Netsanet: Januar 2015

Samstag, 31. Januar 2015

እና አሁን ምንድን ነው መደረግ ያለበት?። ዳዊት ዳባ

የተለመደውን ኮሮጆ ገልብጦ አሸንፌያለው ማለት ሁሌ የሚሰራም አስተማማኝም በጭራሽ አልሆነም። በይበልጥ ደግሞ አሁን ባለው ጠቅላላ ያገራችን ሁኔታ መስረቅ እሰከጭራሹ እንዳይቻል ለማድረግ በቀላሉ ይቻል ነበራ። ካነሰም ሌብነቱ መውጫ የሌለው ጦስ ይዞ እንዲመጣ ለማድረግ የሚቻልባቸው መንገዶች እንዳሉ በጥልቀት ያሰቡበት አይተውታል። በይበልጥ ደግሞ አንድነቶች። አገዛዙ የምርጫ ጫወታ ይኖራል እስካለ መጫወቱ የምናተርፍበት ነው ተብሎ ሱገፋ የነበረው ለዚህ ነው። እኛ ጠንካራ ሆነን የመቅረባችን ጉዳይ ነው እንጂ አንድ ቀን ተነስቶ ምርጫ የሚባል ጫወታ ከዛሬ ጀምሮ የለም ሊል እንደሚችልም ግልፅ ነበር። በእርግጥ ያአንባገነን ለከት ያጣ የፍራቻ ባህሪ ሆኖ ነው እንጂ አሁን ላይ ወደዚህ ውሳኔ እንዲደርስ የሚያስገድደው ዝግጅትና ጥንካሬው ተቃዋሚው ነበረው ለማለት ይከብዳል።

ስለዚህ ምርጫ በፃፍኩ ቁጥር ከፈለገ “እራሱ የምርጫ ጫወታ ቀርቷል” ይበል የምትለዋን ነገር በአፅኖት በተደጋጋሚ አንስቻታለው። ለምን ቢባል እዚህ ውሳኔ ላይ በቀላሉ ማድረስ እንደሚቻል ስላወኩ ነው። ገና ከመነሻው ከምርጫው እንታቀብ የሚለው ሀሳብ ትርፉ አላጠገበኝም። ያን በማድረግ ሊገኝ የሚታሰበውን ትርፍ በተሻለ መንገድ ጨማምሮ በቀላሉ ማግኘት የሚቻልበትም መንገድ ስላለም ነዋ።

አሁን በገሀድ ወናዎቹን ተቀዋሚዎች አግዷዋችዋል። አንድነትና መኢአድን ከምርጫው ማገድ ማለት ምርጫ ጫወታ የለም ማለት ነው በራሱ። በአዋጅ መልክ ባያስነግረውም በቀላሉ የምርጫ ጫወታ ቀርቷል እንዲል ተገዷል ማለት ይቻላል። በአዋጅ መከልከሉም በቀጣይ በምንወስደው ፖለቲካዊ ውሳኔ ድግሞ የሚወሰን ነው የሚሆነው። ይህን ወይ ያንን እውነተኛ ተቃዋሚ ከምርጫው በማገድ ተሳስቶ ነው እንጂ ወያኔ የሚያገኘው ትርፍ የለም። ባቂላ ጠፋ ቢሉ አይነት ነው ለለውጥ ፈላጊው የመጨረሻ ወጤቱ። በግድ በአንድ ይሰባስበናል አለቀ። ይህ ደግሞ ያቃተን ልንሰራው ግድ ይል የነበረ የቤት ስረችን ተሰራ ማለት ነው። በእርግጥ በዚህ ታስቧቸውና ፍራቻቸው ሰማያዊ ፓርቲንም ከምርጫው ማገዳቸው እንደማይቀር እሙን ነው። ላሁኑ ግን ሰማያዊም መድረክም የምርጫው ጫወታውስጥ አሉ። እና አሁን ምንድን ነው ማድረግ ያለብን?።

በመጀመርያ በተፈጠረው ሁኔታ የተናደድን ያዘንን የተናደድንበትና ያዘንበት አካል። እንዲሁ ለዚህ ፍፁም ኢፍትሀዊና አንባገነናዊ እርምጃ ተጠያቂ የምናደርገው ክፍል አምታች መሆን አልነበረበትም። በዚህ ተጨባጭ ሁኔታ ጅብ በቀደደውም አይሰራም። ያለው ጅብ ብቻ ነዋ። የቀደደውም የገባውም ጅብ ነው። ድርጅቶቹ በትንሹ ቢሰላ እንኳ ብዙሺ አባላት አላቸው አስርጎም ለማስገባት ሆነ ያኮረፈ፤ ገንዘብና ስልጣን ፈላጊ፤ ሰርቆ ወይ ቦርቧሪ ሆኖ የተባረረ አንድና ሁለት ሰው ከየደርጅቶቹ ማግኘት ከባድ ተደርጎ የታየው ለታየው እንዴት ነው?። ቆይ በረከት ስሞንን የአንድነት። ተክላይ ተክሉ የመኢአድ አባል ነበሩ ብሎ ፎርጅድ መታወቂያ ሰርቶ አሳይቶን ለበረከትና ለተክላይ ቢያድላቸውስ ኖሮስ። ይህን አበባውና አወልን ባይገኙ ኖሮ የማያደርጉት ነበር ወይ?። ይቁረጥ አለዛ እኔ እቆርጥልሀለው። እዚህ ደረጃ የሚወርድ ፍፁም የሆነ አሪዬስ ስልጣን ላይ እስካለ ለወደፊቱም የትኛውም ድርጅት ሊያስቀረው የሚቻለው ችግር በጭራሽ አይደለም። የፈለገ ጊዜ በቀላሉ የትኛውም ድርጅት ላይ ሊያደርገው የሚችለው ቀላል ነገር ነው።ለነገሩ ደደብነታቸው ነው እንጂ ፍርድ ቤቱም የነሱ በምርጫ ቦርድ ተብዬው ከሚያደርጉት በፍርድ ቤት ቢያደርጉት ይሻላቸው ነበር።

ለማንኛውም የምናለቅስበትን አካል እንለይ። ተቃዋሚዎች ታቃዋሚዎች ሲሉ ማስለቀሱ ላይ ወያኔዎች ማልያ ቀይረው በመጀመርያ ረድፍ አሉበት ይግባችሁ። ጅብ በቀደደው የሚሰራው እዚህ ላይ ነው። ፋይዳ የሌለው አመል ብቻ የሆነ ፖለቲካል ትርፍ ለማግኘት ወይ እኛ ትክክል ነበርን ለማለት ሲባል በዚህ መንገድ ልናጮህው የምንፈልግ አደብ እንግዛ ። ምርጫ 97 ላይ ወያኔ ከወሰደው እርምጃ በላይ ትግል ላይ ነን የሚሉ ክፍሎች የሰሩት ስህተት ነው። ብዙ የዋህ ዜጎችን ዛሬም ድረስ ተቃዋሚ፤ ፖለቲካና ትግል የሚባል ነገር ሲሰሙ እንዲንዘፈዘፉ ያደረገው። በሗላ ማቃናቱ እንደማጥፋቱ ቀላል አይሆንም። አንዳንዴ ዝም ብዬ ሳየው ላፉ ተተኩሶ ነው መባረር ያለባቸው ከሚለው ክፍል በላይ በሰላም እንታገላላን የሚሉት በሰላም ሲሉ የነሱን ሰላማዊነት ለመግለፅ ነው እንጂ ከሰላማዊ ሀይል ጋር እንደማይታገሉ በደንብ ያውቃሉ። እንደሚገለን እናውቃለን፤ እንደሚያስረን እናውቃለን፤ እንደሚጨፈጭፈን አውቀን ነው ሌባ ነው ኮሮጆ ይገለብጣል። ይኮ የሁሉም በጋራም የተደረሰበት ከልብ የሆነ አቋም ነው። የዘመኑን ትግል ክፉም ልዩም ያደረገውም ይህ ነው።

