Netsanet: April 2015

Donnerstag, 30. April 2015

ኢትዮጵያ በታሠሩ ጋዜጠኞች ብዛት በአፍሪካ አንደኛ ነች!!!

Netsanet Yibeltal's photo.Netsanet Yibeltal's photo.
Netsanet Yibeltal's photo.Netsanet Yibeltal's photo.Netsanet Yibeltal's photo.
ኢትዮጵያ እሥር ላይ የምትገኘውን ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙን፤ ቪየትናም ደግሞ የኢንተርኔት ፀሐፊዋን ወይም ብሎገሯን ታ ፎንግ ታንን እንዲለቅቁ ዩናይትድ ስቴትስ ጠየቀች፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቃል አቀባይ ጄፍ ራትካ ናቸው ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ይህንን የመንግሥታቸውን ማሳሰቢያ ያስተላለፉት፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በዚህ ሣምንት እያወጣቸው ባሉ ተከታታይ የፕሬስ መግለጫዎች በዓለም ዙሪያ በየእሥር ቤቱ ያሉ ጋዜጠኞችን በየቀኑ እያነሣ ይገኛል፡፡
በዚህ “FREE THE PRESS” ወይም “ፕሬስን ነፃ አውጡ” በሚለው ዘመቻው የዛሬው የመሥሪያ ቤቱ መግለጫ ካተኮረባቸው ሁለት ጋዜጠኞች አንዷና ቀዳሚዋ የቀድሞ የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የእንግሊዝኛ መምህር ኢትዮጵያዊቱ ፍሪላንስ ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ነች፡፡
በፀረ-ሽብር ሕጉ መሠረት በተመሠረተባት ክሥ ጥር 10/2004 ዓ.ም ተፈርዶባት እስከዛሬ ወኅኒ ቤት እንደምትገኝ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ ጄፍ ራትካ ጠቁመዋል፡፡ “… ርዕዮት ኢትዮጵያ ውስጥ ከሥራቸው ጋር በተያያዘ በተመሠረቱባቸው ክሦች ምክንያት ከታሠሩ 18 ጋዜጠኞች አንዷ ስትሆን ይህ ሁኔታም ኢትዮጵያ በአህጉሩ ብዙ ጋዜጠኞችን በማሠር ቀዳሚዋ እንድትሆን አድርጓታል …” ብለዋል፡፡
ርዕዮት የመንግሥቱን ፖሊሲዎች የሚተቹ ፅሁፎችን በጋዜጣ በማውጣቷ ምክንያት በሰኔ 2003 ዓ.ም ተይዛ የሽብር ፈጠራ ክሥ ከተመሠረተባት በኋላ የ14 ዓመት እሥራት ተፈርዶባት እንደነበረ ያስታወሱት ራትካ የእሥራት ዘመኗ ወደ አምስት ዓመት ዝቅ እንዲል ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በነሐሴ 2004 ዓ.ም መወሰኑን ተናግረዋል፡፡
ይሁን እንጂ ክሡ ሙሉ በሙሉ እንዲሠረዝላት በተከታታይ ያቀረበቻቸው የይግባኝ አቤቱታዎች ውድቅ መደረጋቸውንም ራትኮ አመልክተዋል፡፡
“… ሃሣብን የመግለፅ ነፃነት መብቷን ተግባራዊ በማድረጓ ብቻ ታሥራ የምትገኘውን ርዕዮትን እንዲፈታ ለመንግሥቱ ጥሪያችንን እናቀርባለን – ያሉት ራትኮ – መንግሥቱ ፀረ-ሽብር አዋጁን ሃሣብን በነፃነት የመለዋወጥን ተግባር ለመጠምዘዝ ጉዳይ ከመጠቀም እንዲቆጠብም እናሳስባለን …” ብለዋል፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ቃል አቀባይ ጄፍ ራትኮ በመቀጠልም በአውሮፓ የዘመን አቆጣጠር የ2013 ዓ.ም ጀብዱ ፈፃሚ ሴቶች ዓለምአቀፍ ሽልማት ያሸነፈችውና የቪየትናምን መንግሥትና ኮምዩኒስት ፓርቲውን የሚተቹ ፅሁፎችን ኢንተርኔት ላይ በማውጣቷ የአሥር ዓመት እሥራት ተፈርዶባት ወኅኒ የምትገኘው ታ ፎንግ ታንን የቪየትናም መንግሥት በአፋጣኝ እንዲለቅቅ መንግሥታቸው እንደሚያሳስብ አስታውቀዋል፡፡
ምንጭ:- ቪኦኤ አምሀሪክ

Donnerstag, 23. April 2015

ኢትዮጵያኖቹ በ ISIS ሲገደሉ በግድ እንዲያይ የተደረገው ታዳጊ ህፃን


አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 15፣ 2007(ኤፍ.ቢ.ሲ) የ16 ዓመቱ ኤርትራዊ ስደተኛ ናኤል ጎይቶም የኤይ ኤስ ታጣቂዎች ኢትዮጵያውያኑን እና ኤርትራውያኑን በግፍ ሲቀሉ እና ሲረሸኑ እንዲመለከት መደረጉን ይናገራል።

ታዳጊው ኢንተርናሽናል ቢዝነስ ታይምስ ከተሰኘው ጋዜጣ ጋር ባደረገው ቃለምልልስ እንደተናገረው፥ ታጣቂው የአይ ኤስ ቡድን ይህን አሰቃቂ ድርጊት አስገድዶ እንዲመለከት አድርጎታል።

ይህ አሰቃቂ ድርጊት ከተከናወነ ከጥቂት ቀናት በኋላ ከሌሎች አራት ኤርትራውያን ጋር በሊቢያ ታስረውበት ከነበረው ካምፕ ማምለጣቸውንም ተናግሯል።

በእዚህ አረመኔ ቡድን ከመቀላት ለማመለጥ መሞከር አዋጭ መሆኑን የተናገረው ናኤል፥ ከቡድኑ ካምፕ ካመለጡ በኋላ እርዳታ የሚያገኙበት ስፍራ እስኪደርሱ ድረስ ለአራት ቀናት ያህል በሊቢያ በረሃ ውስጥ መጓዛቸውን ይተርካል።

ከአንድ ወር ለሚበልጥ ጊዜ በፅንፈኛው አይ ኤስ ቁጥጥር ስር በነበሩበት ወቅትም “ከመሞት እና እስልምናን ከመቀበል የቱን ትመርጣላችሁ”? የሚል ምርጫ እንደተቀመጠላቸው እና በወቅቱ ሙስሊም መሆንን እንደሚመርጡ እና እንዋጋላችኋለን ሲሉ መናገራቸውንም ያስታውሳል ታዳጊው።

ናኤል ኢትዮጵያውያኑ እና ኤርትራውያኑ በአይ ኤሴስ ከተያዙ በኋላ በአንድ ትልቅ ጉድጓድ መቀመጣቸውንም ተናግሯል ።

ከእለታት በአንዱ ቀንም 47 ያህል ኢትዮጵያውያንን እና ኤርትራውያንን ጥቋቁር እና ብርቱካናማ ልብሶችን አልብሰው ወደ ሜዲትራኒያን ባህር ዳርቻ እንዲሁም ሊቢያ በረሃ እንደወሰዷቸው እና እሱም ይህን ይመለከት ዘንድ አብሯቸው እንደወሰዱት ከዚያም ይህን ጭካኔ የተመላበት ድርጊት እንዲመለከት መደረጉንም ይናገራል።

ታዳጊው በአይ ኤስ እንዴት ተያዘ?

ናኤል እንዴት በፅንፈኛው የአይ ኤስ እጅ እንደተያዘም ያብራራ ሲሆን፥ 10 ኤርትራውያን ሴቶችን እና 8 ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ 61 ከሚሆኑ ስደተኞች ጋር ከአንድ ወር በፊት በሱዳን አድርግው ደቡብ ሊቢያን ሲያቋርጡ በአይ ኤስ ታጣቂዎች መያዛቸውን እና ሀይማኖት ነክ ጥያቄዎች መጠየቃቸውን ያስታውሳል።

ከመካከላችሁ ማን ነው ሙስሊም? ብለው እንደጠየቋቸው ነገር ግን ክርስቲያን የሆንነው መስቀል እና ክርስቲያን መሆናችንን የሚያሳዩ መንፈሳዊ ምስሎችን በመያዛችን በወቅቱ ማንነታቸንን መደበቅ አላስቻለንም ብሏል።

በአይ ኤስ ካምፕ ውስጥ ከ300 እስከ 400 የሚሆኑ የፅንፈኛው ቡድን አባላት የሚገኙ ሲሆን፥ ኢትዮጵያዊያን እና ኤርትራዊያን ተይዘው በካምፑ ውስጥ እንዲገቡ ሲደረግ፣ ሶማሊያውያን ግን መሄድ ወደፈለጉበት እንዲጓዙ ይፈቀድላቸው እንደነበር ይተርካል።

ናኤል ኤይ ኤስን አስቀድመው የተቀላቀሉ እና ለሽብር ቡድኑ የሚዋጉ ሶስት ኤርትራውያን የነበሩ ሲሆን፥ እነሱ ይረዱናል ብለን ስንጠብ ግን ስለኛ ምንም ስሜት አልተሰማቸውም ሲል ታሪኩን ያወጋል።

ናኤልን ጨምሮ ዮሃንስ መብራቱ፣ ቶማስ ገብረህይወት፣ አብርሃም ናይዝጊ፣ አማን ሺሻይ የተሰኙ ታዳጊ ኤርትራውያንም ከአይ ኤስ ካመለጡ እና ከአራት ቀናት አድካሚ የበረሃ ጉዞ በኋላ አንድ ሱዳናዊ አግኝቷቸው በሰሃራ በረሃ በርካታ ስደተኞች ወደሚገኙበት የስደተኞች መጠለያ እንዳደረሳቸው ገልጿል።

ታዳጊው ህይወቱን ማትረፍ ቢችልም ባየው እና በደረሰበት መከራ እና እንግልት ሳቢያ ውስጡ መጎዳቱን ነው የተናገረው።

አይ ኤስ ከ30 ደቂቃ በማያንስ የተንቀሳቃሽ ምስል (ቪዲዮ) በአለም ዙሪያ ባሰራጨው መልዕክቱ 30 ኢትዮጵያዊያን እና ኤርትራዊያን ንፁሃን ዜጎችን ገሚሱን በሜዲትራኒያን ባህር ዳርቻ ሲቀላ፥ ገሚሱን ደግሞ በሊቢያ በረሃ በጥይት በመተኮስ ሲገድል ማሳየቱ ይታወሳል።
ምንጭ፦ http://www.ibtimes.co.uk

የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትናዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያቀረቡት አስቸኳይ ጥሪ

የአርበኞችግንቦት 7: የአንድነትናዲሞክራሲንቅናቄሊቀመንበርለኢትዮጵያሕዝብያቀረቡትአስቸኳይጥሪ
የተከበራችሁ ወገኖቼ፤  ከሰላሳ በላይ የሆኑ ወገኖቻችንአይሲስ በተሰኘህሊናቢስ፣ፀረ-ሰውእናፀረ-ስልጣኔቡድንበሊቢያበአሰቃቂሁኔታየመገደላቸውመርዶከትናንት ወዲያ ሚያዝያ 11 ቀን 2007 ዓምደርሶን ኢትዮጵያዊያን በያለንበት በመሪር ሀዘን ውስጥ ነን። ዛሬ “እግዜር ያጥናህ” ወይም “እግዜር ያጥናሽ” የሚባል ሰው የለም። ሁላችንም ሀዘንተኞች ነን። ካጣናቸው ቁጥራቸው በብዙ እጥፍ የሚበልጥ ወገኖቻችን አሁንም በአራዶች መዳፍ ውስጥ መሆናቸው ሀዘናችን እጅግ የበረታ ያደረገዋል። ቁጥራቸው በትክክል የማይታወቅ ሆኖም በሺህ የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን ዛሬም ሊቢያ ውስጥ ናቸው። በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን አሁንም ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ናቸው።  ሌሎች በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ደግሞ በየመን ከሰማይም ከምድርም በቦንብና በጥይት እየተማገዱ ነው።
ለምንድነው ኢትዮጵያዊያን እንዲህ እሳት ውስጥ ለመማገድ የምንደፍረው? መልሱ ግልጽ ነው። አገር ውስጥ ተስፋ የለም፤ ወያኔዎች ተስፋችንን አጨለሙት። ከሳዉዲ በመከራ የተመለሱ ወንድሞቻችን ናቸው በሊቢያ በኩል ለመሰደድ ሲሞክሩ በአይ ሲስ ተይዘው የታረዱት። ወያኔዎች አገራችንና ክብራችን ዘረፉን። ወያኔዎች  ስብዕናችንን ገፈፉን።
የዘመኑ ጥቂት የህወሓት ቱጃሮች ፎቆችን እየገነቡ በነሱ መጥገብ እኛ እንድናገሳላቸው ይፈልጋሉ።  የኢትዮጵያ ሕዝብ መራቡ፣ መታረዙ፣ መደህየቱ እውነት ነው፤ ሆኖም ግን “ተራብኩ”፣ “ታረዝኩ”፣ “ደኸየሁ” ብሎ መናገር አይችልም። እውነት መናገር ያስቀጣል፣ ያስወነጅላል። በፍርደ ገምድል ችሎት እውነት መናገር “ሽብርተኛ” ያስብላል። እስር ቤቶችን የተሞሉት ለእውነት፣ ለፍትህ፣ ለነፃናትና ለእኩልነት በቆሙ ሰዎች አይደለምን?
በአይ ሲስ ያሳረደን ማነው? መልሱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ ነው። ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው።  እንደ አገርና እንደ ሕዝብ የደረሰብን ውርደት የትም ብንሄድ የምናመልጠው አልሆነም። በአገር ውስጥ የደረሰብንን ውርደት ለማምለጥ ስንሰደድ ውርደት ተከትሎን ይመጣል።
ወገኖቼ፤ ለኛ ለኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ የተሻለች አገር ሊኖረን አይችልም። ዛሬ የመሸሻ ጊዜ አይደለም። አገራችንን ከወያኔ ነጥቀን፤ በአገራችን ኮርተን በሰላም መኖር እንሻለን። ይህ መብታችን ነው። አገራችን የኛ ነች። አገራችን የጥቂት ወያኔዎች መፈንጫ አይደለችም።
ወገኔ፤  ዛሬ ሚያዝያ 13  ቀን 2007 ዓም  በአርበኖች ግንቦት 7 ስም የማደርግልህ ጥሪ አድምጠኝ። በሀይማኖት፣ በብሔር፣ በጾታ ልዩነት ሳታደርግ ዛሬ በአንድነት እንደተሳህ አንድነትህን እንደጠበቅህ ቀጥል። አንድነትህን ለመሸርሸር ወያኔ የማይፈነቅለው ድንጋይ አይኖርም፤ ለወያኔ ዱለታ ጆሮህን አትስጥ። የወያኔ አገዛዝ እንዲያበቃ በአንድነት ተነስ። ዛሬ የጀመርከው ትግል እዳር ሳይደርስ እረፍት የለንም።
አርበኞች ግንቦት 7፣ ከትግራይ፣ ከኦሮሚያ፣ ከአፋር፣ ከኦጋዴን፣ ከጋምቤላ፣ ከቤሻንጉል ድርጅቶች ጋር በመጣመር የአገር አድን ኃይል የመገንባት ሥራውን እያጠናቀቀ  ነው። እኛ ልጆችህ በብሔርም ሆነ በሀይማኖት ሳንከፋፈል፤ ከትግራይ እስከ ኦጋዴን፤ ከአፋር እስከ ጋምቤላ ሁሉንም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ባካተተ ስብስብ ውስጥ አብረን ህወሓትን እየታገልን ነው። ይህ ትግል ግን የአንተ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ነው። የትግሉም የአገሪቷም ባለቤት አንተ ነህ። ስለሆነም ተነስ! “እንቢኝ” በል። ዘርፈ ብዙ የትግል ስልቶችን በመጠቀም ወያኔን አዳክም። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! በትግልህ ፍሬ የአገርህ ባለቤት ሁን።
የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ሆይ!እናንተ የሕዝብ አካላት ናችሁ። የደረሰብንን ብሔራዊ ውርደት እያያችሁ፤  እሮሮዓችን እየሰማችሁ በሕዝብ ላይ መተኮስ በራሳችሁ ጭንቅላት ላይ መተኮስ ማለት መሆኑን ለደቂቃ እንኳን አትዘንጉ። ይልቁኑ ዛሬውኑ ነፃነትና ፍትህ ከጠማው ወገናችሁ ጎን ቁሙ።
የኢትዮጵያ ወጣቶች፤ የወጣትነት የፈጠራ ችሎቻችሁ መፈተኛው አሁን ነው። ለእያንዳንዱ ጥቃቅን ጉዳይ መመሪያ እስኪሰጣችሁ አትጠብቁ። እያሰላችሁ፣ እያጠናችሁ፣ እያደባችሁ፣ ወያኔን ታገሉ።
የታፈረች፣ የተከበረችና የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናደርጋለን።


ብርሀኑ ነጋ
የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር
ሚያዝያ 13  ቀን 2007 ዓም

Dienstag, 14. April 2015

‹‹ጆሮ ዳባ ልበስ›› የተባለው የሠብዓዊ መብት ጥሰት! – ኤልያስ ገብሩ ጎዳና

Elias
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት፣ በነጋሪት ጋዜጣ ታውጆ፣ በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ጠባቂነት ወጥቶ፣ በዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ፕሬዚዳንትነት ነሐሴ 15 ቀን 1987 ዓ.ም በ106 አንቀጾች መጽደቁ የሚታወስ ነው፡፡
መሻሻል አለባቸው የሚባሉ አንቀጾች እንዳሉ ሆነው፣ በሕገ መንግሥቱ ረቂቅ ላይ ሕዝብ በደንብ አለመወያየቱም ሳይዘነጋ፣ እኔን ጨምሮ ብዙ ኢትዮጵያውያን በሕገ-መንግሥቱ መጽደቅ እንስማማለን፡፡
የኢህአዴግ ሥርዓትም ይህ ሕገ-መንግሥት የህጎች ሁሉ የበላይ መሆኑን፣ የሐገሪቷን ብዙ ችግሮች መፍታቱን፣ ለኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦች፣ ህዝቦች እኩልነት መሰረት መጣሉንና ሕገ-መንግሥቱም የግድ መከበር እንዳለበት …ወዘተ. ዘወትር አስረግጦ ይናገራል፣ ይገልጻል፡፡ ከመርህ አኳያ፣ ሕገ-መንግሥቱ መከበር እንዳለበት ብዙዎቻችን የምንስማማበት ሀቅ ነው፡፡

ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ፤ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይ ይገኙ የነበሩ ዜጎች፣ ‹‹ሕገ-መንግሥቱን በሀይል ለመናድ …››፣ ‹‹ሕገ-መንግሥቱን በዐመጽ ለማፍረስ …››፣ ‹‹ሽብር ለመፍጠር…››፣ ‹‹አመጽ ለማነሳሳት …›› ወዘተ በሚሉ ወንጀሎች ተጠርጥረው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ፤ በተለይ በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ሰብዓዊ መብቶቻቸው ክፉኛ መጣሱን ፍርድ ቤት ሲቀርቡ ያሰሙ ከነበሩት አቤቱታዎች መካከል ግንባር ቀደሙ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡
በፍርድ ሂደት እና በፍርድ ውሳኔም ኢ-ሕገ መንግሥታዊ እና ኢ-ፍትሃዊ ድርጊት/እርምጃ እንደተወሰደባቸውም የብዙዎቹ ሮሮ ሆኖም ሰምተነዋል፡፡ ‹‹ምን ያህሉ የወንጀል ክሶች ትክክለኛ ፍትህን አገኙ?›› የሚለው እውነተኛ ጥናት የሚያስፈለገው ይመስለኛል፡፡
ከፍርድ በኋላም፣ በወህኒ እና በማረሚያ ቤቶች የበርካታ ዜጎቻችን ሰብዓዊ እና ሕገ-መንግሥታዊ መብት እንደተጣሰ እና እየተጣሰ እንደሚገኝ ብዙ ጊዜ በቅሬታ፣ በአቤቱታ፣ በበደል ድምጸት፣ በምሬት ቃልና በሀዘን ዕንባ ሰምተናል፣ በተግባርም አይተናል፡፡
ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያን፣ ተማሪዎችና በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይ የሚገኙ ዜጎች ከማዕከላዊ ጀምሮ እስከቃሊቲ፣ ቂሊንጦና ዝዋይ እስር ቤቶች ድረስ ሰብዓዊ መብቶቻቸው መጣሱን ጉዳያቸው በሚታይበት ፍርድ ቤት በተደጋጋሚ አቤቱታ ቢያቀርቡም፣ ክስ ቢመሰርቱም ‹‹መብት ጥሰዋል›› በተባሉት አካላት እና ግለሰቦች ላይ ትክክለኛ ምርመራ ተደርጎ ሕጋዊ እርምጃ ሲወሰድ አይታይም፡፡
የታሳሪዎች ጥያቄ እና አቤቱታ በአግባቡ አለመመርመሩ፣ አለመፈተሹና ከቃል ያለፈ ተግባራዊ የፍትህ እርምጃ አለመወሰዱ፣ የዜጎች ሰብዓዊ መብት ይበልጥ እንዲጣስ በር ከፍቷል! የልብ ልብ ሰጥቷል! ትምክህትን አንግሷል! ያልተጻፈ ሕግ ፈጥሯል! ሥርዓት አልበኝነትን አስፍኗል!
የሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 18/1 ላይ፣ ‹‹ማንኛውም ሰው ጭካኔ ከተሞላበት፣ ኢ-ሰብዓዊ ከሆነ ወይም ክብሩን ከሚያዋርድ አያያዝ ወይም ቅጣት የመጠበቅ መብት አለው›› ይላል፡፡ ይህንና ሌሎች የሕገ-መንግሥቱን አንቀጾች መከበር አለመከበራቸውን አስመልከቶ ‹‹ኢትዮጵያን ማን ይታደጋት?›› በሚለው የእኔ እና አቤል አለማየሁ መጽሐፍ ላይ የቀድሞ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት እና የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር የነበሩት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እንዲህ የሚል ምላሽ ሰጠተው ነበር፡ –
‹‹ሕጉ አልተከበረም፡፡ ባለፈው ሳምንት እንኳን ከዚህ ጉዳይ ጋር የተገናኘ ነገር እየሰማን ነው፡፡ [ይህ ቃለ ምልልስ የተደረገው 03/08/2005 ዓ.ም ነበር] ከማረሚያ ቤቶች የሚወጡ ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት ይፈጸማል፤ ‹‹እመኑ›› ወይም ‹‹በሌላ ሰው ላይ መስክሩ›› ይባላል፡፡ ሠው ወደኋላ ታስሮ፣ መሬት ላይ ተወርውሮ፣ ቀዝቃዛ ውኃ ይደፋበታል፡፡ ስለዚህ ይሄ ሕግ አለመከበሩን፣ኢ-ሰብዓዊ ድርጊቶች እንደሚፈጸሙ ከሚደርሱን ሪፖርቶች እንረዳለን፡፡››
እንግዲህ በዶ/ር ነጋሶ የፕሬዚዳንትነት ዘመን ጸድቆ ሥራ ላይ የዋለው ሕገ መንግሥት በርካታ አንቀጾች አለመከበራቸውን ዶ/ሩ በመጽሐፉ ውስጥ በዝርዝር ምሳሌ እያቀረቡ ምላሻቸውን ሰጥተዋል፡፡
የሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 10/1 እና 2 ‹‹ሰብዓዊ መብቶችና ነጻነቶች ከሰው ልጅ ተፈጥሮ የሚመነጩ፣ የማይጣሱና የማይገፈፉ ናቸው፡፡››፣ ‹‹የዜጎች እና የሕዝቦች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ይከበራሉ›› በሚል ይደነግጋል፡፡ ነገር ግን፣ በርካታ ዜጎች እነዚህ ሕገ-መንግሥታዊ መብቶቻቸው ተገፍፈው ነበር አቤቱታተቸውን ደጋግመው የሚሰሙት፡፡
በሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥረው ከሚያዚያ ወር 2006 ዓ.ም ጀምሮ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለው ክስ የተመሰረተባቸውና ዋስትና ተከልክለው በማረሚያ ቤት የሚገኙት ሴት ጦማሪያን ማኅሌት ፋንታሁንና ኤዶም ካሳዬ፣ ከአያያዝ ጋር በተገናኘ በማረሚያ ቤቱ ችግር እንዳለባቸው በተደጋጋሚ ያቀርቡት የነበረው አቤቱታ፣ ‹‹በማስረጃ የተደገፈ አይደለም፤›› ተብሎ መጋቢት 15 ቀን 2007 ዓ.ም በተሰጠ ብይን ውድቅ መደረጉን የሪፖርተር ጋዜጣ የፍርድ ቤት ዘጋቢ ጋዜጠኛ ታምሩ ጽጌ በነጋታው አስነብቦን ነበር፡፡
የጦማሪዎቹ ጥያቄ፣ ከእናትና አባቶቻቸው ውጪ እንዳይጠየቁ መከልከሉ፣ ሽብርተኛ መሆናቸው በፍርድ ቤት ተረጋግጦ ፍርድ ሳይሰጥባቸው እንደአሸባሪ መቆጠራቸው፣ በሕገ-መንግሥቱ የተደነገገውን ንጹህ ሆነው የመገመት መብታውን የሚያሳጣ መሆኑ፣ ከሌሎች እስረኞች ጋር እንዳይቀላለቁ መደረጋቸውንና ሌሎችንም ደርሰውብናል የሚሏቸውን ችግሮች ነበሩ፡፡ ለዚህ መሰል ሕገ-መንግሥታዊ ጥያቄ ‹‹በማስረጃ የተደገፈ አይደለም›› በሚል ምክንያት በቃላሉ አቤቱታ ውድቅ ይደረጋል፡፡ አቤቱታው በትክክል መፈጸም አለመፈጸሙን ማን ትኩረት እና ግድ ሰጥቶት ይመረምረው?! የመብት ጥሰትን ለመከላከል በፓርላማ ኃላፊነት ተሰጥቶት የተቋቋመው መንግሥታዊው የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ ከአስፈጻሚው አካል ተጽዕኖ ሥር ተላቅቶ ሥራውን በአግባቡ እየተወጣ ነው ብሎ ማሰብ ራስን በቀላሉ ማታለል ይሆናል፡፡
ከወራቶች በፊት፣ ጋዜጠኛ ኤዶምና ጦማሪ ማህሌት ጨምሮ በተመሳሳይ ክስ በቂሊንጦ እስር ቤት ታስረው የሚገኙት ጋዜጠኛ ተስፋለም ወለደየስ እና አስማማው ኃይለጊዮርጊስ፣ ጋዜጠኛና ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉ፣ ጦማሪያኑ አቤል ዋበላ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ ዘላለም ክብረትና አጥናፍ ብርሃኔ በጋራ ሆነው በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ለአራት ወራት ያህል ታስረው በነበረበት ወቅት የደረሰባቸውን አስከፊ እና አሳዛኝ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ለኮሚሽኑ በዝርዝር ቢያቀርቡም ጉዳዩ ‹‹ጆሮ ዳባ ልበስ›› የተባለ ይመስላል፡፡
በእነዘላለም ወርቅአገኘሁ የክስ መዝገብ በጸረ-ሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ ከሚገኙት መካከል ፖለቲከኞቹ ሀብታሙ አያሌው፣ አብርሃ ደስታ፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ዳንኤል ሺበሺ …ከማዕከላዊ ጀምሮ እስከቂሊንጦ እስር ቤት የደረሰባቸው አስከፊ እና አሳዛኝ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ትናንትም ሆነ ዛሬ ተገቢ መልስ አላገኙም!
በጥቅምት ወር 2007 ዓ.ም ፍትህ ጋዜጣ ላይ የጻፋቸው ጽሑፎች ‹‹አመጽ ቀስቃሽ ናቸው›› ተብሎ (በአንድ በኩል ‹አንድም በጻፈው ጽሑፍ የታሰረ ጋዜጠኛ የለም› ብለው የመንግሥት ሃላፊዎች እየተናገሩ ባሉበት ሁኔታ) በግፍ የሶስት ዓመት ፍርድ የተበየነበት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝም በዝዋይ እስር ቤት ህክምና አጥቶ በጀርባ፣ በወገብና በጆሮ ህመም እየተሰቃየ እንደሚገኝ ሰምተናል፣ አድምጠናል፡፡ ይህም ብቻ አይደለም፣ ከአንድ ወር በላይ በማንም ሰው እንዳይጠየቅ መከልከሉም አይዘነጋም፡፡
ከዚህ ቀደምም ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ እና ውብሸት ታዬም ህክምና መነፈጋቸው እንዴት ይረሳል?! ርዕዮት አሁንም ድረስ ይህም ሕገ-መንግሥቱን በግልጽ የሚጻረር የመብት ጥሰት ተፈጽሞባት ይገኛል – ከአንድ ዓመት ከስድስት በር በላይ ከወላጅ እናቷና አባቷ ውጪ በማንም አትጠየቅም፡፡ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና ፖለቲከኛው አንዷለም አራጌ በእስር ቤት በርካታ የመብት ጥሰቶች ተፈጽሞባቸዋል፤ እስከንድርን ከጥቂት ሰዎች ውጪ ማንም እንዳይጠይቀው ተከልክሏል፡፡
የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት (እነአህመዲን ጀበል፣ ኡዝታዝ አብበከር አህመድ፣ የሙስሊም መጽሄት አዘጋጅ አሙበከር ዓለሙ …)ና ሌሎች ሙስሊም ወንድምና እህቶቻችንም ላይ መሰል የመብት ጥሰቶች መፈጸማቸውን ከችሎታቸው ውሎ አድምጠናል ነው፡፡ ፖለቲከኞቹ አበበ ቀስቶ እና ዘሪሁን ገ/እግዚአብሄር ከድብደባ ባለፈ በጆሮ እና በአንገት ህመም ህክምና አጥተው ተሰቃይተዋል፡፡ በእነብ/ጄኔራል ተፈራ ማሞ የክስ መዝገብ የነበሩ ከ40 በላይ ተከሳሾች በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ የደረሰባቸውን የመብት ጥሰት እንባ እየተናነቃቸው ሲናገሩ በችሎት ታድሜ ዘግቤያለሁ፡፡ በተለይ፣ በዚህ መዝገብ የብቸኛዋ ሴት እማዋይሽ ስቃይ ከህሊና አይጠፋም፡፡ በርካታ የኦሮሚያ ክልል ተወላጆች በኦነግ ስም ተጠርጥረው ከታሰሩ በኋላ በማዕከላዊ የደረሰባቸውን መከራ ለችሎት ሲናገሩ አድምጫለሁ፡፡ ባለፈው ዓመትም በማዕከላዊ ለጥቂት ቀናት ታስሬ በነበረበት ወቅት፣ ከጋምቤላ፣ ከአማራ፣ ከኦሮሚያ ….ክልሎች በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው ከታሰሩት መካከል የተወሰኑት በ‹‹ጨለማ ክፍል›› እያሉ የደረሰባቸውን የመብት ጥሰት በአዘኔታ፣ ሲልም ሳቅ እያሉ በግልጽ ነግረውኛል፡፡ በዚህች ጽሑፍ፣ ስንቱን አንስቼ እችለዋለሁ?
ይህን ሁሉ ማለቴ፣ ሕገ-መንግሥቱ ላይ በግልጽ የሰፈረው የዜጎች ሰብዓዊ መብት በግልጽ እና በስውር መደፍጠጡን፣ መናዱን፣ ተሰምቶ ‹‹ጆሮ ዳባ ልበስ›› መባሉን አሁንም ይበልጥ ለማስገንዘብ ነው፡፡ አሁንም ‹‹የዜጎች የሰብዓዊ መብት ይከበር!›› እንላለን፡፡
የሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 9/2 ‹‹ማንኛውም ዜጋ፣ የመንግሥት አካላት፣ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ሌሎች ማኅበራት እንዲሁም ባለሥልጣኖቻቸው፣ ሕገ-መንግሥቱን የማስከበርና ለሕገ መንግሥቱ ተገዢ የመሆን ኃላፊነት አለባቸው›› ይላልና ኢህአዴግ ሆይ! እባክህ በዋነኝነት ራስህ ያወጣኃቸውን ሕገ-መንግሥታዊ ድንጋጌዎች ብትችል ቀድመህ፣ ባትችል …ሰልሰህም ቢሆን አከብረህ ለማስከበር ድፈር! አሊያ፣ የግፍ እና የመከራ መብዛት ከሌሎች ችግሮች ጋር ተደምረው እንደአይን ብሌን የምትሳሳለትን ሥልጣን እስከወዲያኛው በእርግጠኝነት ያሳጡሃልና ልብ ያለው ልብ ይበል!
ቸር እንሰንብት!

