለው አቶ  አንተነህ  የተሰየመው እሱ ብቻ መሆኑን ገልፆአል።

 " እኔም ከጤናዬ አንፃር ሊታሰብልኝ ይገባል።ጨጓራ አለብኝ። መብላት አለብኝ" ብሏል አቶ አንተነህ።

የቀኝ ዳኛው አቃቤ ህጉ ያነሱት ጥያቄ መስቀለኛ ጥያቄ ሳይጀመር ቢሆን ኖሮ ተገቢ ይሆን እንደነበር  ገልፀው መታገስ እንደሚገባ በመጠቆማቸው  አቃቤ ህጉ " ትክክል ነው። ታግሼ መስራት እንዳለብኝ አውቃለሁ። እዚህ ቦታ ላይ ቆሜ የምሰራው ጤና ሲኖረኝ ነው። ህመሜን እያዳመጥኩ ልጠይቅ አልችልም።" ብሎ የምሳ ሰዓቴ ይከበር የሚለውን ጥያቄ ገፍቶበታል።

አቶ በቀለ ገርባ በበኩሉ "  ይህ ከዚህ ትልቅ  ተቋም የሚጠበቅ አይደለም።  እኛ እየተራብን፣ ብዙ መከራ እያየን ነው ያለነው። ህዝቡም የፍትህ ሂደቱን እንዲያይ ነው። አቃቤ ህግ ከተለየ አካል ትዕዛዝ ሊቀበል ካልሆነ በስተቀር ይህ በምክንያትነት ሊቀርብ አይገባም" ብሏል።

 መሃል ዳኛው" ከዚህ ወንበር ተቀምጠን ትዕዛዝ መስጠት አለብን። ሁለት አቃቤ ህጎች ስላሉ አንዱ ተክቶ ሊሰራ እንደሚችል እንረዳለን። ይህ የትዕዛዝ ጉዳይ አይደለም።" ቢልም ሂደቱ ተቋርጦ ለምሳ ተወጥቷል።
 ይህ የምሳ ሰዓት ይከበር ጥያቄና ክርክር በታዳሚውና ተከሳሾች  ሳቅ የታጀበ ነበር።

Mittwoch, 9. August 2017

እነ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ በሀሰት እየተመሰከረባቸው እንደሆነ ገለፁ • (በጌታቸው ሺፈራው)