ሰማያዊና መድረክ ከምርጫው አንዱ የሚታገድ ከሆነ አብሮ ከምርጫው ለመወጣትና፤ ለምርጫው እጩዎችን መደላደል ላይ ብቻ ስምምነት በቀናት ሰርቶ ቅንጅት መፍጠራችሁን ይፋ ማድረግ ሁለት።

አንድነትና መኢአዶች በህግ ቤት የተቀማችሁትን መብት ለማስመለስ መሞከሩ። በሂደት አዲስ ድርጅት ሆኖ መውጣቱም ሆነ ያሉት ድርጅቶች ውስጥ ተደባልቆ የመታገሉ አማራጭ እንዳለ ሆኖ አሁን ሙሉ እውቅና ምርጫው ውስጥ ለቀሩት ድርጅቶች መስጠት። በአዋጅ ላአባሎቻችሁም ለደጋፊዎቻችሁም ለህዘብም ሙሉ ድጋፍና ርብርቦሽ ይሆን ዘንድ መናገር። ሶስት
ከአገር ውጪ ያሉ ድርጅቶች አመራሮች በሙሉ አንድ ቦታ ላይ በአካል ተገናኝታችሁ በሚታይ፤ በሚሰማ መንገድና ፕሮቶኮል በጠበቀ ሁኔታ እጥር ያለና ቀጥተኛ ጠንካራ የሆነ እውቅናን ምርጫው ላይ ለቀሩት ድርጅቶች መስጠት። ድጋፍ ሰጪ አካል ማቆም። ሶስት ወር የሚቆይ የምርጫ ዘመቻ መጀመር። አራት።

ለየትኛውም አይነት ምት የፃፈ ምት ያስፈልገዋል። አናደርገውም እንጂ ሁሌም ደግሞ ድላው ነበረን። ተመጣጣኝ ነው አይደለም ሌላ ጉዳይ ነው። ለቅሶ እንጂ አፀፋ ስለማንመልስ ግን ዜጋውንም አፈዘዝነው። አለማምደነው ቢሆን ይህ ህዝብ ጉለበተኛነቱን የሚያሳይበት መልካም አጋጣሚ ነበር። ባለመሆኑ ማንን ፍርቼ ገደባ አጣ። ለነገ እየተሰራበት ያለው ዱላ በጊዜው ይደርሳል። አሁን ላይ የሚቻለውንና ያለንን ዱላ ስናሳርፍ ነው ለትልቅ ጉዳይ ህዝባችንን ማሰለፍ መቻላችንን እርግጠኛ መሆን የሚቻለው።

ሰማያዊና መድረኮች መጠንቀቅ የሚገባችሁ ሶስት ወር አምስት አመት አይደለም። በቀጥታ ምርጫው ላይ ልትሰሩበት ይገባ የነበረ ጊዜ እያማሸከ ነው። በዛ ላይ ለመምረጥ መመዝገቡ የጊዜ ገደብ አለው። በሌሎች ነገሮች ተወጣጥራችሁ ስላላችሁ ለመምረጥ ምርጫው ላይ እናንተ መኖራችሁን ብቻ ሳይሆን ቀጥሉን የሚጠብቁ ሚሊዬን ለውጥ ፈላጊዎች መመዝገቢያው ጊዜ እንዳያልፍባቸው ጠንከር ተደርጎ አሁኑኑ መምረጫ ካርዳችሁን ያዙ ሊባሉ ይገባል። ካርድ ይዞ አለመምረጥ ይቻላል። ካርድ ሳይዙ መምረጥ ግን አይቻልም። ምርጫውን በሚመለከት ሌሎችም የጊዜ ገደብ ያላቸው ጉዳዬች ይኖራሉና ድርጅቶች ጠንቀቅ ነው። ምረጡንም ስራ አሁን እንደውም ዛሬ ነው መጀመር ያለበት። አደባባይ ሰልፉን ለጊዜው ተውትና ምረጡን ምረጡን ብቻ በቀረው ጊዜ።

Zone 9 Bloggers Move to Trial on Amended ATP Charges in Ethiopia

Zone 9 Bloggers Move to Trial on Amended ATP Charges in Ethiopia
U.S. Department of State - Great Seal
Press Statement

Jen Psaki
Department Spokesperson
Washington, DC
January 29, 2015
The United States is concerned by the Ethiopian Federal High Court’s January 28, 2015, decision to proceed with the trial of six bloggers and three independent journalists on charges under the Anti-Terrorism Proclamation. The decision undermines a free and open media environment—critical elements for credible and democratic elections, which Ethiopia will hold in May 2015.

We urge the Ethiopian government to ensure that the trial is fair, transparent, and in compliance with Ethiopia’s constitutional guarantees and international human rights obligations. We also urge the Ethiopian government to ensure that the trial is free of political influence and continues to be open to public observation.

The use of the Anti-Terrorism Proclamation in previous cases against journalists, activists, and opposition political figures raises serious questions about the implementation of the law and about the sanctity of Ethiopians’ constitutionally guaranteed rights to freedom of the press and freedom of expression.

Freedom of expression and freedom of the press are fundamental elements of a democratic society. We call on the government of Ethiopia to support freedom of expression and freedom of the press to demonstrate its commitment to democracy as it approaches its May 2015 national elections.