Montag, 13. April 2015

የአክራሪዎች፣ የተስፈንጣሪዎችና የአሸባሪዎች ዘመን

ይሄይስ አእምሮ (አዲስ አበባ)
ወቅቱ ለክርስቲያኖች የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል ሰሞን እንደመሆኑ በዓሉ የሚመለከታቸውን አንባቢ ወገኖቼን “እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው [በሰላም] አደረሳችሁ” ማለትን እወዳለሁ፡፡ የደርግ ጊዜ አንድ ትዝታ አለኝ፡፡ በአብዛኛው በሀገር ወዳድ ደናቁርት የታጨቀው የደርግ መንግሥት ሠለጠንኩ ብሎ ሃይማኖተቢሱንና ሃይማኖተኝነትን ከልካዩን የሶሻሊዝም ሥርዓት ካወጀባት ጠማማ ዕለት ጀምሮ በዓል በመጣ ቁጥር በተለይም የአብዮቱ በዓል በሚከበርበት ወቅት “እንኳን ደረሳችሁ” ይል ነበር – ያ ለአገራችን ባዕድ የነበረ የአገዛዝ ሥርዓት አንዲት ፊደል ላይ እንዲያ ይጨነቅ የነበረው፣ ሰው ለበዓሉ የደረሰው በራሱ እንጂ በፈጣሪ እንዳልሆነ ለማጠየቅ ነበር፤ የሥርዓቱ አቀንቃኞች በአብዛኛውና በግልጽ ይዞታቸው ሶሻሊስትና ኮሚኒስት እንጂ የሃይማኖት ሰዎች አልነበሩም – አንዳንዶች አምልኮታቸውን በኅቡዕ ያከናውኑ እንደነበርና ልጆቻቸውን ሣይቀር በድብቅ ክርስትና ያስነሱ እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ በመሠረቱ አንድ ሰው ምንም ዓይነት እምነት ላይከተል ይችላል፡፡ መብቱም ይመስለኛል፡፡ ነገር ግን ሃይማኖት አልባነትን በግድ መንግሥታዊ ሥርዓት ውስጥ በማጫፈር በእምነትና በሃይማኖት ጸንቶ የኖረን ሕዝብ በአንዴ እግዜርን ወይም አላህን ወይም የምታመልከውን ሌላ መንፈሣዊ አካልን ክደህ ኮሚኒስት ሁን ማለት የደርግን ብልህነት ሣይሆን ጅልነት የሚያሣይ ነበር – ሠለጠነች ቢሏት ጊዜ የባሏን መጽሐፍ ያጠበችውን ሴት ዓይነት ጅልነት፡፡ መጨረሻው ባለማማሩ ይከተለው የነበረውንም የአካሄድ ሥርዓት አይረቤነት በእግረ መንገድ መረዳት አይከብድም፡፡ እንዲያው ትዝ ብሎኝ ነው፡፡
ርዕሴን በእንግሊዝኛ ብጽፈው ኖሮ “The Age of Terrorists, Extremists and Deviants” በሚል እንዲነበብ አደርገው ነበር፡፡ ያለንበትን ዘመን ከየአቅጣጫው ስንቃኘው ጥቂት የማይባሉ አክራሪዎች፣ ተስፈንጣሪዎችና አሸባሪዎች ዓለማችንን እያተረማመሱ እንደሚገኙ መገንዘብ አያስቸግርም፡፡ ሌላውን ዓለም ለአሁኑ እንተወውና ወዳገራችን ተስፈንጣሪዎችና ምናምንቴዎች እንመለስ፡፡ በነሱ ነውና መቅኖ አጥተን የቀረነው – “ትንቢትሰ ይቀድሞ ለነገር” የምትለዋን ሐረግ እንድታስታውሱልኝ ግን ልማጠን፡፡
ትናንት አንድ ወዳጄ ቤቴ መጥቶ በላፕቶፑ ከዩትዩብ ያወረዳቸውን አንዳንድ ድንቃድንቅ ቃለ መጠይቆችና ልዩ ልዩ ዝግጅቶች አስኮመኮመኝ፡፡ ሁለቱን ተስፈንጣሪዎችና ጠብ ጫሪዎች የተመለከትኩት በዚያን ጊዜ ነው፡፡ አንደኛው ተስፈንጣሪ መምህር ገብረ ኪዳን ደስታ ይባላል፡፡ እኔን የታሪክ ተመራማሪ ያድርገኝና የታሪክ ተመራማሪ እንደሆነ ተነግሮለታል፡፡ አፄ ቴዎድሮስን እንዴት አድርጎ እንደሚስላቸው ብታዩ ትደመማላችሁ፡፡ አበሻቅጦ፣ አበሻቅጦ ነው የለቀቃቸው፡፡ ሲናገር ደግሞ ታሪክን እንደሚተርክ ሣይሆን በስሜት እየተወራጨና ክፉኛ እየተቆጣ እዚያው እቦታው ላይ ያለ ያህል ሆኖ ነው፡፡ የታሪክ ተመራማሪና ተንታኝ – በኔ ጥራዝ ነጠቅ ግንዛቤ – ትንታኔውንና ሀተታውን ማቅረብ ያለበት በጥላቻና በበቀል ስሜት እየተንዘረዘረ ሣይሆን የሆነውን ነገር እንዳለ በተረጋጋና አድልዖ በሌለበት ሁኔታ ነው – ታሪክ ነዋ! የዛሬ ሣይሆን የዱሮ ዘመን ድርጊት ነው፡፡ ዛር ከፈረስ የመሆን ወገንተኝነት ለታሪክ ተመራማሪ የሚፈቀድ አይመስለኝም፡፡ ይህ የታሪክ ተመራማሪ ግን አንድ ቦታ ሲናገር እንደሰማሁት አንሻፍፌም ቢሆን እጠቅሳለሁ፤ “ሀፄ ዮሐንስ ምኒልክን ቢያስሩት ኖሮ ጥሩ ነበር፡፡ መታሰር ነበረበት፡፡ ሀገር ከሃዲና ሻጭ ስለነበረ የሀፄ ዮሐንስ መኳንንትና መሣፍንት ‹ይህን ሰው ነገር ሳያመጣ እንሰረው› ሲሉ ሀፄው በምሕረት ማለፋቸውና ‹መኳንንቴ ሊያስሩህ ይፈልጋሉና አምልጣቸው› ብለው የሸዋን ንጉሥ እንዲያመልጥ ማድረጋቸው ትክክል አልነበረም፡፡…” እኔ የታሪክ ተማሪ አይደለሁም፡፡ ባልሆንም ግን እንዲህ ያለ ጭራሽ ወደ አንድ ወገን ያጋደለ የታሪክ ትንተናና ቅጥ ያጣ ዘረኝነት ስመለከት የምናደድና ምሁር ተብዬውን የምቃወም መሆኔን መግለጽ እፈልጋለሁ፡፡ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴን የተቸበትንም መንገድ ስመለከት አዝኛለሁ፡፡ ባህሩ ዘውዴ ኢትዮጵያ በአጸደ ሕይወት ካሏት ብርቅ የታሪክ ተመራማሪዎች አንዱ መሆኑን አውቃለሁ፡፡ ሁሉም ነገር ለከት ሊኖረው ይገባል፡፡
ዐፄ ምኒልክንና ዐፄ ቴዎድሮስን ለማቋሸሽና በሕዝብ እንዲጠሉ ለማድረግ ይህን ያህል ዘመቻ ማድረግ ትርፉ ለጊዜው ትዝብት ብቻ ቢሆንም እውነቱ ባለበት ይኖራልና የማስተባበሉን ዋና ኃላፊነት ለባለሙያዎቹ መተውን መርጫለሁ – አልተከታተልኩ ሆኖ እንጂ በጊዜው መልስ ተሰጥቶበትም ሊሆን ይችላል፡፡ ሰውዬው ግን በግብዝነቱ አሳዘነኝ፡፡ ደግሞም ሁለት ፀጉር ያበቀለ እንደኔው ትልቅ ሰው ይመስላል፡፡ ለምን ይህን ያህል ርቀት ተጉዞ ራሱን ትዝብት ውስጥ ማስገባት እንደፈለገ አልገባኝም – የእውነት አንጻራዊነት ደግሞ አስደነቀኝ፤ እውነት ሺህ ጊዜ አንጻራዊ ትሁን እንጂ ደግሞ ይህ ሰው ይህን ያህል ማፈንገጡ በሰዎች ተፈጥሮ እንድገረም አስገድዶኛል፡፡ ነገሥታቱን በዘራቸው ምክንያትም ይሁን በሌላ አይጥላቸው ወይም በግድ ይውደዳቸው ማለቴ አይደለም፤ ነገሥታቱ ምንም ጥፋት የሌለባቸው ምሉዕ በኩልሄ ናቸው ማለቴም አይደለም – ሰዎች እንደመሆናቸው እንደማንኛችንም ተራ ዜጎች ያጠፋሉ፤ ያለማሉም፡፡(በነገራችን ላይ ስለትግራይ ነገሥታትም ሆነ መሣፍንት እንዲሁም ስለ ዳግማይ ወያኔ የአስተዳደር በደል አንድም ነገር ትንፍሽ አላለም፤ ይህ ደግሞ ፍጹማዊ አድልዖና ወገናዊነትን ያሳያል፤ ምራቅ ከዋጠና ፈሪሃ እግዚአብሔር ካለው ጨዋ የትግራይ ሕዝብ የተገኘ የታሪክ ተመራማሪ እንዲህ ያለ ጭፍን አስተያየት ይሰነዝራል ተብሎ በጭራሽ አይጠበቅም – በኔ ግምት ንግግሩ ደመ-ሞቃታዊ ግልብ አስተያየት እንጂ በምርምር የተደገፈ እውነተኛ ታሪክ ነው ማለትም ያስቸግራል)፡፡
እኔ እምለው ታዲያ ጥላቻችንንም ይሁን ውዴታችንን የምንገልጽበት መንገድ አግባብ ይኑረው ነው ፡፡ ስንወድ፣ ስንወድ ሰዎች ባልዋሉበት ጦር ሜዳ ሺዎችን እንደገደሉና እንደማረኩ እያስመሰልን የምንኳሽ ፣ ስንጠላ ስንጠላ ደግሞ ጥቁሩን ነጭ፣ ነጩን ጥቁር እያደረግን ጥላሸት የምንቀባ ከሆነ አመክንዮታዊ ተፈጥሯችንን ገደል ከተትነው ማለት ነው፤ እንዲህ ስናደርግ ታሪክ ሣይሆን ኩሸትና ምናባዊ ገድል እየጻፍን ነው – እንደዚህ ያለ ነገር መጻፍ ወይ መናገር ካማረን ደግሞ በታሪክ ትምህርት አሳብበን ሣይሆን በልቦለድ ውስጥ ስሜታችንን መግለጽ እንችላለንና ወደዚያ መግባት ነው – የሰውዬው አካሄድ አህያን ተገን አድርጎ ጅብን እንደመውጋት ነው – ትልቅ የስብዕና ኪሣራ፡፡ ሰው የተባለ ፍጡር ደግሞ እንዲህ እንዲሆን አይጠበቅበትም፡፡ እንስሳ ብንሆንም ማሰብና ማመዛዘን የምንችል የሌሎች እንስሳት አለቃዎች በመሆናችን የማስተዋል ጥበብን እስከዚህን ድረስ በወረደ ሁኔታ ልንነጠቅ አይገባም፡፡ የዘረኝነትን ጭምብል አውልቀን፣ የሆድ አምላኪነትን ምኩራብ አፍርሰን፣ የጥላቻን ግምብ ንደን በሃቅ መፍረድ ካልቻልን ሰው መሆናችን ይቀርና በአንዲት አጥንት ሣቢያ የሰገሌን ጦርነት እንደሚያስታውሱን ውሾች እንሆናለን፡፡ ይህ ደግሞ ከንቱነትና እንደነቢዩ ሰሎሞን አነጋገር ንፋስንም እንደመከተል ያለ ሞኝነት ነው፡፡ ለምኑ ብለን? ነገ ጧት ሁሉም እርግፍ ብሎ ለሚቀረው? አቅል ጀባ መምህር ገብረ ኪዳን! ከጥቂት ጊዜ በኋላ ትግሬና አማራ ይቅርና የሰው ዘር በአጠቃላይ የሚበጠርበትና የሚበራይበት ዘመን ይመጣል፡፡ ያኔ እውነት የምትነግሥበት፣ ሀሰት የምትዋረድበት አዲስ ዘመን ይብታል፡፡ ያኔ ላለማፈር አሁን ትንሽ ስንቅ መያዝ ይገባናል፡፡ ጊዜ የሰጠው ቅል ድንጋይ መስበሩን ካላቆመ ድንጋዩም ቅል ለመሆን እንደሚመኝ ማሰብ ተገቢ ነው፡፡ ከኅሊና መታወር አምላክ ይሠውረን!
ታሪክ ሲጻፍ በስማ በለው ሊሆን አይገባም፡፡ የስማ በለው ታሪክ አፈ-ታሪክ(ሌጄንድ) እንጂ እውናዊ ታሪክ ሊሆን አይችልም፡፡ ታሪኩን ወደድነውም ጠላነውም እኛ ግን እንዳለ ማስተላለፍ ይኖርብናል፡፡ አንድ ሃኪም ጠላቱ ታሞ ቢመጣ በመርፌ ወይ በከኒና ሊገድለው እንደማይገባ ሁሉ(በሙያዊ ሥነ ምግባር ኮዱ መሠረት አስቀድሞ መሃላም ገብቷልና) አንድ የታሪክ ቅንጫቢም እኛ ጋ ሲደርስ ስለማንፈልገው ብቻ አንሻፈን መናገሩ ወይም መጻፉ እኛን ለትዝብት ከሚዳርገን ውጪ ታሪኩን አንሰርዘውም፤ እውነት አትሰረዝምና፡፡ ስለሆነም ያ አፈንጋጭ የታሪክ ሰው ራሱን እንዲመረምር በዚህ አጋጣሚ ልጠቁመው እወዳለሁ፤ የጎመን ጥጋብ ያልፋል፤ የጉሽ ጠላ ስካርም ይበርዳል፡፡ ለነገሩ እንኳንስ ብዙም የሚያስደስት ነገር የሌለው የኢትዮጵያ ታሪክ ይቅርና ሰማይና ምድርም ያልፋሉ – ሊያውም ይህም ሊሆን የቀረው ጊዜ ከአንድና ሁለት ሐሙሶች የሚዘል አይመስለኝም፡፡ ጤናማ አተያይ ለሁላችን እንዲያድለን ፈጣሪን እለምናለሁ፡፡ ደግሞስ አንዳችን አንዳችንን አበሻቅጠን የት እንደርሳለን፡፡ የሁላችንም ታሪክ በየራሱ የቆመ ሣይን እርስ በርሱ የተጋመደ ነው፡፡ ትግሬ ውስጥ አማራ አለ፤ አማራ ውስጥ ትግሬና ኦሮሞ ሌላውም አለ፡፡ ተማርን የምንል ወገኖች ግን አይፈጥሩ ጠብና ቅራኔ እየፈጠርን ደጉን ባላገር ባናምሰው ይሻላል፡፡ ማወቃችንን በቅጡ እናድርገው፡፡ ልሂቅነት ለዕልቂት ከበሮ ጉሰማ ሣሆን ለዕርቅና ለዕድገት አቅጣጫ ትለማ እናውለው፡፡ ኃላችንን ወደ ማፈርስ ሣይሆን ወደመግናበት አናዙረው፡፡ ጥላቻን መዝራት ይብቃን፡፡ ወደፍቅርና መተሳሰብ አምባ እንውጣና ሌሎች ያበላሹትን እኛ እናቃና፡፡ በተበላሸና በተሰባበረ መንገድ እየተጓዝን ቁስላችን ይበልጥ እያመረቀዘ የሚሄድበትን ሥልት ከመንደፍ ይልቅ በምንፈወስበት ዘዴ ላይ ጊዜና መላ አቅማችንን እናፍስስ፡፡…
ሌላው አፈንጋጭ ወይም ተስፈንጣሪ ደግሞ ያ የሰንበት ጽንስ ተስፋየ ገብረ“ባብ” የሚባለው ነው፡፡ ይህን ሰው አደብ የሚያስገዛ ጠፍቶ ይሄውና ሽብልቁን እየቀበቀበብን ከኛም አንዳንዶቻችን የሚቀበቀብብንን ሽብልቅ ባለማጤን እያጨበጨብንለት መቃቃርንና ግጭትን ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ እየነዛ ይገኛል፡፡ ሼክስፒር እንደሚለው – እጠቅሳለሁ – “To do a great right do a little wrong” እንደሚለው ይህን የእባብ ልጅና አለምነው መኮንን የተባለውን የዲያብሎስ ውላጅ በአንዳች ጥበብ የሚያስወግድ ኃይል ቢኖር በኔ በኩል ድጋፌን እንደማልነፍግ እገልጻለሁ – የንስሃ ዕድሜ እንዳገኝ ከመጸለይ ጭምር፡፡ ሰይጣንን ማስወገድ ወይም ቢያንስ አደብ ማስገዛት ከኃጢኣት አይቆጠርም ባይ ነኝ፡፡ ጠላትን መውደድ ጥሩ ነው፡፡ ነገር ግን ስትወደው የሚጠላህን መሠሪ ጠላት ከይሁዳ እንጂ ከተራ ጠላት አትመድበውም፡፡ እነዚህን መሰል ፀረ-ሰውና ፀረ-እግዚአብሔር ግለሰቦች ሰባት ጊዜ ሰባ ብቻም ሣይሆን ሰባ ጊዜ ሰባት መቶ ያህልም ይቅር ቢባሉ ተፈጥሯዊ የፀላኤ-ሠናያት ባሕርያቸውን ሊያቆሙ አይችሉም – ተፈጥሮን ደግሞ ተመክሮ አይመልሰውም፡፡ ይሁዳ ምሕረትን እንደማያገኝ ክርስቶስ በአንደበቱ ተናግሯል – “የሰውን ልጅ በመሳም አሳልፎ የሚሰጥ የወፍጮ መጅ ባንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቁ ባህር ቢወረወር ይሻለዋል” በሚል ልዩ አንደበታዊ ማኅተም፡፡ ስለሆነም ተስፋዬ ገብረባብና ይሁዳ አንድ ናቸውና ሞት ቢያንሳቸው እንጂ አያንሳቸውም የሚል እምነት አለኝ፡፡ ጨካኝ ሆኜ ግን እንዳይመስላችሁ፡፡ በፍጹም፡፡ ያጨከነኝ ሥራቸው ነው፡፡
ተስፋየን ይሁዳ ያልኩበት ምክንያት የበላበትን ወጪት በመስበሩና ያደገባቸውን ሁለት ማኅበረሰቦች ለማጋጨት ከራሱ ይሁን ከሌላ ተቀብሎ የተሸከመውን ታሪካዊ ኃላፊነት ሳይታክትና ሳይሰለች እየተወጣ የሚገኝ የእፉኝት ልጅ በመሆኑ ነው፡፡ ይህ ሰው ኢትዮጵያ ውስጥ ተወልዶ የእምዬ ኢትዮጵያን ጡቶች እየጠባ ቢያድግም አሁን እንደ ቀትር እባብ እየተቅነዘነዘ የሚያደርገውን ስንታዘብ ሰውዬው በማንነት ኪሣራ የተዘፈቀና ያን ለመርሳት በሚያደርገው ጥረትም የሚሠራውን እንደማያውቅ ሰው ትልቅ ጥፋት እያደረሰ መሆኑን ነው፡፡ በውነቱ ሰውዬው በራሱ አንደበት እንዳረጋገጠውና በድረገፆች በተጋለጠው መታወቂያውም እንደተመለከትነው ኢትዮጵያዊ አይደለም፡፡ ኢትዮጵያዊ ካልሆነ ታዲያ ስለኢትዮጵያ ይህን ያህል አብዝቶ መጨነቁ ለምን ይሆን ብሎ መጠየቅ አግባብ ነው፡፡ እኔ ለምሣሌ ስለ ኬንያና ታንዛንያ ከሀገሬ በላይ እንቅልፍ አጥቼ አልጨነቅም፡፡ “የራሷ አርሮባት የሰው ታማስል” እንዲሉ ካልሆነ በስተቀር ተስፋየ ሀገሬ ናት የሚላት የቀድሞዋ የኛም ሀገር ኤርትራ ብዙ የልማትና የብልጽግና ሥራ እንዲሠሩላት እጆቿን ዘርግታ ልጆቿን እየተማጸነች በምትገኝበት ወቅት ይህ ሰው ስለኢትዮጵያ እንዲህ መባዘኑ ይገርመኛል፡፡ ይህ ሁሉ መቸገሩ አለነገር እንዳልሆነ ደግሞ ለብዙዎቻችን የተሠወረ አይደለም፡፡ አንድ ሰው እንቅልፍ አጥቶ ማደር ያለበት ስለራሱ ጉዳይ መሆን አለበት፤ ከዚያ ውጪ ግን ያልበላውን እንደማከክ ነው፡፡ የሚያስደንቀው ደግሞ ህ ሰው እየባሰበት እንጂ እየቀነሰለት ሲሄድ አለመታየቱና ደህና የሚባሉ ኢትዮጵያውያን ሣይቀሩ የጥፋቱ ተባባሪዎች እየሆኑ መምጣታቸው ነው፡፡ “ዘይገርም ሻሸመኔ ትብስ ኮፈኔ” ማለት ይሄኔ ነው፡፡ ዘመነ ግርምቢጥ!
በትናንትናው የጓደኛየ የቪዲዮ ግብዣ ኦ.ኤም.ኤን(ኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ) የተባለ የሚዲያ አውታር ያሠራጨውን አንድ ዝግጅት ተመለከትኩ፡፡ የቀድሞ ወዳጄ በፈቃዱ ሞረዳ ጠያቂ ጋዜጠኛ፣ ተስፋየ ገብረባብ ተጠያቂ እንግዳ ሆነው ነበር “እንግዳ” በሚል ፕሮግራማቸው ይህን ጉደኛ ውሉደ ዲያብሎስ ያሳዩን፡፡ በፈቃዱን ሳውቀው ኢትዮጵያዊ ሆኖ ነው፡፡ አሁን ግን ያነሰብኝ መሰለኝ – ግምቴ ትክክል ከሆነ ደግሞ በጣም ነው የማዝነውና የምጨነቀው – በተጣባን ሾተላይ እተክዛለሁ፡፡ በቃለ ምልልሱ እንደተረዳሁት ተስፋየና በፈቃዱ ቀደም ሲል ዐይጥና ድመት ነበሩ – ያ ጥሩ አልነበረም፡፡ ያስታረቃቸው ነገር ሲታይ በፈቃዱ በተወሰኑ ሰዎች ግፊት ምክንያት ዘረኛ እንዲሆን መገደዱን “የሚያበሥር” ግጥም በኢትዮጵያ ዛሬ ድረገፅ ተስፋየ አንብቦ የምኞቱን ሥኬትና የዓላማ መመሳሰል ካስተዋለ በኋላ ሁሉንም ቂሙን/ቁርሾውን እርግፍ አድርጎ በመተው በፈቃዱን ሊወደው እንደቻለ ነው፡፡ ይህ ፍሩዳዊ የምላስ ወለምታ – ኧረ ግልጽ ነው የምን ወለምታ – የሚያሳየን ተስፋየ የሚፈልገው ኢትዮጵያ ውስጥ ሁሉም ዜጋ እየተነሣ በየፈፋውና በየጢሻው በመውረድ ፍጹም ዘረኛና አንዱ ከአንዱ የማይስማማ ሌባና ፖሊስ እንዲሆን መሻቱን ለዚያ ዓላማ ሥኬትም የማይፈነቅለው ድንጋይ አለመኖሩን ነው፡፡ ይህ “የሰው ሀገር ሰው” የራሱን የማንነት ኪሣራ ችግር ሳያስወግድ በበጎች መሀል እንደገባ ተኩላ ኢትዮጵያን ለመበታተን የሚጥሩ ታሪካዊ ጠላቶችን እያገለገለ የሚገኝ ሁለት አፍ እንዳለው ሠይፍና ጎራዴ ሊታይ የሚገባው መሠሪ ጠላት ነው፡፡ ይህ ዓይነቱ አደገኛ ሰው በእንጭጩ ካልተቀጨ – አሁንና ዛሬ ‹እንጭጭ› የሚልን ቃል መጠቀም ከቻልኩ – የዞረ ድምሩ ከባድና በቀላሉም የማይፈታ ነው፡፡