እነ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ በሀሰት እየተመሰከረባቸው እንደሆነ ገለፁ • ‹‹ህዝብ እውነታውን እንዲረዳልን እንፈልጋለን›› መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ (በጌታቸው ሺፈራው) ቂሊንጦ እስር ቤትን አቃጥላችኋል፣ ንብረት አውድማችኋል እንዲሁም የሰው ህይወት አጥፍታችኋል በሚል የሽብር ክስ የተመሰረተባቸው እነ ማስረሻ ሰጤ ነሃሴ 2/2009 ዓ.ም ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት በሀሰት እየተመሰከረባቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በትናንትናው ዕለት ሁለት ምስክሮች የቀረቡ ሲሆን አንደኛው ምስክር በ13 ተከሳሾች ላይ ምስክርነት ሰጥቷል፡፡ ምስክሩ እነ ማስረሻ ሰጤ፣ ሰይፈ ግርማ እና ፍቅረማርያም አስማማው የአማራ ብሄር ተወላጆችን እየሰበሰቡ ለግንቦት ሰባት በአባልነት ይመለምሉ እንደነበር ሲገልፅ፣ ወልዴ ሞቱማ፣ አበበ ኡርጌሳና ሌሎች ተከሳሾች የኦሮሞ ብሄር ተወላጆችን በመሰብሰብ ለኦነግ ይመለምሉ ነበር ብሎ መስክሯል፡፡ ሆኖም ምስክሮቹ የአማራና የኦሮሞ ብሄር ተወላጆችን ለግንቦት ሰባትና ኦነግ ይመለምሉ ነበር የተባሉት ተከሳሾች ከየትኛው ብሄር እንደሆኑ ሲጠየቁ አናውቅም ብለዋል፡፡ ምስክሮቹ የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በቃጠሎው ወቅት የሞቱትን እስረኞች ፎቶ ቀድሞ በማሳየት ለምስክርነት ያዘጋጃቸው መሆኑን ለችሎቱ የገለፁ ሲሆን ተከሳሾቹም በሀሰት እየተመሰከረባቸው እንደሆነ ለፍርድ ቤቱ አስታውቀዋል፡፡ 1ኛ ተከሳሽ ማስረሻ ሰጤ በበኩሉ በሀሰት እየተመሰከረባቸው መሆኑን በመግለፅ ‹‹በተቋም ደረጃ የሀሰት ምስክርነት እየተሰጠ ነው፡፡ ህዝብ እውነታውን እንዲረዳልን እንፈልጋለን›› ብሏል፡፡ ሌሎች ተከሳሾችም በሀሰት እየተመሰከረባቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ዛሬ ነሃሴ 3/2009 ዓ.ም ሁለት ተጨማሪ የአቃቤ ህግ ምስክሮች የተሰሙ ሲሆን የምስክር መስማት ሂደቱ እስከ ነሃሴ 12/2009 ዓ.ም ይቀጥላል ተብሏል፡፡ ምስክሮቹ ነሃሴ 28/ 2008 ዓ.ም ተኩስ እንደነበር፣ በጥይት የተገደሉና የቆሰሉ እስረኞች እንዳዩ እንዲሁም ወደ እስረኛው የጭስ ቦንብ እንደተወረወረ ገልፀዋል፡፡ ለቃጠሎው መንስኤ የአስተዳደር ችግር፣ ምግብ መከልከሉና በመታሰር የተፈጠረ ብሶትም እንዳለበትም ተገልጾአል፡፡ ቶፊቅ ሽኩር፣ ሸቡዲን ነስረዲን፣ ኡመር ሁሴን፣ ሸምሱ ሰይድ፣ ከድር ታደለ፣ ተመስገን ማርቆስ፣ አሸናፊ መለስ፣ ሚስባህ ከድር፣ አግባው ሰጠኝ፣ ምትኩ ደበላ፣ ካሳ መሃመድ፣ ከበደ ጨመዳ፣ ጌታቸር እሸቴና ፍጹም ጌታቸው በሁለቱ ቀን የፍርድ ቤት ውሎ ምስክር ተሰምቶባቸዋል፡፡

https://netsanetlegna.wordpress.com/2017/08/09/%e1%8a%a5%e1%8a%90-%e1%88%98%e1%89%b6-%e1%8a%a0%e1%88%88%e1%89%83-%e1%88%9b%e1%88%b5%e1%88%a8%e1%88%bb-%e1%88%b0%e1%8c%a4-%e1%89%a0%e1%88%80%e1%88%b0%e1%89%b5-%e1%8a%a5%e1%8b%a8%e1%89%b0%e1%88%98/

Dienstag, 1. August 2017

ግብር በአምባገነን አገዛዝ (በዶ/ር ታደሰ ብሩ ኬርሰሞ)