የገዢውን ፓርቲና መንግስትን ሽፍትነት ያጋለጠው አንድነትን የማፍረስ የምርጫ ቦርድ ውሳኔ በኢትዮጵያዊን ዘንድ ተቀባይነት አይኖረውም!!! – ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

ጥር 21/2007 ዓ.ም በኢትዮጵያ ታሪክ የምርጫ ቦርድ የሚባል ተቋም ያለበትን ደረጃ ይፋ ያደረገ ሲሆን፤ በዚህ ደረጃ እንዲዋራድ ከጀርባ ሆኖ አመራር የሚሰጠው ገዢ ፓርቲም ሆነ መንግሰት በዚያው ልክ የሚገባቸውን የተዋረደ ደረጃ የያዙበት ዕለት ነው ብለን እናምናለን፡፡ አንድነት ፓርቲ አንድም የህግ ጥሰት ሳይፈፅም የሚያደርጋቸውን ሁሉ በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብና በሀገሪቱ ህግ እየፈፀመ ባለበት ሁኔታ በህግ ሽፋን የገዢው ፓርቲ ልሳን የሆነው ፋና ሬዲዮ፣ የመንግሰት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ከምርጫ ቦርድ ጋር በመተባበር የከፈቱት ዘመቻ የመጨረሻ የሆነውን አንድም ህጋዊ መሰረት የሌለውን ህገወጥ ውሳኔ በአንድነት ፓርቲ እና አባላት ላይ አሰተላልፈዋል፡፡
ገዢው ፓርቲና መንግሰት በምርጫ ቦርድ በኩል እንዲነበብ ያደረጉት የፖለቲካ ውሳኔ በኢትዮጵያ ሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ስርዓት ከወረቀት አልፎ በተግባር እንዳይታይ ግብዓት መሬቱን ፈፅመዋል፡፡ በዚህ ፀያፍ ተግባር ከፊትም ሆነ ከጀርባ ሆነው የተሳተፉ ግለሰቦችም ሆኖ ተቋማት በታሪክ ተገቢው የውርደት ቦታ እንደሚይዙ እምነታችን ነው፡፡ ይህ ህገወጥ አካሄድ ህጋዊ መሰመር እንዲከተል የበኩላቸሁን ድርሻ የተወጣችሁ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች በሀገር ውሰጥም ሆነ በውጭ የምትገኙ ሁሉ በተለይ በገዢው ፓርቲ እኩይ ሴራ በሀስት ተወንጅላችሁ በወህኒ ቤት ለምትማቅቁ ታጋዮች ታሪካችሁ በወርቅ ቀለም ተፅፎዋል፡፡ በቀጣይም ያለምንም መዘናጋት እና ተሰፋ መቁረጥ በምናደርገው ሰላማዊ ትግል በሀገራችን ኢትዮጵያ የመድበለ ፓርቲ ሰርዓት ትንሳኤ እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለንም፡፡
የምርጫ ቦርድ ተብዬው ተቋም በህገወጥ መንገድ ለሆዳቸው ባደሩ ጥቂት አንድነት ፓርቲ አባላት እና በአንድነት አባልነት በማይታወቁ የገዢው ፓርቲ ጥርቅሞች ለተደረገ ጠቅላላ ጉባዔ ዕውቅና ሰጥቻለሁ ማለቱን በምንም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው ሲሆን፣ የአንድነት ፓርቲ አባላት ያነገብነው የነፃነት መንፈስ በምርጫ ቦርድ በሚሰጥ ሰርተፊኬትና ዕውቅና ማዕቀፍ ውስጥ የሚገኝ ስለአልሆነ ለነፃነት የምናደርገውን እልህ አስጨራሽ ትግል የምንቀጥል ሲሆን፤ በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የአንድነት መዋቅሮች እና የአንድነት አባላት ለዚህ ህገወጥ ቡድን በግልፅ እውቅና እንዲነሱ እንጠይቃለን፡፡
ፓርቲያችን በመጨረሻ ሰዓት እንኳን ተፈትነው ለወደቁ ተቋማት እድል ለመስጠት ወደ ፍርድ ቤት ለመሄድ ወሰኖ እንቅሰቃሴ በማድረግ ላይ ቢሆንም፤ በዛሬው ዕለት ጥር 22/ 2007 ከቀኑ ሰባት ሰዓት ጀምሮ የፓርቲያቸን ፅ/ቤት በፖሊስ ተወሮ የፓርቲው ንብረት ያለምን ህጋው ርክክብ በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጎዋል፡፡ በአሰተዳደር የተሰጠን ውሳኔ በፍርድ ቤት የማሰለወጥ ህጋዊ ሰርዓት እንዳለ ቢታወቅም ህገወጥ አስተዳደራዊ ውሳኔን በፖሊስ ወረራ ለማሰፈፀም የተሄደበት መስመር ገዢው ፓርቲና መንግሰት አሁንም ከጫካ አሰተሳሰብ ያለመውጣቸውን እና የአውራ ፓርቲ ፍልስፍናቸውን በማናለብኝነት ለመተግበር መቁረጣቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህ ህገወጥ ድርጊት ተጠያቂው ትእዛዙን ያስተላለፈው ክፍል መሆኑ መታወቅ ይኖርበታል፡፡
ሰለሆነም በሀገር ውስጥ እና በውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን፣የሰብዓዊ መብት ተማጋች ድርጅቶች፣ የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ እንዲሁም በኢትዮጵያ ሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ሰርዓት እንዲጎለብት ፍላጎት ያለችሁ ሁሉ ይህን እኩይ ተግባር በማውገዝ ተጨባጭ እርምጃ እንድትወሰዱ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
ድል የህዝብ ነው!!!