ስለተስፋየ አንዲት ነገር በምሳሌ ልናገር፡፡ እንደዛሬው ሣይሆን በዱሮው ዘመን ጦጣን የሰው ልጅ ይይዛታል፡፡ ከሰው ጋር የከረመችዋን ጦጣ ዘመዶቿ ጋር እንድትቀላቀል ወደ ጫካ ቢሰዷት እርሷ ዕውቀቷ አነስተኛና ጦጥኛ በመሆኑ ልትቀላቀል ትሄዳለች፡፡ ነገር ግን በዚያን ደግ ዘመን ማኅበረጦጣ ያቺን ከሰው አምልጣ ወይም ነፃነቷን በሰዎች ይሁንታ አግኝታ የመጣች ጦጣ በቡጢና በክርን እየደለቀ ያባርራታል እንጂ አያስጠጋትም፡፡ ምክንያቱም ሰው ሰው ትሸታቸዋለችና የነሱ ቅርጽ ቢኖራትም በጠረኗ ምክንያት አያስጠጓትም፡፡ የሁለት አገር ሰው ፣ የሁለት አገር ፍጡር መሆን ዕዳ እንግዲህ እንደዚህ ነው – አጣምሞ እንዳይፈጥር ከመጸለይ ውጪ ምንም ማድረግ አይቻልም፡፡ሁሉም በጥርጣሬ ዐይን ስለሚመለከተው የማንነት ቀውስ ውስጥ ይዘፈቅና ከሚደርስበት ሥነ ልቦናዊ ችግር የተነሣ የወንጀለኝነትን ባሕርይ በቀላሉ ይላበሳል፡፡ ከዚያም የራሱ ጤናማ ኅሊናና ቀና አስተሳሰብ ስለማይኖረው እንደጠፍ አህያ ያገኘው ሁሉ የፈለገውን ይጭነዋል፤ ወደፈለገውም ይልከዋል፡፡
ሲላላክም መጠነኛ መቁሽሽ ስለሚሰጠው ስለሚያገኘው ድርጎ እንጂ ስለሚሠራው ዕኩይ ተግባር ቅንጣት አይጨነቅም – የሞራልና የሃይማኖት ዕሤቶችም ስለሌሉት ሕይወቱ በብዙ መልክ የተሰነካከለ ነው፤ በመጠጥ የሚናውዝ፣ በሴሰኝነት ካገኘው ጋር የሚከንፍ፣ በቃላባይነት ሁሉንም የሚያስቄም ከንቱ ዜጋ ሆኖ ይቀራል፡፡ ይህ ዓይነት ሰው እንደነዱሽ ነው – ልክ እንደሮቦት፡፡ ይህን መሰል ሰው ወደኅሊናው በቀላሉ አይመለስም፡፡ ቢመለስም ምናልባት እንደይሁዳ ራሱን ይገድል ይሆናል እንጂ በንስሃ ታጥቦና ተጸጽቶ ጥሩ ሰው የመሆን ዕድሉ በዜሮና በአንድ የመቶኛ ስሌት ውስጥ የሚገኝ ነው፡፡ ከዚህ ይሠውር ውድ ወገኖቼ፡፡ በሀገራችን ስንትና ስንት እንደነዱሽ ቀፎ ራስ ሞልቷል መሰላችሁ! ሆዱ ከሞላ እናቱንም፣ሚስቱንም፣ ልጆቹንም ባወጡ የሚሸጥ ገነት ዘውዴንና አለምነው -ገዱ – ልደቱ አያሌውን የመሰለ ብኩን ዜጋ ሞልቷል፡፡ እውነቴን ነው የምላችሁ እነዚህን “ሰዎች” ሳስብ ሰው ሆኜ መፈጠሬን እጸየፋለሁ፡፡ የጠራ ድህነት ወርቅ አይደለም እንዴ እባካችሁ!
ተስፋየ አቅሉን ስቶ የሚራወጠው ኢትዮጵያውያንን ለማደባደብ መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ የነበፈቃዱ ዓላማ ግን ብዙም አልገባኝም፡፡ “ያልወለድኩት ልጅ ቢለኝ አባባ፣ አፌን አለው ዳባ ዳባ” ይባላል፡፡ ዛሬ ከመሬት ተነስቶ ተስፋየን “ኦሮሞ ነህ” ማለት መንስኤው ግልጽ ቢሆንም ውጤቱን ግን ማጤን ያስፈልግ ነበር፡፡ ተስፋዬ ለዓላማው ሥኬት ካዋጣው ልክ እንደወያኔ የማይሆነውና የማያደርገው ነገር የለም፡፡ የማርስና የቬኑስ ዜጋ ነህ ቢሉትም በደስታ ይቀበላል – እንዲህ ዓይነቱ ነገር በጣም ይስማማዋል(የቬኑስ ዜጋ እንኳን አሁንም ነው – ቬነስ ከወሲብ ጋር እንደምትገናኝ አስቡልኝ፤ ቬኔሪያል ዲዚዝ … ምናምን ከዚያ የመጣ ነው ይባላል፤ የሼክስፒርን ምናባዊ ፍጡር ሸፍጠኛውን ሻይሎክም (በቬኑሱ ነጋዴ ተውኔት) አስታውሱ)፡፡ ይህ ዓይነቱ “ማዕረግ” ለስንኩል ዓላማው ትልቅ እገዛ ያደርግለታል፡፡ ብዙም ባልተማረው ማኅበረሰባችን ውስጥ እንደዚህ ዓይነት የጭቡ ሥራ ምን ዓይነት ዳፋ ሊያስከትል እንደሚችል የቲያትሩ ደራሲያን ሊያስቡበት በተገባ ነበር፡፡ የሚያጣላ አላጣንም፡፡ የብሔር ማንነት ካባ ሳይደረብለት የሚያቆራቁሰን ሞልቶ ሳለ ይህን አሸባሪ ሰው – ይህን ተስፈንጣሪ ወጪት ሰባሪ – ይህን የአእምሮ በሽተኛ ሰው “ኦሮሞ ነህ” ማለት ትርጉምም ስሜትም የሚሰጥ አይደለም፡፡ ቀን ሲያልፍ የሚያስተዛዝብና እሳት የማያጫጭር፣ የማያቀባብርም አጉል ድርጊት መሥራት ሞኝነት ነው፡፡
በፈቃዱ ሞረዳም ትልቅ ሰው ነው፡፡ በጣም የማከብረውና በጦማር ጋዜጣው ስለእናት ሀገሩ ኢትዮጵያ ብዙ የደከመ ሰው ነው፡፡ ጉድና ጅራት እንዲሉ ሆኖ አሁን በማንኛውም ምክንያት ይሁን ወደታች ወርዶ ፈፋ ውስጥ ተወሽቆ ከሆነ ከምር አዝናለሁ፡፡ “የት ይደርሳል የተባለ ጥጃ ሉካንዳ ደጅ ታዬ” እንዲሉ ካልሆነ በስተቀር ወደላይ መሄድ ቢያቅት እንኳን ባሉበት መቆየትም ትልቅ ጠጋ ነው፡፡ ሰዎች ሰዎችን ለማሳሳት ሆን ብለውም ሆነ ሳያውቁ አንዳንድ ነገር ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ እነሱን በጭፍን ከተከተልን ገደል እንገባለን፡፡ እርጥቡን ከደረቅ እየለየን በአስተውሎት ከተራመድን ግን ጊዜ ይፍጅ እንጂ የተሳሳተን ለማረምና ወደ ፍጹም ሰውነት ለመቅረብ ይቻለናል – ፍጹም መሆን በሒሣባዊ ትወራ ይጠጌ አይነኬ ቢሆንም፡፡ ታጥቦ ጭቃ መሆን በታሪክም ይሁን በትውልድ ራስን ዝቅ ያደርጋል፡፡ የበላሁትን ቁርስ ያህል የማውቀው ፍቄ እንዲህ ሆኖ ከሆነ ለማመን ብቸገርም እንደሚመለስ ግን ተስፋ አለኝ፡፡ እርግጥ ነው – ተስፋ መቁረጥ ብዙ ዕዳ ውስጥ እንደሚከት አላጣውም – ቢሆንም ፍቄን በዚህ ጠርጥሬው አላውቅም፡፡ በሥነ ግጥሙ እንደተረዳሁት “በነሱ ግፊት እኔም ዘሬን አሽትቼ ወደዘሬ ተቀላቀልኩ” የሚለው አስተሳሰብ ደግሞ አይሠራም፡፡ እንደተስፋየ አጠራር ኢትዮ-አማሮች የሚባሉት “አክራሪዎች” የፍቄን ጽኑ አቋም አናግተውት ከሆነ ስህተቱ አሁንም ከፍቄ ራስ አይወርድም፤ እንዲያ ከሆነ ዱሮም ፍቄ ባላመነበት ኢትዮጵያዊነት ይዳክር ነበር ማለት ነውና፡፡ ለመሆኑ እነሱ እነማን ናቸው? ስንትስ ናቸው? እነሱ ዘረኛ ቢሆኑ እኛስ ስህተትን በስህተት ልናስተካክል ይገባናል ወይ? የምወደው ፍቄ ያስብበት፡፡ ይህን የምለው በተመለከትኩት ቃለ ምልልስ በግልጽ ሣይሆን በ“ሦስተኛው ዐይኔ” አማካይነት የተገነዘብኩት አንዳች ነገር ስላለኝ ነው፡፡ ግጥሚቱ ቀላል መልእክት አይደለም የታቀፈችው፡፡ “ዘረኛ ሆነው ዘረኛ አደረጉኝ” ትላለችና፡፡
የሁለቱ ሰዎች መታረቅ ደስ ይለኛል፡፡ የታረቁት በፀረ-ኢትዮጵያዊነት የዓላማ ቁርኝት ከሆነ ግን ዕርቃቸው አሳሳቢ ነው፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ የሀገራችን ችግር የዘር አይደለም፡፡ ችግራችን የዴሞክራሲ ዕጦት ነው፤ የመልካም አስተዳደር ዕጦት ነው፤ የተማረና የተመራመረ ዜጋ ሥልጣኑን ያለመያዝና ሕዝባዊ ወደሆነ የዕድገትና ብልጽና አቅጣጫ ያለመግባት ችግር ነው ለዘመናት የተጠናወተን፤ የማይምነት መንሠራፋት ነው አበሳችን፤ የሆዳምነት መንገሥ ነው ችግራችን፤ የራስ ወዳድነት መንፈስ የሃይማኖት ያህል መስፋፋት ነው ራስ ምታታችን፤ በሙስናና በጉቦ መበስበስ ነው ናላ የሚያዞር ማኅበራዊ ነቀርሳችን፡፡ ዘረኝነቱ ጎልቶ የታየው ካለፉት 24 ዓመታት ወዲህ እንጂ ቀደም ሲል ይህን ያህል አሳሳቢ ችግር አልነበረም፡፡ ያገኛትን ትንሽ ቀዳዳ ተጠቅሞ ጎጃሜ ጎጃሜን ዌም ጎንደሬ ጎንደሬን ቢቀጥር፣ ሐረርም ሐረሬን ወለጋም ጊምቢንና ነቀምቴን ይስብ ነበር፡፡ ሁሉም በየፊናው የፈለገውንና የመሰለውን ያደርግ ነበር እንጂ አንድ ዘውግ ተለይቶ የሚወቀስበት ሁኔታ ሊኖር አይችልም፡፡ ይልቁንስ ፈታ እንድትሉ አንድ ቀልድ ቢጠየ ላስታውሳችሁ ከፈለጋችሁ፡- አንድ ኦሮምኛ ተናጋሪ ጄኔራል ወታደር ለመሆን ያመለከቱ ተመዝጋቢ ወጣቶችን በተርታ አሰልፈው የቅጥር ፎርም ለማስሞላት ወደግቢ ያስገባሉ አሉ፡፡ የሚያስገቡት ታዲያ ኦሮሞ ኦሮሞውን እየመረጡ ነው አሉ፡፡ ስማቸውን ሲጠይቁ ታዲያ ተሰላፊው ስሙን “ደቻሳ” ሲል ጄኔራሉ “ግባ”፣ “ጉርሜሣ” ሲል “ግባ”፣ “ፈይሣ” ሲል “ግባ”፣ “መልካሣ” ሲል “ግባ”፣ “ድንቄሳ” ሲል “ግባ” … “ዓለማየሁ” ሲል “ውጣ”፣ “ስንሻው” ሲል “ውጣ”፣ “ደምመላሽ” ሲል “ውጣ” … እያሉ ሲያስገቡና ሲያስወጡ የታዘበ አንድ “ተንኮለኛ” አማራ እውነተኛ ስሙን ትቶ “እኔሳ” ሲል “ግባ” አሉት እየተባለ በጨዋታ መልክ ሲወራ ሰምቻለሁ፡፡ ነገሩ እንዳልኳችሁ ጨዋታ ነው፡፡ ግን እሳት በሌለበት ጪስ የለምና ይህ ዓይነቱ የዘርና የቋንቋ ልዩነት አልነበረም ብሎ መካድ ከእውነት መራቅ ነው፡፡ ይህን ነገር ታዲያ ሙሉ በሙሉ በአማራ ላይ ብቻ ማላከክ ትልቅ ነውረኝነት ነው፡፡ ሁሉም ያደርገው ነበር፡፡ ሁሉም ተሰዳድቧል፤ ሁሉም ተፈቃቅሯል፤ ሁሉም ተጎሻምጧል፤ ሁሉም በጋብቻ ተሳስሯል፤ ሁሉም አማራ ሆኗል፤ ሁሉም ትግሬ ሆኗል፤ ሁሉም ኦሮሞ ሆኗል፤ በጥቅሉ ሁሉም ሁሉንም ሆኗል፡፡
የትኛው ከየትኛው ይበልጥ ተሰድቧል ወይም ተበድሏል ብሎ ለመፍረድ ደግሞ መሥፈሪያ ቁና ወይም መለኪያ ሚዛን ያስፈልጋል፡፡ ያን ለማድረግ ደግሞ አስፈላጊነቱ አይታየኝም፡፡ ወደፊት መሄድ እየተቻለ ጉድጓድ መቆፈርና ስላለፈ ታሪክ መነታረክ ለምን አስፈለገ? “በቅሎ አባትሽ ማነው” ስትባል “እናቴ ፈረስ ነች” ያለችውን መለሳዊ ያልተገናኝቶ መልስ እናስታውስና ይልቁናስ የሚያዋጣን ነገር ወደኋላ መሮጥ ሣይሆን ወደፊት መገስገስ ነው፡፡ በዱሮ ታሪክ ማላዘን ሥራ-ፈትነት ይመስለናል፡፡ ሥንፍናና ድንቁርናም ነው፡፡ ከዘመን ጋር ለመራመድ ያለመቻል የአስተሳሰብና የአመለካከት ደካማነትም ነው፡፡
ተስፋየ እንደትልቅ ችግር ያነሳውና እርሱ መፍትሔ እንደሰጠው የጠቀሰው በእስካሁን የኢትዮጵያ ልቦለዶች ውስጥ አንድም የኦሮሞ ገጸ ባሕርይ አለመኖሩ ነው፡፡ እዚህ ላይ ከማስገረምም አልፎ አስቆኛል፡፡ በቡርቃ ዝምታና በሌሎች የዐዞ ዕንባ አጉራፊ ድርሰቶቹ የፈጠረውን ክፍተት ይበልጥ ያሰፋ መስሎት ይህን ቢልም ለዚህ ድምዳሜ ያበቃውን የጥናት ውጤት ግን አልገለጸም፡፡ በብዙ ሺዎች የሚገመቱትን የኢትዮጵያ ልቦለዶች ሁሉንም አንብቦ እንዲህ ሊል እንደማይችል መቼም ግልጽ ነው፡፡ ደግሞም ደራሲያን የኦሮሞ ስም እንዳይጠቀሙ የከለከለ አንድም የቀድሞ መንግሥት አላውቅም፡፡ ይህ ወዘና የሌለው ጠብ-ጫሪ ሃሳቡ ብቻ ይህን ተስፋየ የሚባልን ጋኔን ለማውገዝና አክ እንትፍ ብሎ ለመጣል በቂ ነው፡፡
በዱሮ ጊዜ እኔም ነበርኩ፡፡ ስምን በሚመለከት ከመንግሥት ጋር ምንም ትስስር በሌለው ሁኔታ ኅብረተሰቡ ራሱ በልማድ የሚተገብረው የስም አወጣጥ ሂደት ነበር፡፡ የኔ የአክስቴ ልጅ ለምሣሌ ከአማራው አካባቢ ስትመጣ የነበራት እገሊት የሚባል ስም አዲስ አበባ ላይ ስለሚያስቅባት ለውጣለች – ትሠራ የነበረችውም ቡና ቤት ነው ፤ የብዙዎች አማሮች ሴቶች የመጨረሻ መዳረሻ ሴተኛ አዳሪነት ነበርና፡፡ ያኔ አማራ መሆን የተለዬ ጥቅም አያስገኝም ነበር፤ እኔ ራሴ የአማራ ዝርያ እንዳለብኝ የተረዳሁት ብዙ ዘግይቼ በ83ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ ቢሆንም የስም ለውጥን በተመለከተ እኔ ራሴ ከመጀመሪያ ስሜ አንዷን ሆሄ ከግዕዙ ወደ ራብዕ ፊደል በገዛ ሥልጣኔ ለውጫታለሁ – ዘመናዊ ለመባል፡፡ እነሸንተሞ፣ እነየዝና፣ እነጓንጉል፣ እነ አዝብጤ፣ እነአንጓች፣ እነጠጂቱ፣ እነወርቅያንጥፉ፣ እነግምብወግሽ፣ እነጉማታ፣ እነባንችይርጉ፣ እነታንጉት፣ እነጉዝጉዝ፣ እነጣፈጡ፣ እነማንጠግቦሽ … ስንቱን ጠቅሼው… እነዚህ አማሮች ሁሉ አዲስ አበባ ሲገቡ ስማቸውን ለመለወጥ ይገደዱ ነበር – “ዝናር ባንገቴ”ና “ዱቤ ክልክል ነው” የሚያስብልባቸውን የአንገትና የፊት ንቅሳታቸውን ለማጥፋት ስንቶች አማራ ሴቶች ገላቸውን በማስፈቅፈቅ መከራቸውን ያዩ ነበር፡፡
ስማቸውንና የፊት ገጽታቸውን እንደዘመኑ ማድረግ ካልቻሉ ደግሞ ከብት ባልዋለበት ኩበት ለመልቀም እየታከቱ የሚገኙት አዛኝ ቅቤ አንጓቾቹ እነተስፋየ እንደሚሉት መንግሥታዊ ተፅዕኖ ኖሮ ሣይሆን ማኅበረሰቡ ራሱ ስለሚስቅባቸው ክፉኛ ይሳቀቁ ነበር፡፡ መንግሥትማ እንዴት ስምን ቀይሩ ሊል ይችላል? ኦሮሞና አማራው አጤ ምኒልክ፣ ጉራጌ፣ አማራ፣ የመኑና… ኦሮሞው አጤ ኃይለ ሥላሴ፣ አማራና ኦሮሞው መንግሥቱ ኃ/ማርያም፣ ተጋሩ አኅዋትና ፍስሐ ደስታና ጄኔራል አማን አንዶም፣ … በምን ድፍረታቸው ዜጎችን ከዚህ ወደዚያ ወይም ከዚያ ወደዚህ ስማችሁን ቀይሩ ሊሉ ይችላሉ? አያ ጅቦ ሳታመካኝ ብላኝ ነው ነገሩ፡፡ ኤዲያ! ምን ዓይነት ጊዜ ላይ ደረስን ጎበዝ፡፡
ከዚህ መሠረታዊ ጭብጥ አንጻር የወለጋው ሰርቤሳ አዲስ አበባ ሲገባ ወይም የአርሲዋ ጫልቱ ናዝሬት ስትደርስ ኤርምያስና ሉሊት ብለው ስማቸውን ቢቀይሩ ተወቃሹ ማን ነው? ዕቁብ ያልበላን ሰው፣ ዕቁብ ስለመኖሩም የማያውቅን ሰው “የበላኸውን ዕቁብ ውለዳት!” ብለው በማይገባው ነገር ቢከሱትና ቢያደነቁሩት ምን ዋጋ አለው? ፍርድ ከራስ ነውና አማራ ያልሆናችሁ ሰዎች በተለይ ፍረዱኝ፡፡ የዚህን የተስፋየ ገብረባብ ሥውር ተልእኮ ደግሞ አስተውሉልኝ፡፡ ጊዜው የፈቀደው ፋሽን ሆኖ እንጂ ይህ የፈረደበት አማራ ያመጣው ፈሊጥ ሆኖ አልነበረም – አማራ እንደአማራ ሣይሆን በስሙ የነገዱና አሁንም ድረስ ሊነግዱበት የሚቋምጡ ጥቂት ቆሻሻ ዜጎች የሉም ለማለት እንዳልፈለግሁ ግን ተረዱልኝ፤ ክፋትና ደግነት በብሔረሰብና በብሔር የሚገደብ አይደለም፡፡ ደግነቱ “ሥራ ለሠሪው እሾ ላጣሪው” እንዲሉ ሁሉም ክፉዎች ዜጎች በጊዜያቸው የሥራቸውን ያገኛሉ – እንደመለስ ዜናዊና መሰል የከይሲው ልጆች፡፡ እነተስፋየ ተሟጋችና ተከላካይ የለውም ብለው በወደቀ ግንድ ላይ ምሣር ለመቀብቀብ ሌት ከቀን የሚተጉት ዘመናቸው የሰጣቸው ሰይጣናዊ ኃላፊነት በመሆኑ ሕዝብን መከፋፈልና ማበጣበጥ ከዚያም የተላኩበትን መሠሪ ተልእኮ ሲፈጽሙ ከሀገራችን ግልጽና ድብቅ ጠላቶች የሚሠፈርላቸውን ድርጎ መቀበል ዓይነተኛ ሙያቸው ስለሆነ ነው፡፡ እነዚህ አፈንጋጮች ፀሐያቸው መጥለቋ አይቀርም – የጊዜ ጉዳይ ነው፡፡ ደህና የነበርን ሰዎች ግን ከተስፋ መቁረጥ ተቆጥበን ታሪክ የሚያሳየንን ተዓምር በትግስት እንጠብቅ፡፡ ቀኑ ደርሷል፡፡ የነፃነትን መባቻ ቀን የሚያውቅ አንድዬ ብቻ ቢሆንም ቀኒቱ መቅረቧን የምንገነዘብባቸው ብዙ ምልክቶችን እያየን ነው፡፡
ሰማይ ክፉኛ ሲጠቋቁር፣ ደመናው ሲከብድ፣ ጭቆናውና እንግልቱ፣ ስደቱና ሰቆቃው ሲበረታ የቀኑን መቅረብ መገመት እንችላለን፡፡ የኢትዮጵያ ሰማይ ጭጋግ መልበስ ጀምሯል፡፡ ተራሮች ደም ቋጥረዋል፡፡ ሸለቆዎች አንዳች ነገር ሊያፈነዱ አቆብቁበዋል፡፡ ወንዞችና ሐይቆች አኩርፈዋል፡፡ … እንደቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ልበልና ልጨርስ – “የቆምን የሚመስለን ይበልጥ እንጠንቀቅ፤ የተቀመጠውን የሚያሳስበው መውደቅ የለምና፡፡” ለማንኛውም ልብ ይስጠን፡፡ እያለንም ሞተንም መኖር እንድንችል ለሚያደርገን አኩሪ ተግባር እንጂ እያለንም ሞተንም የሞት ሞት እንድንሞት ለሚያደርገን አስነዋሪ ድርጊት እንዳንጋለጥ ተግተን እንጸልይ፡፡ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ፡፡
yiheyiseaemro@gmail.com