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ)
*******************************
ግብር በአምባገነን አገዛዝ
-------------------------
በዶ/ር ታደሰ ብሩ ኬርሰሞ
 ስለ አምባገነን አገዛዝና ግብር ሲነሳ መጥቀስ የምወደው የእውቁ ኢኮኖክስ ማንኩር ኦልሰን  Dictatorship, Democracy, and Development ነው።  ከዚህ ጽሁፍ በዛ አድርጌ ልጥቀስ።
===
ዘላን ወንበዴዎች /roving bandits/ ነጥቀው ይሮጣሉ፤ መቼ እንደሚመለሱ አይታወቅም። እነዚህ ወንበዴዎች ነጥቀው በሮጡ ቁጥር የማኅበረሰቡ ሀብት የማፍራት ፍላጎት ስለሚዳከም በሚቀጥለው ዙር የሚዘርፉት ነገር እያነሰባቸው ይመጣል። ቀን ባለፈ መጠን ነጥቆ መሮጥ ራሳቸውን እንደሚጎዳቸው ይገነዘቡና ከተዘዋዋሪ ወንበዴነት ወደ ቋሚ ወንበዴነት /stationary bandit/  ይቀየራሉ። ለንጥቂያቸውም ሥርዓትና ልክ ያበጁለታል፤ ስሙን “ግብር” ይሉታል። ማኅበረሰቡንም፣ ራሳቸውንም ከሌሎች ተዘዋዋሪ ወንበዴዎች ይከላከላሉ። ይህ ሥርዓት ከሥርዓተ አልበኝነት የተሻለ፣ የቅሚያውም መጠንም አስቀድሞ የሚታወቅ ከመሆኑ ጋር ማኅበረሰቡ ለሚከፍለው ተመጣጣኝ ባይሆንም የሚያገኘው ጥቅም (ሰላምና ሌሎችም ማኅበራዊ ምርቶች) ስላሉ ምርት ይጨምራል፣  ዕድገትም ይኖራል።
 ይሁን እንጂ አምባገነን ሰፋሪዎች በተደላደሉ መጠን ፍጆታቸው እየናረ መሄዱ ፈጽሞ የማይቀር ነው። ለጦር ሠራዊቱ፣ ለቤተመንግሥቱ፣ ለማሰልጠኛው፣ ለመታሰቢያ ሀውልቶች ግንባታ፣ ለአዳራሾች ግንባታ፣ ለአምባገነኖች፣ ለተከታዮቻቸውና ቤተሰቦቻቸው የክብር ልብሶችና ጌጣጌጦች፣ “ለመጠባበቂያ“፣ .....  የሚያስፈልገው ወጪ በጨመረ ቁጥር ሕዝቡ በግብር አሊያም በሌላ መንገድ እንዲከፍል ስለሚገደድ ሥርዓት በመስፈኑ ምክንያት አንሰራርቶ የነበረው የሥራ ፍላጎት እንደገና ያሽቆለቁላል። የሰፋሪ ወንበዴዎችን የሀብት ማጋበስ፣ ምቾትና እዩልኝ ፍላጎቶችን ማርካት አይቻልም።
==
 በማንኩር ኦልሰን ላይ የምጨምረው የለኝም፤ ሁሉንም ብሎታል።
 ወንበዴዎች ሕዝብን ለማስገበር ሁለት ነገሮች ያስፈልጓቸዋል።  አንዱ ጉልበት ነው። ሞኝ ሽፍታ ዘርፎ ይሮጣል፤ ብልጣብልጥ ሽፍታ ደግሞ ቁጭ ብሎ መዝረፍ ያምረዋል።  ብልጣ ብልጥ ሽፍታ ራሱን በመንግሥትነት ሰይሞ ለዘረፋው “የመንግሥት ግብር “ የሚል ስያሜ ሰጥቶ ተዘራፊን አሰልፎ ደረሰኝ እየሰጠ ይዘርፋል።