ህወሃት በዘረፈውና በሚዘርፈው ሃብት ተጠቅሞ ለወዳጆቹ የሚያኮራ፣


ህወሃት በዘረፈውና በሚዘርፈው ሃብት ተጠቅሞ ለወዳጆቹ የሚያኮራ፣ ትውልድ ለሚላቸው የሚበጅ ተግባራት እያከናወነ እንደሆነ ይነግረናል፤ ይነግሩናል። ውስን ባለሥልጣናትና አበሮቻችው በሃብት ተመንድገዋል። በንዋይ ሰከረው የሚያደርጉት እስኪጠፋቸው ናጥጠዋል። የት ጋር አንደሚያበቃ ባይታወቅም፣ የተደሰቱ፣ የተከፉ፣ የተናቁ፣ የተሰረቁ፣ የሚሰረቁ፣ እየሰረቁ ያሉ፣ የተትረፈረፈላቸው፣ በስማቸው የሚነገድባቸው፣ ባሪያዎችና ባንዳዎች፣ ቀን የሚጠብቁ፣ ጥርሳቸውን የነከሱ፣ … ወዘተ “አብረው” አሉ፡፡ ዘመን፣ ወራትና ቀናት ቅዠትን በመሰሉበት ዓለም፣ ቁራሽ ለሚሞላው ከርስ ራሳቸውንና ማንነታቸውን፣ ከዚያም አልፎ የትም የማይደበቁትን ኅሊናቸውን ያቆሸሹ፣ የአገር “እንግዴ ልጆች” ወይም “ውርጃዎች” ለህወሃት የማከሰምና የመግደል ሴራ ተላላኪ ሆነው የህዝብን ክብር ሰልበው ረክሰው ያረከሳሉ። ከዚህም በላይ ነገ እንደ ውዳቂ ላንቲካ መጣላቸውን እያወቁ፣ አሽከርነት፣ ከሃዲነት፣ ውርደት፣ መለያቸው እንዲሆን መርጠው ተሳቅቀው ይኖራሉ። እነሱን ጨምሮ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ባመነበት መንገድ እንዲጓዝ ለመታገል የሚውተረተሩትን ተኩላ ሆነው ያስበሏቸዋል። ቅንጅትን በሉት። ቅንጅትን አሳረዱት። ተቀራመቱተ። የውስጥ ችግሩ እንዳለ ሆኖ እነርሱ ግን ዕጣ መድበው ተጣጣሉብት። አየለ ጫሚሶና ባልደረቦቻቸው “የክህደት ዋንጫ” ተሞላላቸው። ከዚያም ተጣሉ። አሁን “ምርጫ” ደርሷል፤ ድንጋጤ ጨምሯል፤ የሕዝብ ሱናሚ አስፈርቷል፤ የህንጻውና የመንገዱ ሁኔታ አልበቃም፤ የሰዉ ህይወት ከመቅለሉ የተነሳ ለሚዛን አልበቃ ባለበት አገር ህይወቱ “በቀላል ባቡር ሊቀልል” ሽር ጉድ ይባላል፤ “ሥራ ላይ ነን፤ ምርጫ ደርሷላ”፤ አስተናጋጇ ህወሃት በለመደችው መንገድ ልታባብል ብዙ ትጥራለች፤ በየማዕዘኑም እያደባች ነው፤ እስከ “ምርጫ” ቤቷን አሳምራ ቄጠማ ጎዝጉዛ፣ ፈንዲሻ ነስንሳ፣ ዕጣኗን አጫጭሳ “እንኮምር” እያለች ነው፡፡ ግን አልበቃትም፤ አላመነችም፤ ተጠራጥራለች፤ ተጨንቃለች፤ ተቀናቃኝ ፓርቲዎችን በተለይም አንድነትን ለማጥፋት “ቡና ጠጡ” በማለት የሚላላኩላት የቦርዱ “ምሁራን” ላይ ታች እያሉ ነው። ኃላፊው ለምን ይህንን የተላላኪነት ሥራ እንደፈለጉት ባይታወቁም የቦርዱ አሽከርካሪ ምክትላቸው ግን “የዜግነት” ድርሻውን እየተወጣ ነው፡፡ “ለወገን ደራሹ ወገን” አይደል የሚባለው! ስለዚህ ህወሃት የሰፈረውን “የሚያገለማ ጽዋ” ለመጋት ርኩቻው ደርቷል። ፕሮፌሰርነት ከሚሰጠው ክብር ይልቅ “ተላላኪነት” ኩራት ሆነ በአገራችን ሶስት ዓይነት ባርነት እንዳለ ይነገራል፡፡ የእነዚህ ባሪያዎች (ባንዶች) ማንነት ገፍቶ የሚወጣው “ምርጫ” በደረሰ ጊዜ ነው፡፡ አንደኛውና የመጀመሪያው ባሪያ “ምርጫ ቦርድ” የሚባለውና ሌሎች መሰል “የተቋም ባሮች” ናቸው፡፡ ሁለተኛው ባሪያ ምርጫ ቦርድን እና ተመሳሳይ ተቋማትን የሚመሩ አመራሮች ናቸው፡፡ ሦስተኞቹ ባሮች ደግሞ ህዝባቸውን ለንዋይ ሲሉ የሚሸጡ አገልጋዮች ናቸው፡፡ በሌላ ቋንቋ ህወሃት የጠፈጠፋቸው፣ ያቦካቸው፣ የሚነዳቸው፣ ሲፈልግ አዋርዶ የሚያባርራቸው ናቸው፡፡ የዘመንና የትውልድ ሁሉ ተጠያቂ ባንዳዎች! ሰሞኑን ምርጫ ቦርድ የባርነቱን ዘመን ለማራዘም በለመደ እጁ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች ላይ “አብዮታዊ ዴሞክራሲ” ጡጫ ለማሳረፍ፣ ለመሰንጠቅ፣ ለማክሰምና ለማፍረስ ደፋ ቀና እያለ ነው፡፡ ምርጫ ቦርድ ቀደም ሲል ቅንጅትን በማፍረስ ታማኝ ሎሌነቱን እንዳስመሰከረ ሁሉ አሁንም ለህዝብ የእንግዴ ልጅነቱን ለህወሃት/ኢህአዴግ ደግሞ ታማኝ አሽከርነቱን ለማረጋገጥ እየተባ ይገኛል፡፡ እኛም እንደ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የባንዳዎችን ጥርቅም እናወግዛለን፡፡ ታሪክና ትውልድም ይህንን እንዳይረሱት እናሳስባለን፤ እንመዘግባለን፡፡ አገራችን ኢትዮጵያ የሚዘርፉትን፣ እየዘረፉ ያሉትን፣ የተዘረፉትን፣ እየተዘረፉ ያሉትን፣ ዘርፈው የሚያደርጉት የጠፋባቸውን፣ በሃብት የናወዙትን፣ በደም የተጨማለቁትን፣ የራባቸውን፣ ምርጫ ቦርድን፣ የኢህአዴግን ሎሌዎች፣ አሽከሮች፣ ሁሉ ይዛ እየነጎደች ነው፡፡ የጥጋቡም የግፉም ማብቂያ መቼ እንደሆነ ባይታወቅም የከፋቸውና ጥርሳቸውን የነከሱ እንዳሉ ከበቂ በላይ ማስረጃ አለን፡፡ ንጹህ አገር ወዳዶችና እኛም ጎልጉሎች ያንን ቀን አንናፍቀውም፡፡ ባንዶች ግን ይህንን ቀን የማስቀረት አቅም አላችሁና ወደ ኅሊናችሁ ተመለሱ፡፡ ህዝብ ይምረጣቸው ወይም ይጥላቸው አንድነትንም ሆነ ሌሎቹን የተቀናቃኝ ፖለቲካ ፓርቲዎችን ከራሳቸው ችግር ጋር ለህዝብ ውሳኔ ብትተዋቸው ይሻል ነበር፡፡ ነገርግን ውሻ ወደ ትፋቱ እንደሚመለስ እናንተም ዳግመኛ ባንዳነታችሁን አስመሰከራችሁ፤ ባርነታችሁንም ቀጠላችሁበት፡፡ ...........................source.-www.goolgule.com

ትዕግስቱ አወሉ እንደ አየለ ጫሚሶ:- አንድነትን “እናኝከዋለን፤ እንገድለዋለን” – ምርጫ ቦርድ

በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

አንድነትን “እናኝከዋለን፤ እንገድለዋለን
አንድነትን “እናኝከዋለን፤ እንገድለዋለን
የዛሬ አስር ዓመት “የሕዝብ ሱናሚ” እያለ ሲምል ሲገዘት የነበረው ህወሃት ሱናሚው ወደ እርሱ እየጎረፈ ሲመጣ በረገገ፡፡ መፍትሔ በጠብመንጃ አፈሙዝና በብረት ብቻ እንደሆነ የሚያምነው ህወሃት በረሃ የለመደውን በትሩን አነሳ፤ ንጹሃንን ጨፈጨፈ፤ ደም አፈሰሰ፤ ኢትዮጵያን ወደ እስርቤትነት ቀየራት፡፡ ትዕዛዙን በቀጥታ የሰጡት “ባለራዕዩ” ለፍርድ ሳይቀርቡ “እንደጀመርን እንጨርሰዋለን” ያሉትን ሰፊውን ሕዝብ ሳይጨርሱት እንደ ክዳን ቆርኪ ተስፈነጠሩት፤ ላይመለሱ ሄዱ፡፡