Sonntag, 12. April 2015

የመን ለሚገኙ ወገኖቻችን እንድረስላቸው!

pg7-logoየመን የሚገኙ በመቶ ሺዎች የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን አደጋ ላይ ናቸው። ኢትዮጵያ ውስጥ ካለው የመብት አፈና፣ ሥራ አጥነት፣ ችጋርና ተስፋ ማጣት ለመሸሽ የራሳቸውንና የዘመዶቻቸውን ጥሪት አሟጠው ወደ መካከለኛው ምሥራቅ አገሮች ለሚሰደዱ ወገኖቻችን የመን መሸጋገሪያቸው ናት። ዛሬ የህወሓት ወዳጅ የሆኑም ያልሆኑም የየመን አምባገነን ገዢዎች እርስ በርሳቸው እየተላለቁ፤ ከምድር እሳት እየነደባት መሆኑ ሳያንስ ከሰማይም እሳት እየዘነበባት ነው።
እንኳን አሁንና በሰላሙም ጊዜ የመን ለኢትዮጵያዊያን ምቹ አልነበረችም። በበረሀ ጉዞ የዛሉ እግሮች፤ ከአቅማቸው በላይ በጫኑ ታንኳዎች ባህር በመሻገር የታወኩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች የመን ጠረፍ ላይ የሚጠብቃቸው ተጨማሪ እንግልት፣ ስቃይና መደፈር ነበር። የመን የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ሕይወት እኛ ኢትዮጵያዊያን እንደ አገር የደረስበት አሳፋሪ ደረጃ መገለጫ ሆኖ ቆይቷል። በየመን፣ ወገኖቻችን ተደብድበዋል፤ አካላቸው በስለት ተዘልዝሏል፤ ሴቶች ብቻ ሳይሆን ወንዶችም ተደፍረዋል፤ ጓዳችን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ታፍኖ ለህወሓት ተላልፎ ተሰጥቶብናል። አሁን የመን እየነደደች ነው።
እጅግ የሚያሳስበን ቁጥራቸው ከመቶ ሺህ ይበልጣሉ ተብሎ የሚታሰበው በአሁኑ ሰዓት የመን ውስጥ የሚገኙ ወገኖቻችን እጣ ፈንታ ነው። የሌሎች አገሮች ዜጎች መንግሥቶቻቸው ደርሰውላቸው ከእቶኑ አውጥተዋቸዋለሁ። የኛ ወገኖች ግን የሚደርስላቸው መንግሥት የላቸውም።
ወገኖቻችን በዚህ ጭንቅ ውስጥ ባሉበት ሰዓት የህወሓት አገዛዝ ያንዣበበባቸው አደጋ የሚያባብሱ ተግባራትን እየወሰደ ነው። ሌሎች አገሮች በየመን ጉዳይ ላይ ያላቸውን አቋም በይፋ ከማሳወቃቸው በፊት ዜጎቻቸውን አስወጥተዋል። ህወሓት ግን ወገኖቻችን ለማዳን አንዳችም ጥረት ሳያደረግ ኃላፊነት በጎደለው መንገድ አንዱን ተፋላሚ ወገን በይፋ በመደገፍ በመቶ ሺህ የሚገመቱ ወገኖቻችን ከወላፈኑ ወደ እቶኑ ወርዉሯቸዋል። ገንዘብ የሚያገኝበት ከሆነ ወያኔ ወታደር ከመላክም ወደ ኋላ አይልም። እናም ለወገኖቻችን ካለ እኛ ማን አላቸው?
ስለ የመን ብቻ ሳይሆን ስለ ስደተኝነት በተነሳ ቁጥር አዕምሮዓችን ውስጥ የሚጉላላ ቁም ነገር አለ። እኛ ኢትዮጵያዊያን አገራችን ውስጥ ያለውን ሥርዓት ለውጠን፤ በምንወዳት አገራችን ውስጥ በክብር እንደመኖር እስመቼ አገራችንን ለህወሓት ወንበዴዎች ትተን እየሸሸን እንኖራለን? ስቃይና ሞት ተሸሽቶም አልተመለጠም። ሞት ኢትዮጵያዊያንን ኬንያ፣ ዩጋንዳ፣ ሱዳን፣ ሰሀራ በረሃ፣ ሜዴትራኒያን ባህር፣ ቀይ ባህር፣ ሳውዲ አረቢያ እና የመን ውስጥ መሽጎ ይጠብቀናል። ኢትዮጵያዊያን በስደት ላይ እያለን የከፈልነው ዋጋ ተጠራቅሞ በአገራችን ውስጥ ለሥርዓት ለውጥ ውሎ ቢሆን ኖሮ ወያኔ አስወግደን በውሸት ሳይሆን በእውነት የበለፀገች ኢትዮጵያን መገንባት አንችልም ነበርን? እውን ወያኔ ከስልጣን ማስወገድ በስደት ምክንያት ያጣነውን ያህል ነብስና በስደት ላይ እየተቀበልነው ያለ ፍዳ ያህል ያስከፍላልን? ለምን በሀገራችንና በራሳችን ላይ እምነት አጣን? ይህ አፋጣኝ እርምት የሚሻ አብይ ጉዳይ ነው።
አርበኞች ግንቦት 7:የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ የመን ለሚገኙ ወገኖቻችን ለመድረስ የተቻለንን ሁሉ እንድናደርግ ጥሪ ያደርጋል። ይህ ሥራ እየተሠራም ትኩረታችን ለዚህ ሁሉ መከራ የዳረገንን የህወሓት አምባገነን አገዛዝን ለማስወገድ በርትተን እንታገል ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

ትራንስፎርሜሽን ወይንስ.......? ገብረጻዲቅ አበራ

የሃሳብ መንገድ
ትራንስፎርሜሽን ወይንስ.......?
https://www.facebook.com/video.php?v=1591837571056663&video_source=pages_finch_main_video
ዛሬ በኢትዮጵያችን ዘወትር የሚታየውን ትተን ከወዳጅ ዘመዶቻችን የምንሰማውንም ችላ ብለን የመንግስት ባለስልጣናት የሚነግሩንን መስማትና በመንግስት ሚድያዎች ስር መጣድ ላስቻለው ገነትን ከመጨበጥ በመመለስ ኢትዮጵያ ሁሉ ነገር ሞ ልቶ የተረፈባት የጎደላትም ባጭር ግዜ ውስጥ መስመር የሚይዝላት የሚሳሳላትና ብዙዎች የሚጎመዧት ሃገር እየሆነች ነው። ኢትዮጵያ ኑሮ ን ለማሸነፍ ባህር እያቋረጡ የሚሰጥሙበት በበረሃ ንዳድ የሚያልቁበት የጨለማ ዘመን እየተሻረ የጎረቤት ሃገር ሰዎች የሚፈልሱባት ጥቂት አመት ከጨመርን ደግሞ አሜሪካዊያን እና አውሮፓውያን የ ኢትዮጵያን ቪዛ ለማግኘት ደጅ የሚጠኑበት ግኔ በጣም እየቀረበ መምጣቱን እንረዳለን ። በመንግስትና በገዢው ፓርቲ ሚድያዎች ስር አስችሎን ከተጣድን። አሁንም ቢሆን ሃገር ጥለው የሚወጡት ስልጣን ቀረብን የሚሉ ጥቂቶች እንዲሁም ኢትዮጵያ ውስጥ ሰርቶ ከማግኘት ይልቅ ሳውዲ አ=ረብያ ውስጥ ሜዳላይ የሚረጨውን ሪያል ተኝተው ለማፈስና ደቡብ አፍሪካ ማሳላይ የተዘራውን ራንድ እያጨዱ ያለስራ ተንደላቀው ለመኖር የመረጡ ሰነፎች እንጂ ለሚሰራባት ኢትዮጵያ ባይነት ባይነቱ ስራ ሞ ልቶ የተረፈባት ብር የምታፈስባት ሃገር እየሆነች ነው። ብርታት ሰቶት መንግስት ሚድያ ስር ለተጣደ።
በረሃብና በችግር ብዛት ህሊናቸው ያልተነካባቸው ባይበሉም በቁንጣን የሚወጠሩ ጥቂቶችን እያዩ አቡጀዲ ቢቸግራቸውም በወርቅ የሚንቆጠቆጡትን እየገረመሙ ያቺ ኢትዮጵያ እነሱ የቆሙበትን የተወችውና ሃገራዊ .... አድርጋ የጥቂት ሺዎች ብቻ የሆነችው መቼ ነው ብለው እየጠየቁ ከረሃቡ በላይ የሚያመው ፕሮ ፖጋንዳ የውስጥ አካላቸው እየተጎዳ እንደሆነ መገመት አያስቸግርም ። በሌላም በኩል የድንቁርና ክፋቱ የዘረኝነት ብርታቱ ከሚታየው በላይ የሚሰማው እውነት ሆኖ ስለሚገለጥ እየተራቡ በቁንጣን የሚወጠሩ እየታረዙ በወርቅ የሚሽቆጠቆጡ ጥቂቶች አይደሉም። ጠኔ እያንጠራወዛቸው በአለማስተዋል የሚነገራቸውን አምነው አሜሪካኖች ኢትዮጵያ ለመግባት ጓጉተው ቪዛ የሚጠይቁበት ግዜ ሲመጣ የሚኖሩት የተደንላቀቀ ህይወት እየታያቸው በተስፋ ፍራሽ ላይ የሚንከባለሉ የሉም ብሎ የሚያምን ካለ አንብበው ያልተገለጠላቸው ብዙዎች ካጠገቡ ቃኝተው ሳያነቡ የተከደነባቸውን መገመት ይችላል። ድሃ በህልሙ ቅቤ ባይጠጣ ንጣት ይገድለው ነበር የሚለው ብሂል ለዚህ የሚስማማ ቢመስልም ይሄ ግን ከህልም ይልቅ የለየለት ቅዠት መሆኑ ደግሞ ሊሰመርበት ይገባል። በጨለማው ዘመን ለጨለማው መሃበርተኞች የዘረኝነትና የድንቁርና ጉዞ በብርሃን አሻግረው የሚያልሙ እነርሱ ድህነትን ብቻ ሳይሆን አለማስተዋልን የደረቡ ከሰው ተርታ ብዙ እርቀት ላይ የሚገኙ ናቸው ለማለት ያስደፍራል። እርግጥ ነው ጨለማው በብረሃን እንደሚረታ የጨለማው መሃበርተኞች በብረሃን መልእክተኞች እንደሚሻሩ ምልክቶችን አይተው በየ አቅማቸው የዘረኝነትና የድንቁርናን ቀንበር እንዲሰበር የሚሰሩና ሚመኙ ዋሻው ጫፍ ላይ እንደሚታየው ብረሃን እየተጓዙ ስለሆነ እነርሱም በተስፋዎች ውስጥ ስለመሆናቸው እውነት ነውና ተስፋ ሁሉ ግን መሬት የረገጠ ምኞት ደሞ ጤዛ እንዳልሆነም ሊሰመርበት ይገባል።
የዛሬ አምስት አመት አይተን በጠገብነው ቲያትር ሰምተን በጠገብነው ጫጫታ ወንበራቸውን ለ አምስት አመታት በነፍጥ ተመክተው ..... የአምስት አመታት ትራንስፎርሜችን እቅድ ብለው ግርግር ፈጠሩ። በዚህም ሃገሪቱ በሁሉም መስክ በአምስት አመት ግዜ ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ መነሳት እንደምትጀምር መንገዱ ሃዲዱ ፋብሪካው ሁሉ ደጃፍ እንደሚደርስ ተለፈፈ። የአፍሪካ ሃገራትን ጥለን በሱፐር ሶል ጀቶች ፍጥነት አየሩን ቀዝፈን መካከለኛ ገቢ ወዳላቸው ሃገራት መወንጨፍ እንደምንጀምር ለወራት ተነገረን ለአመታትም ቀጠለ ። በኪነጥበብ ባለሙያዎች አማካኝነት በሙዚቃ ድራማም ተገለጸልን። አምስት አመቱ ሲቃረብ ቢቀዘቅዝም። በነፍስ ወከፍ ገቢ በጣም እንደምንነሳ ብዙ ቢነገርም የሞላላቸው ወደ መቶሺ ዶላር ሲቆጥሩ እኛ አንድ ሺ ዶላር አቀበት ሆኖብን አምስት መቶ እንኳን መጠጋት አቅቶናል። አሁንም ከአለም ጠርዝ ቁጭ ብለን በወሬ ግን ከሁሉም በላይ መንሳፈፉን ቀጥለናል። የተግባር አቻዎቻችን እንደኛው ለነፍስ ወከፍ ገቢ ሶስት መቶ ዶላሮች ውስጥ የሚዳክሩት ብሩንዲ ላይቤርያ ኒጀር እና ኮንጎ መሆናቸው ቀርቶ ከመቶ ሾሺ በላይ የነፍስ ወከፍ ገቢ ከሚያስመዘግቡት ከነሞናኮ ሉክሰንበርግ ወዘተ ወደ ሰማንያ ሺ ዶላር ከተጠጉ ኖርዌይ ስዊድን በላይ ህዝቡን በታጠፈ አንጀቱ ሊያንጠራሩት ይዳክራሉ።
ወደ አምስት አመቱ የትራንስፎርሜሽን እቅድ እንመለስ።
የባእዳንን ኪስ ተማምነው ሃገሪቱን በወለድ አግድ አሲይዘው በሚገኝ ብድር እና መዋእለ ንዋይ ለመስራት ቃል የገቡትን ወደ ተግባር ለመለወጥ የተቸገሩት በአንድ በኩል ብድሩ በተባለው ፍጥነት እና መጠን አለመገኘቱን በሌላም በኩል የአቅም ውስኑነት እንዲሁም አበዳሪዎቹንና የብርዱ ሁኔታ አለመገምገም ከምንም በላይ ከግዙፍ ፕሮጀክቶች ጀርባ የህወሃት መሪዎች ለኤፈርት እና ለግላቸው በሚያተርፈው ጉዳይ ላይ ይበልጥ ማተኮራቸው የውጪ ምንዛሬውን የማሸሽ ሂደት ላይ በመጠመዳቸው ኢትዮጵያ በጋራ በሚያመጡ ልጆቻቸው ስም ጭምር የተወሰደው ብድር እዳውን እንጂ ውጤቱን ማየት አልቻሉም። የህዳሴን ግድብ ጨምሮ በመቋቋም ላይ ባሉ ሰባት ግዙፍ የስኳር ፋብሪካዎች እና ለሌሎችም ሲሚንቶና ብረታብረት በማቅረብና መንገድ በመጥረግ የህወሃቱ ኤፈርት ኩባንያዎች መሶቦ መስፍን ኢንጅረሪንግ እና ሱር ኮ ንስትራክሽን በሃገሪቱና በህዝቧ ስም በብድር ከሚመጣው የውጭ ምንዛሬ ከፍተኛ ሃብት እያፈሱ ሲሆን የህወሃት በግለሰብም ሆነ በቡድን ተጠቃሚ በማድረግ ሃገሪቱን የ ኢኮኖሚ የበላይነት አስተማማኝ አድርገው ለመጥረግ በመወሰናቸው በስኳር ኮርፖሬሽኖቹም በድምር በድልደላ ወዘተ ከውጪ ብድር እና ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚታፈሰውን ገንዘብ የሚቀራመቱት ያለጨረታና ውድድር መንገዱ የተለቀቀላቸው የህወሃት መሪዎች የመንደር ልጆች ናቸው። ባጭሩ የትግራይ ተወላጆች ብለን ልናልፋቸው እንችላለን።
በኢትዮጵያ ውስጥ በንጉሱ ግዜ ጀምሮ መገንባት የጀመሩትን አራቱን የስኳር ፋብሪካዎች ደረጃቸውን ከፍ በማድረግ እንዲሁም ተጨማሪ ሰባት ግዙፍ ፋብሪካዎችን በመገንባት ሁሉንም እስከ 2007 ዓ.ም አጠናቀን ስኳር ወደውጪ በመላክ በቢልየን የሚቆጠር የውጪ ምንዛሬ እናገኛለን የተባው አንዱ ባይፈጸምም የህወሃት ኩባንያዎችና የህወሃት ሰዎች ሃብት እያፈሱ መሆናቸው ግን ግልጽ ነው።ለነዚህ ፕሮጄክቶች ከውጪ ብድር ከተገኘው ገንዘብ ባሻገር የኢትዮጵያ ህዝብ ንብረት ከሆነው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሃያ ቢሊየን ብር በላይ መወሰዱንም የባንኩ ምንጮች ይጠቅሳሉ። በለሳ አንድና በለሳ ሁለት እንዲሁም ኩራዝ አንድ ኩራዝ ሁለት ኩራዝ ሶስት እና ኩራዝ አራት እንዲሁም ወልቃይት እና ከሰም ስኳር ፋብሪካዎች ከ2006 በፊት ተጠናቀው ስራ እንደሚጀምሩ እና ኩራዝ አምስት ደሞ በዚህ አመት ተጠናቆ ወደገበያው እንደሚገባ የተነገረ ቢሆንም
አንዱም አልተሳካም። ለኢትዮጵያዊያን የሚያስፈልገውን አመታዊ የስኳር ፍጆታ ስድስት ነጥም አምስት ሚሊዬን ኩንታል ገደማ ግማሽ እንኳን ማሟላት አሁንም ባለመቻሉ በውጪ ምንዛሬ ስኳር ማስገባቱ ም ቀጥሏል። በአለማችን በነፍስወከፍ የስኳር ፍጆታ ኢትዮጵያችን/ ግርግዎስ/ ስገልጽ በሽታ ቀረብን የሚል የድንቁርና መከራከሪያ እንደሚኖር ታሳቢ በማድረግ ጭምር ነው።
በመንግስት የአምስት አመቱ የትራንስፎርሜሽን እቅድ ውስጥ ከተያዙት ሰባት የስኳር ፋብሪካ ፕሮጀክቶች ብድሩ ከውጪም ከሃገር ቤትም ከውጪም እየፈሰሰ ለፍጻሜ ባይደርሱም የህወሃት መሪዎች ከአምስት አመቱ የትራንስፎርሜሽን እቅድ በፊት የተጀመረውን እና የመንግስት ያልነበረውን ፕሮጀክት ከሰሞኑ በማስመረቅ ለምርጫው እየተሟሟቁ ይገኛሉ። ከሰባት አመት በፊት ወለጋ ውስጥ በፓኪስታናዊ ባለሃብት የተመሰረተው አርጆ ደዴሳ የስኳር ፋብሪካ የኩባንያው ባለቤት ከሶስት አመታት በፊት በመኪና አደጋ ሲሞቱ ግንባታው ዘጠና በመቶ የተጠናቀቀ ሲሆን ከሰውዬው ሞት በኋላ ፋብሪካው ወደ መንግስት በመዞሩ ቀሪው አስር በመቶ ባለፉት ሰስት አመታትአልቆ ለምረቃ ተዘጋጅቷል። ያቀዱት ባይሳካም ያላቀዱትን ያስረከቧቸውን የሟቹን ፓኪስታናዊ ሞሻህንጀን ነፍስ በገነት ወይም በጀነት ያቆይልን እያሉ ጫጫታ መፍጠሩ አይከፋም።
ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊያንን በጠመንጃ አግቶ ለሃያአራት አመታት በስልጣን ላይ የቆየው ይሄ ቡድም የአምስት አመቱ የትራንስፎርሜሽኑ እቅድ ባይሳካም አበዳሪዎቹም የተሸከማችሁት ብድር ከአቅማቹ በላይ ነው ብለው ብድር መስጠት ባቆሙበት በጨበጣ ሌላ የአምስት አመት የትራንስፎርሜሽን ዶሴ ሲጠርዙ ተዘጋጅቷል። እስከዚያ ለሟሟቂያ ምንም በሌለበት ነዳጅ መገኘቱን የተፈጥሮ ጋዝ የሃገሪቱን ከርሰምድር ማጨናነቁን ነግረውናል። ወሬው በደንብ ሳይብላላ የጋዝ መተላለፊያ ትቦ ተዘረጋ ብለው ፎቶግራፍ ለጠፉ። ጉዳዩ ሲመረመርም ፎቶው የተወሰደው ከሩስያ ወደ ዩ ክሬን ከተዘረጋው የጋዝ ቱቦ መሆኑን ተደረሰበት። ይባስ ብለው ተናበው ስለማይዋሹ እንኳን ጋዝ ሊገኝ ጋዝ የሚፈልገው ኩባንያዎች ስራ አለመግባታቸው ወይም አለመጀመራቸው በሌላ የመንግስት ባለስልጣናት አንደበት የተጋለጠበትንም ሁኔታ ታዝበናል። የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ መሪዎች ሁሌም የሚሰሙት ራሳቸውን ነው የሚያነቡትም ለነሱ ባለራእይ ለኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን ዘረኛና ማጣቀሻ የሆኑትን መለስ ዜናዊንና ፍልስፍናቸውን በመሆኑ ፍላጎትና ድርጊታቸው በራሳቸው ምህዋር ውስጥ ብቻ እንዲቀዝፉ አድርጓቸዋል። ሃገር ከተመለመሉ ደካሞችን ዲግሪ ገዝቶ በማደል?? አይገነባም። በመንደራቸው ፍቅር የተተበተቡና በኢትዮጵያዊነት ጭምብል ራሳቸውን ሸሽገው ዘረኝነትን በተከናነቡ የጎጥ ማህበርተኞች ሃገራይራይ ኢትዮጵያዊም አይከሰትም።ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊያንን የዘውድ ማስመለሻ መፎካከሪያ ሜዳ አድርገው ተፎካካሪው ልቆ በሄደበትና ሃያአንደኛው ክፍለዘመን ውስጥ በገባበት እነርሱ አስራዘጠነኛው ክፍለዘመን መጨረሻ ላይ ቆመው በቂም ፖለቲካ ተበክለው በጥላቻ በገነቡት ስረአት በደካሞች ተደግፈው ትራንስፎርሜሽ እያሉ ያላዝናሉ። በቂምና በጥላቻ በዛላይም ድንቁርና ተጨምሮ ስታግኔሽን እንጂ ትራንስፎርሜሽን አይኖርም።
ከቻይና የተገኘውን ጨምሮ ከሃያ ቢሊዮን ዶላር በላይ ብድር ከአርባ ቢሊየን ዶላር በላይ እርዳታ ያገኘ መንግስት ለማያዩ ብዙ እየሰራ ቢሆንም አይናቸው ለተገለጠ የሚከሰተው የዘረፋው ፍሰት ነው ። ስልሳ ቢሊየን ዶላር ማለት ግዙፉን የህዳሴ ግድብ አስር ገንብቶ ስኳር ፋብሪካዎቹ ለህንጻ እና ለመንገድ የሚተርፍ ከፍተኛ ገንዘብ ማለት ነው። ይህ ገንዘብ ለ እርሻና ለተለያዩ የንግድ እንቅስቃሴዎች ወደሃገር ቤት ገብተው ለመሬትና ለመሳሰሉት የሚከፍሉት የውጪ ምንዛሬ እንዲሁም አጠቃላይ ሃገራዊ ምርትን በውጪ ሃገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊ የሚልኩትን የውጪ ምንዛሬን አይጨምርም። አለመታደል ሆኖ አለማቀፉ ሁሌታ ፈቅዶ ለእድገትና ለብልጽግና መንገዱ የተከፈተበት ለግሎ ባላይዜሽን ዘመን መንደርተኞች እጅ ወድቀን በወሬ እየፋፋን በተግባር እየቀጨጭን ድህነትና ረሃብ በከተሞች ጭምር ተንሰራፍቷል። በወሬ ፊት ፊቱን እየተጣደፍን በተግባር ሃገራት ግርጌ ተቀምጠን በሁሉም መስክ ስርስሩን አጥብቀን ይዘናል።
አዎ ን እነዚህን መገላገል ከዘረኝነት የምንፈወስበት ከድንቁርና የምንፋታበት ብቻ ሳይሆን በርግጥ የምንለማበት ጭምር በመሆኑ በርግጥ ወስነው በረሃ የሚንከራተቱትን መንገድ ሲጀምሩ ስንቅ ማቀበል ይቻላል እና ተዘጋጅተን እንጠብቃቸው። ገብረጻዲቅ አበራ