 ቁጭ ብሎ ደረሰኝ እየሰጡ ለመዝረፍ ግን ከጉልበት በተጨማሪ ለዘረፋ ሰበብ የሚሆኑ ማኅበራዊ ምርቶች (public goods) ማምረት ያስፈልጋል። ካድሬዎች ሕዝቡን “ግብር የምትከፍለው ለመንገድ፣ ለጤና  አገልግሎት፣ ለትምህርት  ...” ብለው መቀስቀስ አለባቸው። ግብር ግዴታ መሆኑ ቢታወቅም ምክንያታዊ እንደሆነ ማብራራት መቻል አለባቸው። በአምባገነን ሥርዓት ውስጥ ከተሰበሰበው ግብር ምን ያህሉ ወደ ማኅበራዊ ምርት፤ ምን ያህሉ ደግሞ ወደ ባለሥልጣናቱ ኪስ እንደሄደ የሚጠይቅ የለም።  መንገዱም ሆነ ሕንፃው ቢሰራ ለማን፣ ለምን ብሎ የሚሞግት የለም። ሕዝቡ አምፆ እስካላስቀረው ድረስ ደረሰኝ እየተቀበለ ይዘረፋል።
 በህወሓት/ኢሕአዴግ አገዛዝ አገራችን የምትገኝበት ሁኔታ ይህ ነው። የህወሓት ሠፋሪ ወንበዴዎች በግብር ስም እያስራቆቱን ነው። ህወሓት የዘረጋው የግብር ሥርዓት ወንበዴው ቁጭ ብሎ ለፍቶ አዳሪውን የሚመጥበት፤ ድሀው ሀብታሙን የሚደጉምበት ነው። እንዲህ እንዳሁኑ አንዳንዴ የሙስና ዜና  ሲኖር ነው በግብር የተሰበሰበው ገንዘብ የት እንደተከማቸ በወሬ ወሬ የምንሰማው።
 ሌላም ላነሳው የምሻ ጉዳይ አለ:  “ግንዛቤ ማስጨበጥ” የሚሉት።
 አገራችን ውስጥ የወር ደመወዝ ተከፋይ ምንም ከግብር ማምለጫ ቀዳዳ የሌለው በመሆኑ ከሁሉ በላይ ተበዳይ እንደሆነ ስለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ መጠነኛ እውቀት ያለው ሁሉ የሚያውቀው ሀቅ ነው። የግብር ዕዳን ለማስተካከል ሲባል “ነጋዴ ላይ ግብር መጫን የወር ደመወዝተኛው ኑሮ ያሻሽላል” የሚል “ግንዛቤ ማስጨበጥ”  “እኔ ብጎዳም ያንተ ከኔ ይበልጥ መሰቃየት ያስደስተኛል” ዓይነት ሰይጣናዊ አመክኖ ነው። በነጋዴ ላይ የሚጫን ግብር ውሎ አድሮ በሙሉ ወይም በከፊል ወደ ሸቀጦች ዋጋ መተላለፉ አይቀርም።  ይህንን ሽግግር የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅም አያስቀረውም። እናም የወር ደመወዝ ተከፋዩ  የሚጠቀመው በለፍቶ አዳሪው ላይ የግብር ዕዳ በመጫኑ አይደለም። የወር ደመወዝተኛው የሚጠቀመው በለፍቶ አዳሪው ብቻ ሳይሆን በሱም ላይ የተጫነው የግብር ዕዳ  ሲቀንስ ነው።
 ላጠቃለው።
ወገኞቼ፤ ለህወሓት/ኢሕአዴግ አገዛዝ ግብር አልከፍልም ማለት ተገቢ ነው። ለአንባገነን ሥርዓት አልገብርም ማለት ከሥነ ምግባር አንፃር ተቀባይነት ያለው የጽድቅ ሥራ ነው። ለህወሓት አንገብርም ማለት የሚኖርባቸው ነጋዴዎች ብቻ ሳይሆኑ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው።