የዛሬ አስር ዓመት የቅንጅት አካሄድ ያስፈራው ህወሃት ጉዳዩን ለራሱ ለፓርቲውና ለሕዝብ ከመስጠት ይልቅ ደም መቃባት ውስጥ ገባ፡፡ ፓርቲው የነበረበት የውስጥ ችግር እንዳለ ሆኖ የፈሪ በትር የዘረጋው ህወሃት የገደለውን ገድሎ ከጨረሰ እና የኢትዮጵያን መሬት በደምና በእናቶች እምባ እንደገና ካጨቀየ በኋላ ቅንጅትን የማፍረስ ተግባሩን በዕቅድ ይዞ በይፋ መንቀሳቀስ ጀመረ፡፡ ግምባር ቀደም ተሰላፊው የተቋም ባንዳ “ምርጫ ቦርድን”፤ በግለሰብ ደረጃ ደግሞ በተለይ ሁለት ግለሰቦችን አሰለፈ፡፡ ዘመቻ “ቅንጅትን መግደል” ተጀመረ፡፡

በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ ምንም በማያሻማ ሁኔታ በኢትዮጵያ የቀድሞ የአሜሪካ አምባሳደር የነበሩት ዶናልድ ያማሞቶ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር (ስቴት ዲፓርትመንት) ለሚገኙት አለቆቻቸው “THE ETHIOPIAN GOVERNMENT CHEWS THE CUD” (የኢትዮጵያ መንግሥት ቅንጅትን አኘከው) በሚል ርዕስ የጻፉት እንዲህ ይነበባል፤

Over the course of the week of January 7, the National Electoral Board of Ethiopia (NEB) hammered what appear to be the final nails in the coffin of the opposition Coalition for Unity and Democracy (CUD) party. Since their surprise showing in the 2005 elections, gaining enough seats to become the second largest political party in Ethiopia, the CUD has virtually disintegrated as a result of internal power struggles and interference from the Ethiopian Government (GoE). In the latest setback, the NEB awarded the famous victory sign — the CUD symbol widely recognized by voters — to former ally turned foe, Lidetu Ayalew of the United Ethiopian Democratic Party-Medhin (UEDP-Medhin).  The NEB followed this later in the week by finally awarding registration of the reformed Coalition for Unity and Democracy Party (CUDP) party name to yet another former CUD ally turned foe Addis Ababa city council member-elect Ayele Chamisso.  Though Ayele, who is broadly viewed as having been co-opt by the GoE, has invited all faction of the former CUD to join his party, few will likely take his offer.

In a meeting with Ambassador on January 11, NEB board chairman Dr. Merga Bekana and vice-chairman Dr. Addisu Gebre-Egziabhier said that the Board still had not decided on the CUDP’s registration and would continue to consider the matter in coming weeks. Almost immediately following the meeting, however, the NEB publicly announced that it had decided that morning to award the party license to Ayele. This followed their controversial decision earlier in the week to give the CUD’s famous victory symbol to the CUD’s despised adversary Lidetu Ayalew (another person believed to have been co-opted by the GoE during the CUD’s post-2005 election struggles), and his UEDP-Medhin party.

The opposition fiercely accused the NEB of being under the influence of the GoE and of delivering votes to the ruling Ethiopian Peoples Revolutionary Democratic Forces (EPRDF) party after the opposition’s surprisingly strong showing. Since then, a new Board has been put in place, but the opposition have not altered their criticism. The NEB’s recent decisions to award the CUD party symbol and name to politicians, who are at best undeserved and at worst proxies of the GoE, has done much to reignite lingering suspicions regarding the NEB’s independence. As if to prove these suspicions, NEB vice-chairman Dr. Addisu (a Tigrayan political scientist widely believed to be the “enforcer” at the NEB) recently commented to USAID’s Senior Democracy Advisor — a former Stanford University Political Science Professor ) (strictly protect) that the NEB had decided to “kill the CUD.” The NEB decisions of the last week have effectively done exactly that.

ትርጉም

በጃኑዋሪ 7 ሳምንት ወቅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ (ቅንጅት) ፓርቲ የሬሣ ሳጥን ላይ የመጨረሻ የሚባለውን ሚስማር መትቷል፡፡ በ2005 (1997) ምርጫ በአገሪቱ ሁለተኛው ትልቁ የተቃዋሚ ፓርቲ ለመሆን የሚያስችለውን አስደናቂ ድልና በቂ መቀመጫ ካገኘ በኋላ ቅንጅት በውስጡ በነበረው የኃይል (የሥልጣን) ሽኩቻና ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ይደርስበት በነበረው ጣልቃ ገብነት ምክንያት አለሁ ቢልም እየተፈረካከሰ ነበር፡፡ በቅርቡ በተደቀነበት ሌላ ደንቃራ ደግሞ ምርጫ ቦርድ ዝነኛውንና በብዙሃን መራጭ ዘንድ ዕውቅና የነበረውን የቅንጅትን (V) ምልክት ቀድሞ (የቅንጅት) ወዳጅ በኋላ ጠላት ለሆነው የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ፓርቲ – ኢዴፓ-መድህን ልደቱ አያሌው ሸልሞታል፡፡ በመቀጠልም ምርጫ ቦርድ ይህንን ተከትሎ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ የስም ምዝገባ ቀድሞ የቅንጅት ወዳጅ በኋላ ጠላት ለሆነው የአዲስ አበባ ምክርቤት እጩ ተመራጭ አየለ ጫሚሶ ሸልሞታል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ቅጥረኛ እንደሆነ በሰፊው የሚታመነው አየለ ጫሚሶ ከቀድሞው ቅንጅት ተሸራርፈው ለወጡት ሁሉ የእርሱን ፓርቲ እንዲቀላቀሉ ጥሪ ቢደርግም ጥቂቶች ብቻ ጥሪውን
አዲሱ ገብረእግዚአብሔር
ይቀበላሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ . . .addisu  g of neb

የምርጫ ቦርድ ሊቀመንበር ዶ/ር መርጋ በቃና እና ምክትል ሊቀመንበሩ ዶ/ር አዲሱ ገብረእግዚአብሔርከአምባሳደሩ (ያማሞቶ) ጋር ጃኑዋሪ 11 ቀን ባደረጉት ስብሰባ የቅንጅትን ምዝገባ በተመለከተ ገና ውሳኔ ላይ እንዳልደረሱ እና በመጪዎቹ ሳምንታት ጉዳዩን እንደሚመለከቱት ነበር የተናገሩት፡፡ ነገር ግን ወዲያውኑ ስብሰባው እንዳበቃ ማለት ይቻላል የዚያኑ ቀን ጠዋት የቅንጅትን የስም ምዝገባ ለአየለ ለመስጠት መወሰኑን ምርጫ ቦርድ ለሕዝብ ይፋ አደረገ፡፡ ይህ የቦርዱ ውሳኔ በሳምንቱ መጀመሪያ አካባቢ የቅንጅትን ዝነኛ (V) ምልክት በቅንጅቶች ለተናቀውና የፓርቲው ጠላት ለሆነው ልደቱ አያሌውና ለኢዴፓ-መድህን ፓርቲው ለመሸለም የተደረገውን አከራካሪ ውሳኔ ተከትሎ ነው፡፡ (ልደቱ አያሌው ከምርጫ 1997 በኋላ ቅንጅት ውስጥ በነበረው ትግል ውስጥ በኢትዮጵያ መንግሥት የተመደበ ሌላው ቅጥረኛ እንደሆነ ይታመናል)፡፡ . . .