በስለላ ከሆላንድ የተባረረው የጋዜጠኛውን አንገት እቆርጣለሁ አለ

ክንፉ አሰፋ
እለተ እሁድ ከቀትር በሁዋላ አንድ የስልክ ጥሪ ደረሰኝ። ቁጥሩ +251 945226530 ነበር። ስልኩን አነሳሁት።
“ሃሎ”
“አቤት”
“አለማየሁ ነኝ። መን አባክ ነው የምትጽፈው። እኔ አላማዬ ነው። አንተን ግን አንገትህን ቆርጬ ነው የማሳይህ። ለማየት ያብቃህ። ያን የምትጽፈውን ጽሁፍ… እኔ ምንም ልሁን ምን እንደዚህ አይደለሁም። እሺ። እናትክን…(ይህንን ጸያፍ ቃል በድምጽ ስሙት)። … ደግሞ ኢህአዴግ ዘርህን… (ይህንንም ጸያፍ ቃል በድምጽ ስሙት)
TPLF spy in Netherlands
ከሆላንድ የተባረረው የወያኔ ሰላይ አለማየሁ ስንታየሁ(ሀለቀ ፎላ)
ይህ ጸያፍ ዘለፋ እና ማስፈራርያ እንግዲህ ወያኔ ምን ያህል እንደወረደ ያሳየናል። ከነውረኛ ስድቡ ባሻገር ደግሞ ቀላል የማይባል ድንበር ዘለል ሽብር ነው። ለዚህ ሽብር ተጠያቂ የሚሆነውም ተላላኪውና ሆድ አደሩ ብቻ ሳይሆን ላኪውም ጭምር ነው። ህወሃትን በመጠለል ልክ እንደ ISIS አንገትህን እቆርጥልሃለው ሲል መናገሩ መንግሥታዊ አሸባሪነት ለለመሆኑ ግልጽ ነው። ለዚህ ሰው ሲከራከር የነበረው ተሾመ ቶጋም ይህንን ሰምቶ ዝም የሚል ከሆነ የወንጀሉ ተባባሪ ይሆናል።
በዚህ አይነት ማስፈራራት አላማቸውን ማስፈጸም ካሰቡ ግን በጣም ተሳስተዋል። እንዲህ አይነቱ ነገር የበለጠ እልህ ውስጥ ያስገቡናል እንጂ በስራችን ላይ ቅንጣት ያህል ተጽእኖ ሊፈጥሩ አይችሉም። እንደጋዜጠኛ ለመስራት ስንነሳ ፍርሃትን ከእትብታችን ጋር ቀብረነው ነውና ይህንን የምትሞክሩ ተስፋ ቁረጡ ነው የምንላችሁ።
ይህ ሰው ከሆላንድ የመኖርያ ፈቃዱ ተነጥቆ ወደ ኢትዮጵያ እንደተመለሰ በተለያዩ የዜና አውታሮች መዘገቡ ይታወሳል። ስለዚህ ሰው ጉዳይ ተሾመ ቶጋ (የወያኔ አምባሳደር) ከብራስልስ ማስተባበያ ሰጥቶ ነበር። ማስተባበያው ባጭሩ፣ “አለማየሁ ስንታየሁ ሰላይ አልነበረም። ከሆላንድም አልተባረረም። የተሰደደውም ከኢሃዴግ ዘመን በፊት ነው። … ይህ ደጋፊዎቻችንን ለማሸማቀቅ በአሸባሪ የተፈረጁ ሰዎች የሚያወሩት ወሬ ነው።” ይላል።
የሶስት ልህጆች አባት የነበረው አለማየሁ (ዘለቀ ፖላ) የሆላንድ የመኖርያ ፈቃዱን እና መኖርያ ቤቱን ተቀምቶ ከሄደ ሶስት ወራት አልፈዋል። ጉዳዩን ከሚመለከተው ክፍል በማጣራት የዜናውን እውነተኝነት አረጋግጠናል።
ዜናው በውጭ ያሉ የስርዓቱ ደጋፊዎችን በእጅጉ ያስደነገጠ በመሆኑ የተሾመ ቶጋ ማስተባበል የግድ ነበር። ውሸት ነው ማለታቸውም አይደንቅም። እውነት ተናግረው ሰምተናቸው ስለማናውቅ። አለማየሁ ስንታየሁ ችግር እንደነበረበት እና አስፈላጊውን ደብዳቤ ከኤምባሲው ተቅብሎ ወደ ኢትዮጵያ መሄዱን አቶ ተሾመ በቃለ-ምልልሱ አልሸሸጉም።
የተሾመ ቶጋን ውሸት ከሰማሁ በኋላ ጉዳዩን ለማጣራት የሚመለከታቸው የሆላንድ መንግስት አካላትን አነጋግሬአለሁ። ሶስት ክሶች ተመስርተውበት ነበር። አንደኛው ከወያኔ ካድሬዎች ጋር በመመሳጠር አንድ ኢትዮጵያዊ ባለሃብትን እንዲታፈን በማድረጉ፤ ሁለተኛው ክስ የአሱን ስም በማጭበርበር እና፤ ሶስተኛ የሆላንድ መንግስትን ዋሽቶ የስደት ፈቃድ ከገኘ በህዋላ ለገዢው ፓርቲ ይሰልላል የሚሉ ነቸው።
ጭንቀት ውስጥ በነበረ ጊዜ ከአንዴም ሁለቴ ደውሎ በጉዳዩ ላይ አነጋግሮኛል። ከሚኖርበት አካባቢ እንዳይርቅ በሆላንድ መንግስት ታግዶ በነበረበት ወቅትም ከመገኛኛ ብዙሃን፤ በተለይ ከጀርመን እና ከአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ ጋር እንዳገናኘው ጠይቆኝ ነበር።
ይህ ሰው ወደ ሆላንድ የገባው በ1994 (ወያኔ ስልጣን ከያዘ ከአንድ አመት በህዋላ) በሰላም ተጓዥ ስም ነበር። ከዚያ ለበርካታ አመታት በስውር ከዚያም በግልጽ ለወያኔ ሲሰራ ነበር።
ጋዜጠኛ አፈወርቅ አገደው በፌስቡክ ገጹ ላይ ስለዚህ ሰው እንዲህ ሲል አስነብቦናል። “ይህን ግለሰብ በአካል አውቀወለሁ። ብዙ የቅርብ ጓደኞቼም ስለሚሠራቸው የስለላ ሥራዎቹ ያውቃሉ። ከራሱ አፍ እንደሰማሁት ትክክለኛ ስሙ ዘለቀ ፖላ ነው። እዚህ ስደት የጠየቀበት ስሙ ዓለማየሁ ስንተሰየሁ ነው። የወላይታ አካባቢ ተወላጅ ነው። ተቃዋሚ መስሎ ለህወሓት ኤምባሲ ብዙ የስለላ መረጃዎችን የወያኔ ተቃወሚዎችን በሚመለከት እንደሚያቀብል ይታወቃል። … አንዳንዴ ስብሰባዎቹ ሌሎችን በሚያገልል መልኩ በትግርኛ ሲደረግ ዘለቀ ፖላ ይሳተፋል። ምኑ ገብቶህ ነው በማታውቀው ቋንቋ የምትሳተፈው ስንለው ጆሮዬ ክፉ ክፉውን ስለሚሰማ ለእናንተ ወሬ ለማቀበል ነው ይል ነበር።”

Freitag, 10. April 2015

የህወሕት ትግሬ ወጣቶች የሚሰሩት ድብቅ ስራና ሴራ።

አማራ ወጣቶች የጋራ ንቅናቄ

በአንድ ወቅት በአይቲ (ICT) ኢንፎርሜሽን ቴክኖሌጅ ሳይንስ የትምህርት ክፍል ስልጠና ወደ ቻይና ከተላኩ ሁለት መቶ (200) ኢትዮጵያዊያን አንድ መቶ ዘጠና ስምንቱ (198) ትግሪወች ሁነው ተገኝተዋል።ጆሮ ለሰሚው ባዳ ነው አንድ ከአማራ አንድ ከኦሮሞ ሁለቶችን ለምልክት አስቀምጠዋቸዋል ።ኢትዮጵያ የብሔሮች እናት ቅብጥሴ ገለመሌ የሚባለው ለዚህ ነው ?ትግሬ የብሔሮች ክፉ የእንጀራ እናት ቢሆን የሚጠጋጋ ይመስለኛል ።

ትግራዊያን ከቻይናው ስልጠና ከተመለሱ በኋላ ስልክን ፣ፊስቡክን የተለያዩ ወብሳይቶችን በመጥለፍ (ሀክ) በማድረግ መሰማራታቸውን ጽሀይ የሞቀው አገር ያወቀው ሀቅ ሁኗል። በተጨማሪ በእያንዳንዱ ክፍለ ሀገር ቴሌኮሚኒኬሽን ተቋማ ባለበት ከተማ ውስጥ በሀላፊነት ተቀምጠው ስልክን ጠልፎ በመሰለል ስራ ተጠምደዋል ።

አሁን ደግሞ በተለየ ሁኔታ ፊስቡክ ሚዲያ ላይ በመሰግሰግ እልፍ አላፋ ዘመን አብሮ የኖረን ህዝብ ለማጣላት እና መልካም ግንኙነቱን ለማቃቃር ኦሮሞ ከአገራችን ይውጣ፣አማራ ከአገራችን ይውጣ፣ጉራጌ ከአገራችን ይውጣ አፋር ከአገራችን ይውጣ ወዘተረፈ እያሉ በመሰሪ አቋማቸው ለጸብ እና ለብጥብጥ ዋና ምክንያቶች ሁነዋል። ኦሮሞ ኢትዮጵያዊ ካልሆነ ፣አማራ ኢትዮጵያዊ ካልሆነ ፣ጉራጌ ኢትዮጵያዊ ካልሆነ ሁሉም ከአገር ከወጡ ማን ኢትዮጵይልዊ ሊሆን እንደሚችል ሊገባን አልቻለም ።

የወንበዴ ህወሕት ትግሬወችን ቅማላቸውን አራግፎ ሲርባቸው አብልቶ፣ሲጠማቸው አጠጥቶ፣ችግር ሲደርስባቸው ደብቆ የጎንደር ህዝብ አይደለም ሀላፊነቱን ያዙት ከደርግ የማይሻል የለም ብለው አዲስአበባ አራት ኪሎ ቤተ መንግስት ያስገባቸው???

ጅብ እስኪናከስ ያነክስ ነውና ነገሩ ዛሬ አማራውን የሌለው ህዝብ ጠላት ቅኝ ገዥ አድርጎ በመሳል የየዋሁን ህዝብ መልካም ግንኙነት በካፋ ደረጃ አቃቅሮታል ።

ዛሬ ዛሬ ደግሞ በህወሕት ትግሬ ወጣት ምልምሎች በፊስቡክ ሚዲያ ብቅ አድርገዋቸዋል ፣እውነት እና ንጋት እየቆየ ይጠራል እንዲሉ ለጊዜው በአሸናፊነት ስሜት ፈረስ ላይ ሁነው ቢጋልቡም ቅሉ ጊዜውን ጠብቆ ወደ ነበረበት መመለሱ አይቀሬ ነው ።

በአሁነ ስዓት ደግሞ አማራ በመምሰል በአጸያፊ ስድብ ኦሮሞን መሳደብ ፣ኦሮሞ በመምስል በአጸያፊ ስድብ አማራን መሳደብ ዘመቻ ስለወጡ የተከበርህ የኢትዮጵያ ወጣት ሆይ ይህን መሰሪ አቋም የማወቅ ግዴታ አለብህ እላለሁ ፣ከለዚያ ግን በእልህ ጎደና ተያይዘን መውደቃችን ነው እና ከተኛህበት የርኩስ መንፈስ ውስጥ ንቃ ንቃ ንቃ!!!!!!!!!