Montag, 10. Juli 2017

አርበኝነት

አርበኝነት

አርበኝነት ማለት ለወገኑ የተሻለ ህይወትና ጊዜዉን ጉልበቱን እዉቀቱን ገንዘቡን  ንብረቱንና ክቡር ህይወቱን መስዋትነት ለመክፈል የተዘጋጀ ሰዉ ወይም የህብረተስብ ክፍል ማለት ነዉ።

ከዚህም በመነሳት ዛሬ ላይ እየተካሄደ ባለዉ የአርበኝነት ትግል አላማችን እንዲሳካ እራአያችን እንድያብብ የምንሻ ሁሉ የግድ ያለዉን ነባራዊ ሁኔታ ማጤንና መገንዘብ ያስፈልጋል።  የአርበኝነት አላማ ደግሞ ዉጤታማ የሚሆነዉ በእቅድ የሚመራ በተግባር የሚታይና በድርጊት የሚገለጽ  የጥርት ዉጤት ሲሆን ነዉ።
በመሆኑም ድሮ አርበኛ አባቶቻችን በአዋጅ ተሰባስበዉ በራሶችና በደጃዝማቾች የጦር አጋፋሬዎች እየተመሩ ለሃገራቸዉ በነበራችዉ ጥልቅ የሃገራዊ የፍቅር ስሜት አርበኝነትን ተላብስዉ በባዶ እግራቸዉ ወንዝና ሽነተረሩን አቋርጠዉ ዳገት ቁልቁልቱን ወጥተዉ ወርደዉ ከጦርነቱ አዉድማ ሲደርሱ ነጋሪት እየተጎሰመ እንቢልታዉ እየተንፋ ንጉስ ከፈረስ ሳይወርዱ በጦርነተ መሃል ዉስጥ ሆነዉ አዋጅ እያስነገሩ የፊዉታራሬ ጦር ግባ ተብለሃል፥ የቀኝ አዝማች ጦር ግባ ተብለሃል፥የግራዝማች ጦር ግባ ተብለሃል በሚል የአዉደ ዉጊያ የእዝ ሰንሰለት ጊዜዉ በፈቀደዉ የጦርነት ስልት ነበር  በጦር በጎራዴ ተዋግተዉ ደማቸዉን አፍሰዉ ሃገራችን ኢትዮጵያን ከወራሪ  ቅኝ ገዥዎች ያዳኗት።
ዛሬ ላይ ደግሞ ሃገር በቀል ወራሬ የወያኔን ቡድን ለማስወገድ የአርበኞች ግንቦት 7 አርበኛ ታጋዮች በሁለገብ የትግል ስልት ከገጠር እስከ ከተማ ሁሉንም የሃገራችነን ክፍል ባከለለ የህዝባዊ እንቢተኝነትና የህዝባዊ አመጽ እንዲጎለብት በማድረግ በቁርጠኝነት በምታገል ላይ ናቸዉ።
እንድሁም አርበኛ ታጋዮቻችን ከነጻነት ሃይሎችና ከህዝቡ ጋር በመሆን የሽምቅ ዉጊያ በማካሄድ ትግሉ ወደ ላቀ ደረጃ እንድሸጋገር ከፍተኛ ተጋድሎ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።
ስለሆነም የአርበኞች ግንቦት 7 አርበኛ ታጋዮች እንዳ አባቶቻችን የአርበኝነትን  መንፈስ ተላብሰዉ መስዋእትነት በመክፈል ደማችዉን አፍሰዋል።
በአሁኑ ስአትም ደም ገብረዉ ሃገራችንን ከጥፋት ለመታደግ የቆረጡ የህዝብ ልጆች ከአገዛዙ ታጣቂ ሃይሎች ጋር እየተፋለሙ ናቸዉ።
በሌላ በኩል ግን ወያኔን ለማስወገድ ራሱ ወያኔ በመጣበት የትግል ስልት እና ኢህአፓና ኢድዩ የትጓዙበትን የትግል መንገድ የተከተለ አይደለም ምክኔያቱም ዘመኑ ያለፈበት የትግል መንገድ በመሆኑ።
ወይም እንዳባቶቻችን የደጃዝማች ጦር በቀኝ በኩል ግባ ተብለሃል የፊዉታራሪ ጦር በግራ በኩል ግባ ተብለሃል በሚል በአዋጅ የሚደረግ ጦርነት አይደለም ዘመኑ የቴክኖሎጅ ዘመን ነዉ።ስለዚህ አሁን ያለዉ የአርበኝነት ትግል የወቅቱን ነባራዊ ሁኔታን ባገገናዘበ በስልትና ሚስጥር በመጠበቅ የሚደረግ የአርበኝነት ትግል ነዉ ።