ምርጫ ቦርድ በኢትዮጵያ መንግሥት ሥር እንደሆነ እና ተቃዋሚዎች አስገራሚ ውጤት በምርጫው ላይ ካሳዩ በኋላ (የመራጮችን) ድምጽ ለኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢህአዴግ) እንዳስረከበ ተቃዋሚ (ፓርቲዎች) አጥብቀው ይከስሳሉ፡፡ ከዚያ ወዲህ አዲስ ቦርድ የተሰየመ ቢሆንም ተቃዋሚዎች ግን አሁንም ትችታቸውን አላቆሙም፡፡ የቅንጅትን ስም እና ምልክት ፍጹም ለማይገባቸውና ለኢትዮጵያ መንግሥት የቅርብ ወዳጆች ለሆኑት ፖለቲከኞች ማስረከቡ ምርጫ ቦርድ ከአድልዎ የነጻ አለመሆኑ ላይ ያሉትን ጥርጣሬዎች እንደገና እንዲቀጣጠል አድርጓል፡፡ የምርጫ ቦርድ ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር አዲሱ በቅርቡ ለዩኤስኤይድ ከፍተኛ የዴሞክራሲ አማካሪና የቀድሞ የስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ ፕሮፌሰር (ስሙ እንዳይወጣ በጥብቅ የተከለከለ) ምርጫ ቦርድ “ቅንጅትን ለመግደል” ወስኖ እንደነበር መናገሩ እነዚህን ጥርጣሬዎች እርግጠኛ ያደርጋቸዋል፡፡ (የአዲግራት ተወላጅ የሆነው) (ዶ/ር አዲሱ የትግሬ የፖለቲካ ሳይቲስት ሲሆን የምርጫ ቦርድ “ፈጣሪና አድራጊ” እንደሆነ በሰፊው ይታመናል)፡፡ ባለፈው ሳምንት ምርጫ ቦርድ የወሰደው ውሳኔ (የቅንጅትን ስምና ምልክት ለቅጥረኞቹ መስጠቱ) ይህንኑ (ቅንጅትን የመግደሉን ዕቅድ) የሚያረጋግጥ ነው፡፡ . . . (ሹልክዓምድ (ዊኪሊክስ) ላይ የወጣውን ሙሉ መረጃ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

አሁንስ ማነው ባለሳምንት? በዚህኛው የምርጫ ድራማ አየለ ጫሚሶን የሚጫወተው ትዕግስቱ አወል እንደሆነ ይፋ ሆኗል፤ ልደቱንስ ማን ይተውነዋል?

ከዚህ በፊት በሰማያዊና በሌሎች ፓርቲዎች ላይ የደረሰውና አሁንም እየደረሰ ያለው እንዲሁም ሰሞኑን በአንድነት ፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች ላይ የደረሰው ሰቆቃ የዘንድሮውን ሁኔታ የተለየ እያደረገው እንደሆነ ጎልጉል ከተለያዩ ምንጮች የሚደርሱት መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ስለዚህም ነው “ምርጫ ቦርድ” ቅንጅትን በዕቅድ እንደገደለው አሁንም አንድነትንና ሌሎቹን ተቀናቃኞች “አኝኮ ለመግደል” ውሳኔው የሆነው፡፡

ከሕዝብ በኩል የሚሰማው የሰላማዊ ትግል ቁርጠኝነት ግን የህወሃትን የልመና ኮሮጆ በሚሞሉት ምዕራባውያንም ዘንድ ትልቅ ትኩረት የተሰጠው እንደሆነ ጎልጉል የደረሰው መረጃ ያመለክታል፡፡ የአንድነት ፓርቲ ሰልፍ በተካሄደበት ወቅት በተለያዩ የማኅበራዊ ገጾች ላይ ተሰራጭቶ ያገኘነውን መረጃ መጥቀሱ የቁርጠኝነቱን መጠን በተወሰነ መልኩ የሚያመለክት ነው፡፡ “በዕለቱ የደረሰበትን ጉዳት አስመልክቶ ለቢቢኤን ሬዲዮ የተናገረው የአዲስ አበባ ወጣቶች ጉዳይ አንድነት ፓርቲ ኃላፊ ስንታየሁ ቁስሉ ሳይደርቅ በወኔ እንዲህ ነበር ያለው “ወያኔ ላጠፋው ጥፋት የሚያወራርደው ሒሳብ እንዳለ ማወቅ አለበት፡፡ ለትግላችን እንሰዋለን፤ በዋዛ አንላቀቅም”፡፡

Freitag, 30. Januar 2015

ESAT Breaking News, UDJ and AEUP Jan 30 2015 | ESATTUBE

ESAT Breaking News, UDJ and AEUP Jan 30 2015 | ESATTUBE

የሕወሃት ታጥቂዎች የአንድነት ፓርቲን ጽ/ቤት በኋይል ተቆጣጥረዉታል።

የሕወሃት ታጥቂዎች የአንድነት ፓርቲን ጽ/ቤት በኋይል ተቆጣጥረዉታል። ጥዋት ሥራ አስፈጻሚው ስብሰባ አደረጎ የነበረ ሲሆን፣ ከሰዓት በኋላ ምክር ቤት ሊሰበሰብ ታስቦ የነበረ ቢሆን፣ ደህንነቶች ጽ/ቤቱን ከበው ማስገባትና ማስወጣት ስላልተችለ፣ የምክር ቤቱ ስብሰባ ሳይደረግ ቀርቷል። ሆኖም የሥራ አስፈጻሚው ጠዋት ባደረገው ዉስኔዎችን አስተላልፏል። የመጀመሪያ ዉሳኔ በአገሪቷ ክፍል ያሉ የንድነት አባላትና ደግፊዎች በሕወሃት ለተቋቋመው ተለጣፊ ቡድን ምንም ኣይነት እውቅና እንዳይሰጡና እንዳይደገፉ ጥሪ አቀርበዋል። የሥራ አስፈጻሚው በአዲስ ስም መንቀሳቀሱ፣ ሕወሃት ተመሳሳይ እርምጃ እንዳይወሰድ የማያከላክለው በመሆኑ፣ መሰረታዊ የዲሞክራሲ ተቋማት ለዉጥ በሌለበት መልኩ አዲስ ስም አወጥቶ እንደገና መንቀሳቀስ ዋጋ እንደሌለው ገልጸዋል። ሌሎች ድርጅቶችን መቀላቀሉ በተመለከተ ያ የአባላት የግል ዉሳኔ እንደሆነ አስረድተው፣ ነገር ግን እንደ አንድነት ሥራ አስፈጻሚ ወደ ሌል ድርጅት ቢቀላቀሉም፣ አገዝዙ ተመሣሳይ እርምጃ በተቀላቀሉት ድርጅት ላይ ሊወስድ እንደሚችል አስረድተዋል።