Mittwoch, 8. April 2015

በየመን ጦርነት ማጥ ውስጥ ያሉ ወገኖቻችን አበሳ ! – ነቢዩ ሲራክ

* ኢትዮጵያውያን ማን ይታደጋቸው ?
* ከቀሩት የውጭ ዜጎች ምን እንማር ይሆን ?
* ለነፍስ አድኑ ጥሪ የእኛ አማረጭ ምን ይሆን ?
በአረቡ ሀገር ስደት ማጥ ውስጥ የገባውን ወገን ስጋት እያደር ከስጋት አልወጣም ። ሳውዲን መዳረሻ ያደረጉ የመንን በአሳር በመከራ አልፈው በወደብ ከተማዋ ጅዳ እግራቸው ሲረግጥ በጨካኝ ደካሎችና አሸጋጋሪዎች ታግተው የድረሱልኝ ጥሪ ሲያሰሙ ደራሽ አጥተዋል። በህጋዊ የኮንትራት ስራ የመጡትም ሆኑ ህጋዊ መኖርያ ፈቃድ ይዘው ኑሮን በመግፋት ላይ ያሉ ሳይቀሩ በዙሪያቸው ባለው በሚደርስባቸው ፣ በሚያዩ በሚሰሙት እንደኔ ታመዋል ። አረቦች በደሉን ከሚባለው በላይ የራሳችን ወገኖች ደመ ነብሱን ከሚንቀሳቀሰው ያልሞላለት ግፉዕ እስከሞተው በድን ሳይራሩ ፈጣሪ ያየናል ብለው ሳይፈሩ በንዋይ ፍቅር ታውረው ግፍ እየሰሩ ነው ። ሰብዕናቸውን አሽንቀንጥረው ርቀው ሄደው የሚፈጽሙት አስነዋሪ ተግባር የጊዜውን መክፋት ያሳይ እንደሁ እንጃ … እኔም እኛም ሁላችንም ግን ችግሩን እናወራዋለን እንጅ መፍትሔ የለንም ! የየመኑን የጦርነት ግብአት ከመከታተል ጎን ለጎን ሰሞነኛ ውሎየ ያሳየኝ እውነታ ይህንኑ እውነት ነው …
People gather at the site of an air strike at a residential area near Sanaa Airport
እንዲህና እንዲያ እያልን ኑሮን በምንገፋበት ሰማይ ስር ከላይ ስለጠቀስኳቸው የወገን የስደት አበሳ መከራዎች መረጃ ከማቅረብ ቀዳሚው በጦርነት ማጥ ውስጥ ስለወደቁት ወገኖች አበሳ አደርገው ዘነድ ግድ ብሎኛል ። ይህንኑ የማለዳ ወግ ዳሰሳየን አጠናቅሬ ለማቅረብ ተፍ ተፍ ስል ለተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኮሚሽን እና ለሃያሏ አሜሪካ መሪ ለፕሬዚደንት ሁሴን ኦባማ ወገኖቻችን ይታደጉ ዘንድ ፊርማ ማሰባሰቢያ ላይ ፊርማየን አስቀምጨ መረጃ ሳገለባብጥ ለኢሮሞ ስደተኞች ድረሱላቸው የሚል የኢቦ ጁሃር መሃመድን የፊርማ ማሰባሰቢያ ጥሪ ተመልክቻለሁ ።
አንድ ሆነን በጦርነት አፋፍ ላይ ያሉ ወገኖችን እንደ መታደግ ዛሬም በልዩነት ተበታትነን የምናደርገው ጉዞ አልመችህ ቢለኝ አትፍረዱብኝ … ወደ እሰጣ ገባው ሳልገባ ከእኛ ስለሚጠበቀው አማራጭ የራሴን እይታ ላስቀምጥ ቀለም ከነጩ ወረቀት አገናኝቸ እንደጨረስኩ በቀጣዩ የማለዳ ወግ ቅኝት እስክመለስ ከአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ የተላለፈውን ቀጣይ ዘገባ ያደምጡ ዘንድ ልጋብዝዎ ወደድኩ … ! እስኪ በሁለተኛዋ የየመን ከተማ ኤደን ውጊያው ዘገርሽቶ ፣ የአየር ጥቃቱ በርትቶ በሚገኝባት ከተማ እየሆነ ያለውን ስሙት …
ቸር ያሰማን !
ነቢዩ ሲራክ
መጋቢት 30 ቀን 2007 ዓም

የአንዳርጋቸውን የትግል መንገድ ሚሊዮኖች ይከተላሉ። – ሳሙኤል አሊ (ከኖርዌይ)

ወደ በረሃ ወርዶ የሰራውን ስራ በፎቶዎቹ  እያየው ነው እነዚህን ፎቶዎችን ሳይ አይኔ በእንባ ይሞላሉ ልቤ በእልህ ይቀጣጠላል የተዘበራረቀ ስሜት ወደ ውስጤ ሲገባ ይታወቀኛል የደስታ ስሜት፣ የእልህ ስሜት፣ የቆራጥነት ስሜት፣ የጽናት ስሜት፣ የእውነተኝነት ስሜት ብቻ ምን ልበላቹህ ተደበላልቀው ውስጤን ይወጥሩታል እናም ፎቶዎቹን ሳያቸው የሚያወሩኝ ያህል ደስታን ይሰጡኛል ።
አንድ ቀን ታድያ አንድ የጎረቤት አገር ሰው ሁል ጌዜ በተደጋጋሚ ጌዜ  የዚህን ሰውዬ ፎቶዎች  ተመስጠህ ታየዋለህ ለምንድነው አለኝ ።
የኔም መልስ አይ ደስ ስለሚለኝ ነው አልኩት። እርሱም መልሶ ጥያቄወችን ይጠይቀኝ ጀመር አባትህ ነው? ዘመድህ ነው? ገበሬ ነው? ወዛደር ነው? ወታደር ነው? ምንድ ነው? ንገረኝ ደጋግመህ  ስታየው አባትህ ከሆነ  ብዬ ነው አልያም ዘመድህ  ደግሞ ይሄኘው   ፎቶ ገበሬ ደግሜ  ያኛው  ወዛደር ይሄኛው ደግሞ ወታደር ይመስላል ማን ነው ንገረኝ አለኝ እኔም ስመልስለት ልክ ብለሃል  እንደአባቴ የማየው አባት ያውም የኔ ብቻ ሳይሆን ነጻነት ለተጠሙ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ አባት ነው።  ከገበሬም ገበሬ ነው ስለገበሬው ነጻነት የሚታገል የገበሬው ወዳጅ ነው። ከወዛደርም ወዛደር ነው ድንጋይ እየተሸከመ እንጨት እየፈለጠ ወዛደሩን ለማሳደግ የሚተጋ የፍቅር አባት ነው። ከወታደርም ወታደር ነው ወዳጅን ሳይሆን ጠላትን በህዝብ አናት ላይ ቁጭ ብሎ በብረት ረግጦ የነገሰና የሚገዛን አገር አፍራሽ ለመገርሰስ ወታደር ሆኖ ለአገሩ ነጻነት ዘብ የቆመ  ብርቅዬና ውድ የኢትዮጵያ ወታደር ነው  ብዬ ገለጽኩለት። ስሙም አንዳርጋቸው ጽጌ  ይባላል  ስምን መለአክ ያወጣዋል ይባላል እውነት ነው ስምና ተግባርን አዋህዶ  የያዘ  የዘመኑ የኢትዮጵያ ብርቅዬ ልጅ ነው።
አንድ አርጋቸው ማለት የተራራቀን ማቀራረብ፣ የተለያየን ማገናኘት፣ ያልጸናን ማጽናት፣ የሚለውን ትርጉም ሲሰጠን። ጽጌ ማለት ደግሞ አበባ ማለት ነው። ሲተረጉም  የአንድነት አበባ እንደውም  የትም የማይበቅለው ኢትዮ ጵያዊ አበባ የእግዛአብሔር ጸጋ የሚያበቅለው አደይ አበባችን ነው።
ታድያ ይህንን የኢትዮጵያ የሰላም ባንዲራ፣ የነጻነት መዝሙር፣ የፍቅር ቅኔ፣ የእውነት ታጋይ፣ የሆነውን ድንቅዬ መከታችንን  ከአመት በፊት የመኖች ሚልዮን ዶላሮችን ተቀብለው ለአገር አጥፊው እና ለአረመኔው ወያኔ አሳልፋ የሰጠችው አንዳርጋቸው ሰለ ኢትዮጵያ ነጻነት የታገለ  ታጋያችንን የመን አሳጣችን። በአሁኑ ሰዓት በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያን የድረሱልኝ ጥሪ እያሰሙ ይገኛሉ። ወያኔ ግን ይሄን የወገን  ጥሪ የሚሰማበት ጆሮ አልፈጠረበትም። የዜጋቸው ደህንነት ያሳሰባቸውና ያስጨነቃቸው አገሮች ነገሩ ሳይብስ በጊዜው ዜጎቻቸውን አስወጥተዋል። ከ45 በላይ ኢትዮጵያን ግን የሚደርስላቸው አጥተው በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ አርበኛውን አንዳርጋቸው አፍኖ ለማምጣት የመን ድረስ አምርቶ  የነበረው ቦይንግ ዛሬ የጥይት ናዳ እየወረደባቸው ላለው ዜጎቻችን መድረስ አልቻለም።  አንዳርጋቸውን ለማሳፈኛ ለየመን ያወጡት በሚልዮን የሚቆጠር  ዶላር የዜጎቻችንን ነፍስ ለማዳን ሳይችሉ ቀርተዋል።  ይልቅ ለነሱ የወገን ድረሱልኝ ጥሪ ከወደ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር በፌስ ቡክ መስኮት የተናገሩት ቢኖር ስልክ ቁጥር ነው። እንዴት አሳፋሪ ነገር እየሰሩ እናዳለ የሁል ግዜ ተግባራቸውን በድጋሚ አሳይተውናል።  እኔን ያሳዘነኝ ነገር የራሷን የቤት ስራ ሳትሰራ፣ የራሷን የውስጥ መረጋጋት ሳታመጣ፣ ሰለራሳ ሕዝብ ሳትጨነቅ፣ የኢትዮጵያን እውነተኛ ታጋይ አሳልፋ  መስጠትዋ <<የራስዋ አሮባት የሰው ታማስላለች>>  የሚለውን አባባል ያስታውሰኛል ቢሆንም ግን  የመን ለሰራችው ስራ ልትጠየቅ ይገባል።
አንዳርጋቸው በኢትዮጵያን ልቦና ውስጥ የፈጠረው የአንድነት መንፈስ ወያኔን የማስወገድ  ሃላፊነትን ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን መንገድ ያሳየ  በመሆኑ  እኛ ልጆችህ ያሰብከውን ዲሞክራስያዊት አገር የማየት ህልምህን እውን ለማድረግ በአንድ አንዳርጋቸው ምትክ ሚልዮኖች ተተክተው ወደትግሉ ጎራ ገብተናል። ገዳያችንን ልናጠፋ፣  አንባገነኖችን ልንገረስስ፣ ወንጀለኞችን ለፍርድ ለማቅረብ  ቆርጠን ተነስተናል። እናም የተደወለው ደውል  የክተት ነውና  ሁሉም በያለበት  ወያኔ የተባለውን ሰው በላ አውሬ  ከኢትዮጵያ  ምድር እስከ መጨረሻው ለመደምሰስ እና ጨርሶ እንዳያንሰራራ አድርጎ የማስወገድ ደውል ነውና  ሁላችንም ለዚህ ክተት ጥሪ ተሳታፊ ሆነን ትግሉን እንቀላቀል።  የነጻነት ታጋይ የአንዳርጋቸው ጽጌ ልጆች እንዳለን ዛሬ የምናሳይበት ጊዜ  ነውና ገዳያችንን ገለን፣ አሳዳጃችንን አሳደን፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በስደት ከተበታተንበት ተሰባስበን በደስታና በሰላም የምንኖርባት  ዲሞክራሳዊት አገር እንዲኖረን ክተቱን ተቀብለን ነጻነታችንን እናመጣለን።

Sonntag, 5. April 2015

የት ሂዱ ነው? (ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም)

መስፍን ወልደ ማርያም (አዲስ አበባ)
ዓለም ሁሉ ጠላን፤ በየትም አገር እየሄድን ‹‹የሙጢኝ!›› ከራሳችን መሬት በጉልበት እየተነቀልን፣ ከራሳችን ቤት እየተባረርን፤ ከተወለድንበትና ከአደግንበት አካባቢ እየተፈናቀልን፣ ጭራውን ቆልምሞ እንደሚሮጥ ባለቤቱ እንዳባረረው ውሻ በአገኘነው አቅጣጫ እየሮጥን፣ እጃችንን እያርገበገብን ‹‹የሙጢኝ!›› እንላለን፤ የፈራነውን ሞት በየመንገዱ እናገኘዋለን፤ ሞትን ሸሽተን ሞት ያጋጥመናል፤ የሞቱ ልዩነት አይታየንም፤ በየመንገዱ የሚያጋጥመው ሞት የውርደት ሞት ነው፤ የብቸኛነት ሞት ነው፤ ዘመድ-ወዳጅ ለቀብር የማይገኝበት ሞት ነው፤ ሠለስት፣ አርባ፣ ሙታመት የማይወጣበት ሞት ነው፤ ባዕድ ምስጥ ያላሳደገውን አካል የሚበላበት ነው፤ የሞት ሞት ነው፡፡Prof. Mesfin Woldemariam : is an Ethiopian Human Rights activist and philosopher
ኢትዮጵያውያንን ሁሉ ከአገር አስወጥቶ ባዶ መሬት ብቻ ይፈልግ ይመስል የወያኔ ሎሌዎች በማስፈራራት ሁሉም አገሩን እየተወላቸው እንዲሄድ ያቀዱ ይመስላል፤ ጥንት ኢሰመጉ በምሠራበት ጊዜ በየጊዜው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ሰዎችን በማስፈራራት ሰላማቸውን ለመረበሽ ወደስደት ወይም ወደወንጀል ተግባር የሚመሩ የወያኔ አባለች ነበሩ፤ አሁን እንደገና ብቅ ማለት ጀምረዋል፤ ሕጋዊ ሥርዓት እየላላ ጉልበተኞች በግላቸው ለዘረፋና ለቅሚያ እየተሰማሩ ይመስላል፡፡
ስለራሴ ላውራ፤ ከእኔ የሚፈልጉት ምን እንደሆነ እርግጠኛ አይደለሁም፤ የሚፈልጉት የምኖርበትን አፓርትመንት እንደሆነም አላውቅም፤ በእኔ ቤት ያለ ሀብት የሚባል ለወያኔ አገልጋዮች የሚጠቅም ሁለት የገብረ ክርስቶስ ስዕሎች ብቻ ናቸው፤ (በዚህ አጋጣሚ እነዚህን ስዕሎች ለመግዛት የሚፈልግ ያነጋግረኝ)፤ ከዚህ ሌላ ለወያኔ ዋጋ የሌላቸው መጻሕፍት ናቸው፤ ስለዚህም አሁን በእኔ ላይ የተሰነዘረው ጥቃት እኔን ወደስደት ለመግፋት የሚደረግ ሙከራ ይሆናል፤ በ1992 ግድም ተሞክሮ ነበር፤ አልሠራም፤ ዛሬ ይበልጥ አይሠራም፤ ለማናቸውም ምክንያቱን በትክክል ለማወቅ ባልችልም በእኔ ላይ ዘመቻ መጀመሩን አንድ በቅርብ ከማውቀው ወያኔ በትክክል ተረድቻለሁ፤ ይህንን ዘመቻ በመምራት ላይ ያለውንም ሰው ማንነት ተነግሮኛል፡፡
ይህ አገር የአንድ ጉልበተኛ ቡድን ነው ብዬ አልቀበልም፤ የአባቶቼና የእናቶቼ፣ የኤቶቼና የቅድማያቶቼ አጥንትና ደም የገነባው አገር ነው፤ ማንም ለስደት አይዳርገኝም፤ ማንም አስፈራርቶ ኢትዮጵያዊነት መብቴን መግፈፍ አይችልም፤ አልፈቅድለትም፤ በግልጽ በማያጠራጥር ቋንቋ ኑሮዬም፣ ሕይወቴም፣ ሞቴም እዚሁ ነው፤ ከኢትዮጵያ አፈር የሚለየኝ የለም፡፡
እኔን ለማጥቃት ላሰፈሰፉት ወያኔዎችና ሎሌዎቻቸው አንድ እውነት ልንገራቸው፤– በፈለጉትና በተመቻቸው መንገድ በእኔ ላይ በጉልበታቸው ግፍ ቢፈጽሙ ነገ በነሱ ላይ የባሰ ግፍ እንደሚደርስባቸው ይወቁት፤ ሁልጊዜም ከሕግ የወጣ ጉልበተኛነት ጉልበተኛነትን ያነግሣል፤ በመግደል ድል ይገኛል ብለው የሚያምኑ ወያኔዎች ትንሽ ቆም ብለው ያስቡ፤ በመሞትም ድል ይገኛል፤ በመሞትም ማሸነፍ ይቻላል፡፡
በእኔ ላይ የዘመተው ወያኔ ወይም ሎሌ ማናቸውም ሥራ ውጤት እንዳለው ማወቅ አለበት፤ አንድ ነገር አድርጎ ምንም ዓይነት ውጤት አያስከትልም ብሎ ማሰብ ድንቁርና ነው፤ ይህ የሳይንስ ሕግ ነው፤ For every action there is a reaction ይላል!

ህወሃት መሪ ያጣ ድርጅት ነው። Abebe Gellaw

914e2-tplf_failing
ህወሃት መሪ ያጣ ድርጅት ነው። እኔ ለህወሃቶች የምመኝላቸው፣ እውነተኛ እራእይ ያለው መሪ እንዲያገኙ ነው።
ለነገ ሳይስቡ ዛሬ ሆድን በኪሳራ ከሞምላት፣ እራስን ከማወደስ፣ ሌሎችን ከማኮሰስ፣ አፈናቅሎ ከመውረስ፣ አምታቶ ከመዝረፍ፣ በሃሰት ከመክሰስ፣ ህዝብን ፈርቶ ከመኖር፣ በደካማ ዜጎች ስቃይ ከመደሰት፣ በዘርና በጎጥ ከመከፋፈል፣ በባዶው ከመጎረር፣ የሃሰት ክብርና ዲግሪ ከጥቁር ገበያ በርካሹ ከመሰብሰብ፣ ጥራት የሌላቸው የሰው አሻንጉሊቶች ከመሰብሰብ የሚያድን መሪ ያስፈልጋቸዋል።
ህወሃቶች ቆራጥ መሪ ሲያገኙ የትናንቱ ስህተታቸው ሁሉ ፍንትው ብሎ ይታያቸዋል። የበደሉትን ሁሉ ይቅርታ ይለምናሉ። አገር ማለት ሁሉም ያልአድርኦ በዜግነቱ ተከብሮ ከማንም ሳይበልጥ ከማንም ሳያንስ ሊኖርበት የሚገባው ምድር መሆኑ ይገለጥላቸዋል። ህወሃቶች መሪ ሲያገኙ ወደ ገደል ቁልቁል ከማብረር ይድናሉ። ፍሬን ይይዛሉ! ቆም ብለው ያስባሉ…
“ውድ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! በነጻነት ስም፣ ለችግር፣ ለመከራ፣ ለስደት፣ ለእስራት፣ ለግድያ፣ ለግፍ፣ ለዝርፊያ፣ ለአድልኦ፣ ለስርአት አልባነት፣ ተዘርዝሮ ለማያልቅ በደልና ግፍ ዳርገንሃል። ለሁላችንም የሚሆን አዲስ ምዕራፍ መክፈት ግድ ሆኖብናል። ይቅርታህን እንለምናለን!” የሚል ደፋር መሪ ያሳፈልጋቸዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ ሁል ግዜም ይቅር ባይ ነው።
መንደር መሃል እንደነጋበት ጅብ መሄጃ ከማጣቱ በፊት ህወሃት ደፋር መሪ እንዲኖረው እመኝለታለሁ። የእነ መለስን ስህተት ከሚደግም መሪ ይልቅ እወነተኛ ራእይ ያለው ቆራጥ መሪ ያስፈልገዋል። አርቆ አሳቢ፣ ከአድልኦ እና ጠባብነት የጸዳ ከዛሬ ከንቱነት ይልቅ ለመጪው ትውልድ ሁሉ የሚያስብ መሪ..