ይህን ተከትሎ በትጨባጭ የአርበኞች ግንቦት 7 አርበኛ ታጋዮች በመፈቃቀድ ላይ የተመሰረተ አንድነትን ለማምጣትና ዴሞክራሲን ለማስፈን ለሃገራችን ኢትዮጽያ በጎ ራእይን በመሰነቅ  የወያኔን አገዛዝ ለማስወገድ በሁሉም መስክ ትግሉን እያቀጣጠሉ ይገኛሉ።
 ነገር ግን አንዳድ ወገኖች ከራሳቸዉ የግል ጥቅም በመነሳት እና አሁን ያለዉን ነባራዊ ሁኔታ በጥልቀት ባለመረዳት እንድሁም በግንዛቤ እጥረት አራንባና ቆቦ በሆነ አስተሳሰብበ በአዉሮፓና  በአሜሪካ  ካለ የፕረስ ነጻነት ጋር በማመሳሰል እቅዳችን ይሕ ነዉ፥አሁን እንደዚህ እየሰራን ነዉ ፥ወደፊት እንደዚያ ልናደርግ ነዉ የሚል ሪፖርት ወይም ጋዜጣዊ መግለጫ እንድሰጥ የሚፈልጉ የመኖራቸዉን ያክል፥ በሌላ በኩል ደግሞ የሽምቅ ዉጊያ ሚስጥራዊነቱ ተጠብቆ የሚከናወን በመሆኑ አንዳድ ብሄር ተኮር ፖለቲከኞች ለራሳቸዉ የፖለቲካ ስካራ ለግባትነት ለመጠቀም በማሰብ ሆን ብለዉ በተግባር እየተከናወነ ያለዉን ስራ ትቢያ እያለበሱ  ምንም ስራ እንዳልተሰራ በደካማ ጎን በመፈረጅ የወሬ ቋታቸዉን ሲያራግቡ ይስተዋላሉ።
 በጥቅሉ  እነዚህ ግለሰቦች አብሮ ከመታገልና የስናፍጭ ቅንጣት ታክል ለትግሉ አስተዋጽኦ ከማድረግ ይልቅ ችግሮችን እየፈለጉ በስራ ላይ የሚከሰቱትን ጥቃቅን ስህተቶችን ነቅሶ በማወጣት የሚያናፍሱት ወሪ የአርበኝነት ትግሉን ወደኋላ   የሚጎትት እና የወያኔን የአገዛዝ እድሜ ሊያራዝም በሚያስችል በተሳሳተ መንገድ እየተጓዙ መሆናቸዉ ግልጽ ሆኖ እየታየ ነዉ።
ሃግርን ለምዳን በሚደረገዉ የሞት ሽረት ትግል ዉስጥ ሚና በሌለዉ ለግል ጥቅም አንጋጦ በወሬ ብቻ እራስን ከፍ አድርጎ እንደ ታጋይ በመቁጠር የሚመጣ ለዉጥ የለም ከገደል ማሚቶነት ማስተጋባት የዘለለ ሊሆን የሚችል አይደለም ።
በአንጻሩ ግን ለፖለቲካ ግባትነት ያገለግላል ከሚል መነሻነት አማራ ኦሮሞ በማለት ልዩነትን በማስፋት ትርፍን አስቦ የግል ፍላጎትን ለማሟላት የሚደርግ ሩጫ የወያኔን እድሜ ከማራዘሙም በላይ በህብረተሰቡ መካከል ቅራኒን አስፍቶ ዘመን የማይሽረዉን ጠባሳ ይተክላል ።ስለሆነም በህዝብ ደም ለመነገድ ማሰቡ ሊቆም ይገባዋል። 
የዚህ አይነት አመለካከት ያላቸዉ ግለሰቦች ሊያዉቁት የሚገባዉ መሬት ላይ ያለዉ እዉነታ በርበኞች ግንቦት7 ድርጅት ጥላ ስር የትሰባሰቡ በሃገር ዉስጥም በዉጭም ያሉ አርበኛ ታጋዮች በእንቅስቃሴአቸዉ በተግባር እያከናወኑት ያለዉ የአርበኝነት ትግል አንዱን አገዛዝ አስወግዶ ሌላዉን አገዛዝ ለመተካት አይደለም  ምክኒያቱም በትግሉ ሂደት ዉስጥ ሁሉንም እይነት ፈተና በመቀበልና መስዋእትነት እየተከፈለ ያለዉ ሃግራችን ኢትዮጽያ ከገባችበት የአሮንቃ ማጥ ዉስጥ ለማዉጣት ሲባል ብቻና ብቻ ነዉ።
ስለሆነም ክቡር ህይወትን ከመገበር በላይ ሌላ ምስክርነት የሚስፈልገዉ አይደለም ።
ይልቁንም እንደኔ እምነት የሚሻለዉ መንገድ ሁላችንም ግለሰባዊ ጥቅምን ወደ ጎን በመተዉ እንደ ሃገር በጅምላ የደረሰብንን መከራና ስቃይ ዋየታና እሮሮ ለማስቆም በአንድነት ላይ ቁመን በጋራ ተባብረን በአርበኝነት በመታገል ወራሪ የህዉሃትን ቡድን ለማስወገድ ቅድሚያ ልንሰጠዉ የሚገባ ተግባር ሊሆን ይገባዋል።

