የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ቃሊቲ ጉምሩክ ጽሕፈት ቤት ከፍተኛ ኦፊሰር፣ አቶ ዘመን ይሰማው 40,000 ብር ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል በሚል ተጠርጥረው ክስ ተመሠረተባቸው፡፡
ግለሰቡም በተጠየቁት መሠረት ክፍያውን ይፈጽማሉ፡፡ ተጠርጣሪው ኦፊሰር ተጨማሪ 146,000 ብር መክፈል እንዳለባቸው ይገልጹላቸውና 60,000 ብር ከሰጧቸው ግን እሳቸው እንደሚጨርሱላቸው ሲገልጹላቸው፣ በሐሳቡ በመስማማት ቅድሚያ ክፍያ 40,000 ብር ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡ ክስ ለመስማት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሁለተኛ ወንጀል ችሎት ለታህሳስ 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ቀጠሮ ይዟል፡፡
Keine Kommentare:
Kommentar veröffentlichen