የተበላው እቁብ (ምርጫ 2007) እና እኔ ባይተዋሩ…


አቤንኤዘር ጀምበሩ ((አዲስ አበባ)

ጥር 11/07 ዓም ቦታው አፍንጮ በር፣ ከዩሀንስ፣ ከጊዬርጊስ እና ቀጨኔ መድሃኒያለም ታቦቶች ለከተራ ወደ ጃንሜዳ ሲተሙ የሚጋጠሙበት ቦታ። እልልታው ፣ጭፈራው፣ መዝሙሩ ፣ የሐገር ባህል ልብስ፣ ዱላ ፣ሸንኮራ ፣ጠጠር መጣያ ከሌለው ህዝብ ጋር አብረው ሽኝቱን አድምቀውታል ። ከሁሉ ከሁሉ ድምጽ ግን ከጀርባዬ የቆሙ እናት ጮሆ ውስጥ ድረስ ዘልቆ ተሰማኝ ። መቼ ነው ምልጃ እና አግዚኦታ የሚያልቀው? “አምላኬ ወጣቶችን ጠብቅ፣ ምርጫውን በሰላም አጠናቀው ፣ደም መፍሰስን አንተ በቃ በል ፣ ልጆቻችንን ጠብቅ፣ ተለመነን … ” ፣ ሁሉ አንቅስቃሴ ፣ ሁሉ አዲስ ነገር ፣ ሁሉ አዲስ ሐሳብ የስጋት ምንጭ እንደምን ይሆናል? ስጋትን ወደ መልካም አጋጣሚነት መቀየር አይቻልም?
ethiopian election 2015
የቤታችን በር በአማካኝ ሶስት ጊዜ ትንኳኳለች፣ ሰሞኑን አህዟን በእጥፍ አሳድጋ ስድስት ጊዜ መንኳኳት ጀምራለች። ምክንያት ብትሉ ያካባቢያችን ምርጫ አስፈፃሚዎች “ካርድ ወሰዳችሁ፣ ውሰዱ ፣ማን አልወሰደም ፣ መቼ ተወሰደ …” እያሉ ይመጣሉ። ለመምረጥ ካለኝ ጉጉት ሳይሆን መልካም ዜጋነቴን ለማስመስከር ወደ ምርጫ ጣቢያ ሄድኩ ። አሁንም እንደ ጥንቱ ቁራጭ ካርድ ፣ መዝገብ ፣ እስክሪፕቶ የሃገራችን የምርጫ ቴክኖሎጂ? ምርጫው ሲመጣ ደግሞ ባምስት አመት የሚራገፉ ቀዳዳዎች የበዙበት የሸራ ኮሮጆ። በቢሊዬን ህዝብ ያላት ሕንድን ጨምሮ ብዙ የአፍሪካን ሐገራት የምርጫ ቴክኖሎጂን ምርጫን ለማቀላጠፍ ሲጠቀሙ ፣ እኛ ሐገር ስማችንን እንኳን በኮምፒውተር መመዝገብ እንደምን ተሳናቸው?ስራ አጥተው የተቀመጡ ባለ ዲግሪ ወጣቶች ድንጋይ ፍለጡ እየተባለ ፣የትምህርት ደረጃቸው በአብዛኛው ከሁለተኛ ደረጃ ያልዘለሉ የሰፈር ፊትአውራሪዎች ለምን ዋና ተዋንያን ሆኑ? ካርድ ለመውሰድ በሄድኩበት ወቅት በአካባቢያችን የማውቃቸው እናቶች ፣ ፕሮፌሽናል ያልሆኑ የመንግስት ሰራተኞች፣ የቀበሌ ሰራተኞች ተሰብስበዋል (በእርግጥ አንዳንዶቹን አይቼያቸው ስለማላውቅ ማን እንደሆኑ አላውቅም) ። ከመሃላቸው አንዷ ቡና ታፈላለች። በወቅቱ ቦታው ስደርስ የሞቀ ሰላምታ ሰጥተው በፍጥነት አስተናገዱኝ፣ ስወጣ ገለፃ እንደተሰጠብኝ እገምታለሁ ።
የሰሞኗ የአዲሳቤዎች ቀልድ ታዲያ ቀልቤን ስባዋለች። የኢትዮጵያ ፣ የራሺያና የአሜሪካ ልኡካን ስለ ምርጫ ውጤት ልምድ ሲለዋወጡ፣ የራሽያው ልኡክ “እኛ ሐገር ምርጫ በተደረገ በአንድ ቀን ውስጥ ውጤቱ ይታወቃል” አለ። አሜሪካዊው ለጠቅ አድርጎ “ይህማ ዘግይቷል የኛ ከ3–6 ሰአት ውስጥ ” አለ። የኛው ቀበል አድርጎ “የኛ ከሁላችሁም የተሻለ ነው፣ ውጤቱ ከምርጫው በፊት ነው የሚታወቀው ” ብሎ አረፈው (lol)። እናም አሁን ላይ ምርጫው በሰላም ይለቅ ሲባል በቅንፍ ገዥው ፓርቲ ያለግርግር ያሸንፍ እንደማለት ይመስለኛል። እንደሚያሸንፉ የተማመኑት ገዥዎቻችን የቀጣይ አምስት አመት እቅድ መንደፍ ይዘዋል። የተበላ አቁብ ማለት ይህ አይደል ታዲያ?
እናም እላለሁ መንግስት በአንፃራዊ የተሻሉትን ተቃዋሚዎች ተከፋፈሉ እያለ ጊዜ እየገዛባቸው እንደሆነ ይሰማኛል። ችግራቸውም ጊዜው ሲደርስ ይፈታል።ግን በፊት ያልነበረ ክፍፍል ከየት መጣ?፣ የእጩ ማቅረቢያ ጊዜ ለምን ተራዘመ? ከኋላው የፓለቲካ ቁማር መኖሩ አያጠራጥርም። ምርጫው ጥቂት ወራቶች ቀርተውት እንኳን እኛ አዲሳቤዎች በሙሉ አፋችን የተቃዋሚ ፓርቲ ስም አንጠራም (በእርግጥ እነሱም የት እንዳሉ አይታወቅም) ፣ ብንጠራም ግራ ቀኛችንን አይተን ነው። ክርክር የለም፣ የሐሳብ ልውውጥ የለም፣ አማራጭ የለም፣ አዋጪ መንገዶች ዝርዝር የለም። ያለው ስጋት እና የምርጫ ቦርድ ሪፓርቶች። እውን ይሄ የማን ሌጋሲ ይሆን?