ባንዳነት ጌጥ የሆነላቸው (መስቀሉ አየለ)

ባንዳነት ጌጥ የሆነላቸው (መስቀሉ አየለ)
መስቀሉ አየለ
ቡልጋሪያ የምትባል የምስራቅ አውሮፓ ክፍል አለች። ለአራት መቶ አመት ያህል በቱርክ የእሳት ሰንሰለት ተጠፍንጋ የኖረች አገር ናት። የኦቶማን ቱርክን ጦር ቀጥቅጦ ወደ መቃብር የገፋላት የሩሲያ ጦር ነበር። ቡልጋዎች ይህን የነጻነት ቀን በያመቱ ሲያከብሩ የክብር እንግዳው የሚመጣው ከሩሲያ ነበር። ባለፈው አመት ግን ይኽ አልሆነም። በሶፊያ፣ ቡልጋሪያ የሚገኘው የ አሜሪካን አምባሳደር ተቆጣ አሉ፤ ተቆጥቶም አልቀረም ይልቁንም የክብር እንግዳው ከቱርክ መሆን አለበት ብሎ ቀጭን ትእዛዛ ያስተላለፈው ለአገሪቱ ፕሬዝዳንት ነበር።በጌታና የሎሌ ግንኙነት ወቅት ፕሮቶኮል ትርጉም የለውም።Unpatriotic act
የናዚ ጀርመን ጦር አውሮፓን እንዳይወር በወቅቱ የነበሩት መራሄ መንግስትታ ለሂትለር እጅ መንሻ የመስዋእት ጠቦት አድርገው የሰጡት ፖላንድን ነበር። ክፋቱ ሂትለር እርሷን በልቶ አለማቆሙ ነው እንጂ። ፖላንድን ከናዚ ጦር ነጻ ለማውጣት ስድስት መቶ አምሳ ሺህ የሩሲያ ጦር ነበር ያለቀው። በታሪኩ አሰቃቂ በተባለለት አስቸጋሪ የበረዶ ላይ ከበባ ዋጋ ለከፈሉትና ድፍን አውሮፓን ከናዚዝምና ከፋሽዝም ለታደጉት የሩሲያ ወታደሮች መታሰቢያ በፖላንድ ዋርሳው የቆሙትን ሃውልቶች ዛሬ ከአሜሪካ በላይ አሜሪካዊነት በሚሰማቸው የፖላንድ መሪዎች መፈራረስ በመጀመራቸው የሩሲያ መንግስት የወታደሮቹን አጽም በክብር ወደ አገሩ መልሶ ለማሳረፍ ቃል ገብቷል።ዛሬ ፖላንድ ማለት በምስራቅ አውሮፓ ውስጥ ያለች አንዱዋ የአሜሪካን ላፕዶግ መሆኗን በብዙ አጋጣሚ እያስመሰከረች ያለችበት ሁኔታ ነው ያለው።

በኛም አገር ለአገራቸው በጎ የዋሉ፤ ለማንነታቸው ዋጋ የሰጡና እራሳቸውን የተቀደሰ መስዋእት አድርገው ህዝባቸውን የታደጉ አባቶቻችን አጽመ እርስታቸው የሚያርፈው አዲስ አበባ በሚገኘው ዮሴፍ ቤተክርስቲያን እንደነበረ ይታወቃል። አርከበ እቁባይ የተባለ የባንዳ ልጅ የመናገሻውን ቢሮ በያዘ ሰሞን “የኒህን የነፍጠኞች ምናምንቴ አውጥተኽ ጣልልኝ!” ብሎ ባዘዘው መሰረት የዚያ ሁሉ የአርበኛ አጽም ነበር ድፍን አዲሳቤ በኣይኑ ብረት ቆሞ እያየ በቡልዶዘር ተጠራርጎ የፈረሰው። ከላይ በሌሎች አገሮች ተሞክሮ እንዳየነው ባንዳ ሁሉ ስነ ባህሪያቸው አንድ ነው። ሰሞኑንም የፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ፣ መልአከ ብርሃናት አድማሱ ጀንበሬና ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤን አጽም አንሡ መባላችን ያው ከላይ በፖላንድ ካየነው እውነት ልዩነት የለውም። እንዲህ በማንነቱ የሚሸማቀቅ፣ የገዛ ታሪኩን የሚያዋርድና ገንዘብ ባየበት ሁሉ እንደ ሴተኛ አዳሪ የሚገለፍጥ የወያኔ አይነት ባህሪ ለምን የምእራባውያንን ልቦና እንደሚያማልል ግልጽ ነው። ዘመኑ የባንዳ ነው።