Donnerstag, 2. April 2015

በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ በ19ኛው ወንጀል ችሎት እየታየ ያለው የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች የክስ ጉዳይ ለሁለተኛ ቀን ምስክሮችን አሰምቶ በአወዛጋቢ መልኩ ለሚቀጥለው መጋቢት 30 ቀጠሮ ይዞ ተጠናቋል፡፡

11094691_787145494707278_7053697832185679926_n
በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ በ19ኛው ወንጀል ችሎት እየታየ ያለው የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች የክስ ጉዳይ ለሁለተኛ ቀን ምስክሮችን አሰምቶ በአወዛጋቢ መልኩ ለሚቀጥለው መጋቢት 30 ቀጠሮ ይዞ ተጠናቋል፡፡
ከእለቱ ዋዜማ ቃለ መሃላ ፈጽመው ሳይሰሙ የቀሩት ምስክሮች የተሰሙ ሲሆን ቃለ መሃላ በቀደመው ቀን በመግባታቸው ቀጥታ ወደ ምስክርነት ቃላቸው ተገብቷል፡፡ በሃያ ስድስተኛው የፍርድ ቤት ውሎ ተሰሙት ምስክሮች
7ተኛ ምስክር -ተስፋዬ መንግስቴ የመሰከሩት አቤል ዋበላ ላይ ሲሆን ከመንገድ ላይ ፓሊስ ሲፈትሹ አንዲታዘቡ ጠይቋቸው ቤቱ እና መስሪያ ቤቱ የተገኘው ሲዲ መጽሄቶች እና መጸሃፍት ላይ ሲገኙ አይቼ ፈርሜያለው አቤልም ፈርሟል ብለዋል፡፡
8ተኛ ምስክር- አቶ በረከት ጌታቸው በተመሳሳይ መንገድ ላይ ፓሊስ ታዘቡልኝ ብሎ የበፍቃዱ ሃይሉ ቤት ሲፈተሽ መታዘባቸውን በፍቃዱ የፈረመባቸው ነገሮች ላይም መፈረማቸውን ተናግረዋል፡፡ ጽሁፎቹ አማርኛ እና አንግሊዘኛ ከመሆናቸው ውጪ የሚያስታውሱት ይዘት አንደሌለ ተናግረዋል፡፡
9ኛ ምስክር - አቶ አንድነት ስሜ ይባለሉ አጥናፍ ብርሃኔ ላይ የመሰከሩ ሲሆን ቤቱ የተገኙ ወረቀቶች ላይ እሱም ፈርሟል አኔም ፈርሜያለው ብለዋል፡፡ የተገኙት ወረቀቶች አማርኛ እና እንግሊዘኛ ሲሆኑ ሴኩሪቲ ኢን ኤቦክስ የሚል መጽሃፍ አለበት ብለዋል፡፡ በይዘቱ ላይ አቃቤ ህግ አንዲመሰክሩ ቢጠይቅም ጠበቆች በይዘቱ ላይ ለመመስከር ስላልተመዘገቡ አንዳይመሰክሩ ተቃውሞ አቅርበዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ እንዲመሰክሩ ቢፈቅድም ምስክሩ ምንም ይዘት አንደማያስታውሱ ተናግረዋል፡፡
10ኛ ምስክር -አቶ ታምራት ዓለሙ የሚባሉ ሲሆን አቤል ዋበላ ቤት ሲፈተሽ እንደነበሩ በመግለጽ ምስክርነታቸውን አሰምተዋል፡፡ አቤል የፈረመባቸው ነገሮች ላይ ፈርመናል ያሉ ሲሆን የነጻነት ጎህ ሲቀድ መጽሃፍ እስልምና በኢትዬጲያ የሚል መጽሃፍ አዲስ ጉዳይ መጽኄቶች አና እምነት እና ተስፋ በኢትዬጲያ የሚሊ ጽሁፎች ተገኝተዋል፡፡ ሲዲም ተገኝቷል ብለዋል፡፡ የፍተሻውን ቀን ሚያዝያ 11 ነው ብለዋል፡፡ ( ጦማሪ አቤል የታሰረው ሚያዝያ 17 አንደሆነ ይታወቃል)
11ኛ ምስክር አቶ ፋሲል ግርማ ሲሆኑ በፍቃዱ ሃይሉ ቤት ሲፈተሽ ማየታቸውን ተናግረዋል፡፡ ቤት ውስጥ ተገኙት እቃዎች እና ሰነዶች ላይ ተከሳሹ ሲፈርም እኛም ፈርመናል ብለዋል፡፡ የተገኙትን ሰነዶች ብዛትና ይዘት እንደማያሰታውሱም ተናግረዋል፡፡
12ኛ ምስክር አቶ ደረጀ አበበ የኮንስትራክሽን እና ቢዝነስ ባንክ ባልደረባ ሲሆኑ ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀ ቢሮ ሲፈተሽ ፓሊስ ታዘቡ ብሏቸው አንደነበሩ እና ተገኙት ወረቀቶች ላይ ፈርመው ቢሮውን ዘግተው መውጣታቸውን ገልጸዋል፡፡ በወቅቱ የፈረሙበትን ወረቀት ይዘት የማያስታውሱት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
13ኛ ምስክር አቶ አክሊሉ ሃይለማርያም ጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ ላይ የመሰከሩ ሲሆን ስሙን ብቻ ነው የማስታውሰው በማለት ያዬትን ተናግረዋል፡፡ ፈረንሳይ ለጋሲዬን አካባቢ ያለው ቤቱ ሲፈተሽ የተገኙ አማርኛ እና እንግሊዘኛ ጽሁፎች የግል ማስታወሻዎች ሲም ካርድ እና መጽሃፍት የተገኙ ሲሆን ሁሉም ላይ በፍቃዱም ሲፈርም እኔም ፈርሜያለሁ ብለዋል፡፡
በ14ኛ ምስክርነት አቶ የማነ ብርሃኔ የተባሉ ግለሰብ ቀርበው የነበር ቢሆንም አቃቤ ህግ ‹የተለየ ነገር አያስረዱልኝም› በሚል ምስክሩ ሳይደመጡ እንዲመለሱ ፍርድ ቤቱን ጠይቆ ምስክርነታቸው ሳይሰማ ቀርቷል፡፡ አቃቤ ህግ አጠቃላይ 41 ምስክሮችን እንዳስመዘገበ በመጥቀስ ትናንት ካስመዘገባቸው 17 ምስክሮች ውጭ ሌሎቹን ፖሊስ በአድራሻቸው ፈልጎ እንዳጣቸው በመግለጽ ማቅረብ አለመቻሉን አስረድቷል፡፡ በሌላ በኩል ግን 8ኛ፣ 9ኛ እና 27ኛ ላይ አቃቤ ህግ ያስመዘገባቸው ምስክሮች መጥሪያ ደብዳቤ ደርሷቸው እንዳልተገኙለት ገልጹዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ የጠበቆችን (የተከሳሾችን) አስተያየት ጠይቆ ነበር፡፡ በዚህም ጠበቆቹ አሉ የተባሉትን ምስክሮች ፌደራል ፖሊስ ሌሎችን በአድራሻቸው ፈልጎ ማቅረብ ይገባው እንደነበር፣ እግዚቢት ላይ የተመሰከሩት ቃሎችን ፍ/ቤቱ እንዳይመዘግባቸው ማመልከት፣ እንዲሁም ያልተካዱ ዶክሜንቶች ላይ ምስክር መስማቱ ተገቢ እንዳልሆነ በአስተያየታቸው አስረድተዋል፡፡ በመሆኑም አቃቤ ህግ ቀሪ ምስክሮችን ማሰማት ካለበትም ምስክሮቹን በተሰጠው ቀን ( የማስረጃ መስማት ለሶሰት ተከታታይ ቀናት አንደተቀጠረ ይታወሳል) እንዲያቀርብ በማሳሰብ የደንበኞቻቸው የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብት በፍርድ ቤቱና በአቃቤ ህግ በኩል እንዲከበር ጠይቀዋል፡፡ በተለይ ባልተካዱ ዶክሜንቶች ላይ ይህን ያህል ጊዜ መውሰዱ ተገቢ አይደለም ብለዋል ጠንካራ ተቃውሞ አሰምተዋል፡፡ ጦማሪ ናትናኤል በበኩሉ ‹‹አቃቤ ህግ ያቀረበውን ሰምተናል፤ እኛ ብቻችንን አይደለም የታሰርነው፤ ቤተሰቦቻችንና ጓደኞቻችንም አብረውን ታስረዋል፡፡ በህሊና እና በኢኮኖሚ ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰብን ነው፡፡ ስለዚህ ይሄ ሁሉ ‹ውሳኔው ላይ አብሮ እንዲታይልን እናመለክታለን ብሏል፡፡
ፍርድ ቤቱ የጠዋት ምስክር መስማቱን ሂደት አጠናቆ ለከሰአት ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ከሰጠ በኋላ ከሰአት በኋላ ሁለት ጉዳዬች ብይን ሰጥቷል፡፡ የመጀመሪያው የምስክሮች ቃል ከመዝገቡ ጋር አንዲያያዝ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ቀሩ የተባሉት ሶስት ምስክሮች ታስረው ለመጋቢት 30 አንዲቀርቡ እና አቃቤ ህግ ተጨማሪ ምስክሮች አሉኝ ካለም አንዲያቀርብ ነው፡፡በዚህም መሰረት ለሶስት ቀን የታቀደው ምስክሮችን መስማት በአንድ ቀን ከግማሽ ተጠናቋል፡፡ ጠበቆች አቃቤ ህግ ቀድሞ በተወሰነው ቀን ምስክሮችን ሊያቀርብ ሲገባ ሌላ ቀነ ቀጠሮ መሰጠት የለበትም በማለት ያቀረቡትን ተቃውሞ ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል፡፡ አቃቤ ህግ በበኩሉ ምስክሮቹን በፌደራል ፓሊስ እያስፈለኩ ስለሆነ ተከሳሾ ማረሚያ ቤት እንዳሉ ለፍለጋው ጊዜ ይሰጠኝ ብሎ ነበር ፡፡
ጠበቆቹ አቃቤ ህግ የእግዚቢት ሰነዶችን በተመለከተ የመዝገብ ቁጥሩን ገልጾ እንዲቀርብ በጠየቁት መሰረት ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር፡፡ በትዕዛዙ መሰረት አቃቤ ህግ ዛሬ የመዝገብ ቁጥሩን ይዞ መቅረብ የነበረበት ቢሆንም፣ ጠበቆቹ ይህንኑ ጉዳይ በማንሳት ሲጠይቁ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ አልሰጠንም በሚል ክዷል፡፡
የዞን9 ማስታወሻ
አቃቤ ህግ የሌሉትን ምስክሮች ፍለጋ በማለት ለሚያባክነው ጊዜ ፍርድ ቤቱ አንደተለመደው ተባባሪ መሆኑ የፍትህ ስርአቱን በአጠቃላይ እና ይህንን መዝገብ ሂደት ይበልጥ አሳፋሪ አድርጎታል፡፡ አሁንም ቢሆን የተከሳሾች አፋጣኝ ፍትህ የማግኘት መብት ተጠብቆ ሁሉም ተከሳሾች ነጻ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ እንዲሰናበቱ አጥብቀን እንጠይቃለን ፡፡ ያልተሰራ ወንጀል ምስክር አይገኝለትም ፡፡
ዞን9

ወቅቱ የተግባራዊ ትግል ነው። አርበኖች ግንቦት 7፡ የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ

pg7-logoለገዛ ራሱ፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ እና ለኢትዮጵያ ቅን የሚመኝ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ህወሓትን ለማስወገድ ተግባራዊ ትግል ውስጥ መሳተፍ የሚኖርበት ወቅት ላይ እንገኛለን። በዚህ ወሳኝ ወቅት ከዳር ሆኖ መታዘብ ዘረኛውን፣ አምባገነኑን፣ ፋሽስቱን ህወሓት እንደመደገፍ ይቆጠራል።
ዛሬ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ህሊናውና አቅሙ በሚፈቅድለት የትግል ዘርፍ የመሰማራት ሰፊ እድል ተፈጥሮለታል። በዚህም መሠረት የህወሓትን አፈና በጠነከረ ክንድ ለመመከት የቆረጡ ኢትዮጵያዊያን ወደ በረሃዎችና ተራራዎች አቅንተዋል። ብዙዎች በመንገዱ ላይ ያሉ ጋሬጣዎችን ተቋቁመው እየተቀላቀሏቸው ነው። በደል የመረራቸው ሌሎች በርካታ ኢትዮጵያዊያን በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች በቡድን ለነፃነታቸው ዘብ ቆመው በህወሓትና አገልጋዮቹ ላይ እርምጃ መውሰድ ጀምረዋል። ይህ የሚበረታታ እና ተቀናጅቶ ሊጠናከር የሚገባው ጉዳይ ነው።
አሁን ያለንበት ጊዜ ልዩ የትግል ወቅት ነው። ትናንት በከተሞች ይካሄድ የነበረው ፀረ ወያኔ ትግል ዓይነተኛ መታወቂያው ሕዝባዊ ተቃውሞ ነበር። ዛሬ ግን ይህ ሁኔታ ተቀይሯል። በተለይ በአገዛዙ ፈቃድ የሚደረጉ ተቃውሞዎች ፋይዳ ቢስ ሆነዋል። በአገዛዙ ፈቃድ በሚደረጉ ተቃውሞዎች ለውጥ እንደማይመጣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በማያሻማ ሁኔታ ተረድቷል። ስለሆነም ትግሉ ወደ ሕዝባዊ እምቢተኝነት አድጓል።
ዛሬ ከዚህ በፊት ያልተሞከሩ የትግል ስልቶች ተግባራዊ እየሆኑ ነው። በዚህ ረገድ የሙስሊም ኢትዮጵያዊያን የተቀናጁ ርምጃዎች በአርዓያነት የሚጠቀሱና የሁሉም ኢትዮጵያዊያን ድጋፍ የሚሹ ናቸው። እነዚህ የሕዝባዊ እምቢተኝነት ተግባራት የእምነት አጥር ሳይለያየን ፍትህ የተጠማን ዜጎች ሁሉ ልንተገብራቸው የሚገቡ ናቸው።
ለምሳሌ፣ ተንቀሳቃሽ ስልኮችን በተወሰኑ ቀናት መዝጋት በተቀናጀ ሁኔታ ከተደረገ ከፍተኛ ውጤት ሊያመጣ የሚችል፤ በሙስሊም ወገኖቻችን ግንባር ቀደም መሪነትና አስተባባሪነት ተሞክሮ በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ተግባራዊ ሊደረግ የሚችል መሆኑ የታየ አንድ የትግል ስልት ነው።
በአሁኑ ወቅት ተግባራዊ በመደረግ ላይ ያለው ሣንቲሞችን የመሰብሰብ ዘመቻም ሌላ ከዚህ በፊት ያልተሞከረ፤ በተጨማሪ እርምጃዎች ከታገዘ ህወሓት መራሹ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን ገንዘብ መቆጣጠር የማይችልበት ደረጃ ላይ ሊያደርስ የሚችል ጉልበት ያለው ስልት ነው። ውሳኔው ሣንቲሞችን ብቻ ሳይሆን የወረቀት ኖቶችንም ሲያካትት በዝውውር ላይ የሚኖረውን ገንዘብ ብዛት የሚቆጣጠረው ህወሓት ሳይሆን በደል ያንገሸገሸው ሕዝብ ይሆናል። በባንኮች ያለ ተቀማጭ ገንዘብ በማውጣትም የህወሓት የፋይናንስ ተቋማትን ማሽመድመድ ሌላ ተግባራዊ ሊደረግ የሚችል ስልት ነው። በእነዚህ እርምጃዎች የተለማመደ ሕዝብም ወደ ግዢ እቀባ፤ ለተወሰኑ ቀናት ከቤት አለመውጣት ብሎም “ግብር አልከፍልም” ወደማለት ሊሸጋገር ይችላል።
እንዲህ ዓይነቱ ስልቶች ውጤታማ እንዲሆኑ ግን የመላው ሕዝብ ተሳትፎ እና የተቀናጀ አሠራርን ይፈልጋል። ለምሳሌ፣ ሰብስቡ ሲባል መሰብሰብን፤ በትኑ ሲባል መበተን ይጠይቃል። እንዲህ ዓይነት የተቀናጁ የጋራ እርምጃዎች በአምባገኑ የህወሓት አገዛዝ ላይ ከሚያደርሱት ጥቃት በተጨማሪ በኢትዮጵያዊያን መካከል ያለውን መግባባት ያጠናክራሉ። እንዲህ ዓይነት የተቀናጁ የጋራ እርምጃዎች በማኅበረሰብ ቡድኖች መካከል አዎንታዊ መስተጋብር ለመፍጠር የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ ነው።
አሁን አገራችን የምትገኝበት ሁኔታ በጥሞና ሲጤን የኢትዮጵያ ሕዝብ ሳይነጋገር መግባባት፣ እርስ በርሱ መናበብ የሚችልበት ደረጃ ላይ እየደረሰ መሆኑ መረዳት ይቻላል። ይህ ስነልቦናዊ ዝግጅት ደረጃ በደረጃ ጠንከር ያሉ እርምጃዎችን ለመውሰድ ያዘጋጀናል።
በማናቸውም የጋራ እርምጃዎች ለግል ጥቅሞቻቸው ቅድሚያ የሚሰጡ፤ ራሳቸው “ብልጥ” አድርገው በማየት በተፈጠረው ሁኔታ መጠቀም የሚፈልጉ፤ በሌላው ድካም ለማትረፍ የሚሯሯጡ ሰዎች መኖራቸው የማይቀር ነው። ህወሓት ለሃያ አራት ዓመታት ኮትኩቶ ያሳደገው የአድርባይነት ባህልም ሌላው እንቅፋት ሊሆን እንደሚችል መገመት ቀላል ነው። ድህነት ደግሞ በገዢዎች ላይ ጨክነን የመነሳት አቅማችንን እንደሚያዳክም የታወቀ ነው። ሆኖም ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ከፊቱ የቀረበለት ምርጫ “ባርነት ወይስ ነፃነት” መሆኑን የተገነዘበበት ጊዜ ላይ ደርሰናል።
በዚህም ምክንያት ለህወሓት ባርነት ከመገዛት ነፃነትን የሚመርጥ ዜጋ ሁሉ ዋጋ ለመክፈል መዘጋጀት ይኖርበታል። ለሁላችንም የሚሆን የትግል ዘርፍ መኖሩ የሕዝቡን ተሳትፎ ከፍ ያደርገዋል። የሁለገብ ትግል ስትራቴጂ ጥቅሙም እዚህ ላይ ነው። ማንም የማንም ነፃ አውጭ አይደለም። ሁላችንም ተባብረን ሁላችንንም ነፃ እናወጣለን።
አርበኖች ግንቦት 7፡ የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ “ትግላችን ዘርፈ ብዙ ነው፤ ተግባራዊ ትግል የሚደረገውን በሁሉም ቦታዎች ነው፤ እርጃዎቻችን እናቀናጅ፤ ወቅቱ የተግባራዊ ትግል ነው” ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!