አብዮት መንታ ነው (ሄኖክ ታደሰ ጆሃንስበርግ)

revolution
“የአብዮት ያለህ!”፥ አትበሉ ባ’ገሬ፣
በአብዮት መሃል፥ አብዮት አይጠሬ፣
ምስጋና ቢስ ትውልድ፥ ሆነነው ነው እንጂ፣
የግፈኛን ቀብር፥ የምናበጃጅ፣
የሚሞቱልንን፥ የደም ዋጋ ንቀን፣
በአብዮት መሃል፥ ካ’ብዮት ርቀን፣
በአርበኞች መሃል፥ ባ’ርበኝነት ስቀን…
“ደሃ ህዝብ አስፈጁ”፥ ስንል ተሰምተናል፣
“አመሉ ሲታወቅ”፥ ብለን አድንቀናል፣
‘ያስፈጀው’ ሲወገዝ፥ ፈጂውን ትተናል፣
አህያ እየፈራን፥ ዳውላ መ’ተናል።
ልንገርህ ወገኔ፥
አብዮት ሁለት ነው፥ መንታ ነው ፍጥረቱ፣
እርግጥም አብዮት፥ ስም ያገኘበቱ፣
በዳዮችን ሲጥል፥ ስርአት ሲዘረጋ፣
ሙሉ ሥም ያገኛል፥ አቢዮት እዚህጋ።
ነገር ግን ሲመታ፥ በበዳይ ፍላጻ፣
አቢዮት ተሽሮ፥ ይባላል አመጻ።
“አብዮት የለም” አንበል፥ አብዮት አለን እኛ፣
ግዞት ቤቱ የሞላው፥ በአብዮተኛ።
“There are accepted revolutions, revolutions which are called revolutions; there are refused revolutions, which are called riots.” — Les Miserables/ Victor Hugo

Donnerstag, 29. Januar 2015

የሰላም በሮች ሲዘጉ የሁለገብ ትግል ስልት በሮች ይከፈታሉ! (አርበኞች ግንቦት7)


Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy
አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ አማካይነት እየደረሰበት ያለውን በደል ለሕዝብ ለማሰማት ጥር 17 ቀን 2007 ዓም በአዲስ አበባ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ጂንካና ሸዋ ሮቢት የተቃውሞ ሰልፎችን ጠርቶ ነበር። በተለይ በአዲስ አበባው ሰልፍ ላይ የተገኙ ወገኖቻችን ለህወሓት ፍጹም ታማኝ በሆነው የፓሊስ ክፍል ያለርህራሄ መደብደባቸው እና የተቃውሞ ሰልፉም በጉልበት መበተኑ ነፃነትና ፍትህ ናፋቂውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ያሳዘነ ብቻ ሳይሆነ ያስቆጨ ጉዳይ ነው። በመላው ዓለም በሚደረጉ የተቃውሞ ሰልፎች ላይ የተለመደውን ድንጋይ ውርወራ እንኳን ሳይከጅሉ፤ የፓሊሶችን ሰብዓዊ ርህራሄ ለማግኘት “ፓሊስ የኛ ነው” እያሉ እየዘመሩ በፓሊስ ተደበደቡ። ሴቶችና አዛውንት ብቻ ሳይሆን ተላላፊ መንገደኞች እንኳን ከፓሊስ ዱላ አላመለጡም። ከሁሉም በላይ የሚዘገንነው ደግሞ የ 7 ወራት ነብሰ ጡር ሴትም በፓሊስ መመታትዋና ሆዷ መረገጡ ነው። ይህ እኩይ ተግባር የሚፈጥረው ቁጭት በህወሓት ላይ ብቻ አያበቃም። ትዝብቱ ለፓሊስም ተርፏል። ይህ የጭካኔ ተግባር ለፍትህና ለነፃነት በሚደረገው ትግል የሕዝብ አጋር ይሆናል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት የፓሊስ ሠራዊትን የሚያዋርድ ነው። ደካማ እናቶችን፣ አረጋዊያንን፣ ባዶ እጃቸውን ተቃውሞ እያሰሙ ያሉትን ወጣቶችንና ነፍሰጡሮችን በጭካኔ መደብደብ ለራሱና ለሥራው ክብር ለሚሰማው ፓሊስ ውርደት ነው፤ የሞት ሞት ነው። የኢትዮጵያ የፓሊስ ሠራዊት አባላት ተግባራቸው ያሳፍራቸዋል፣ ይቆጫቸዋል፤ ቁጭታቸውንም ይህን ትዕዛዝ በሰጡ አለቆቻቸው ላይ በግልም ሆነ በተደራጀ መንገድ በሚወስዱት እርምጃ እናያለን ብሎ የኢትዮጵያ ሕዝብ ተስፋ ያደርጋል።
የጥር 17 ቀን 2007ቱ ሽብር በአንድ ወቅት የተፈጠረ፤ በአንድነት ፓርቲ ላይ ብቻ ያነጣጠረ፣ የተናጠል ክስተት ሳይሆን ህወሓት ደግሞ ደጋግሞ ሲፈጽመው የነበረ ነው። ከዚህ በፊት በሙስሊም ወገኖቻችን ላይ ፈጽሞታል። የአዲስ አበባ ከተማ ማስተር ፕላንን በተቃወሙ የተለያዩ ዩንቨርስቲዎች ተማሪዎች በተለይም በአምቦ ላይ የብዙዎችን ሕይወት የቀጠፈ ሽብር ነዝቷል። በቅርቡ ደግሞ በሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ ተመሳሳይ አረመናዊ ድርጊት ፈጽሟል።
አርበኞች ግንቦት 7: ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ የህወሓት ታጣቂዎች በወገኖቻችን ላይ ያደረሱትን ድብደባ፣ ህገወጥ እስር፣ እና የተቃውሞ ሰልፍ ክልከላን አጥብቆ ይቃወማል። አርበኞች ግንቦት 7፣ በወገኖቻችን ላይ የደረሰው ህመም ህመሙ፣ ቁስላቸው ቁስሉ ነው።
ባለፉት ሃያ ሶስት ተከታታይ ዓመታት፣ በአምቦ፣ በጅማና በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞችና ገጠሮች፣ በባህዳር፣በጎንደርና በበርካታ የአማራ ከተሞችና ገጠሮች፣ በጋምቤላ፣ በሶማሊ፣ በአፋር፤ በአጠቃላይ በመላው ኢትዮጵያ በየአስፋልቱ፣ በየሜዳውና በየጥሻው በህወሓትና ተላላኪዎቻቸው የፈሰሰው የኢትዮጵያውያን ደም በከንቱ ፈሶ መቅረት የለበትም ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 በጽኑ ያምናል። አርበኞች ግንቦት 7 ከሌሎች መሰል ድርጅቶች ጋር በመተባበር የህወሓትን እድሜ በማሳጠር የእናቶቻችን እምባ ሊያብስ ዝግጁ ነው። አርበኞች ግንቦት 7 ኢትዮጵዊያን እንደከብት እየተደበደቡ ወደ ማጎሪያ የሚያጋዙበት እና በጠገቡ ሰላዮችና ፓሊሶች እየታነቁ የሚታረዱበት ጊዜ ማብቃት አለበት ይላል።
የቱን ያህል ቢለመንም ሆነ ቢወገዝ ህወሓት ለነፃ፣ ፍትሃዊና ተዓማኒን ምርጫ ዝግጁ ሊሆን ቀርቶ በምርጫ የሚወዳደሩት ፓርቲዎች እነማን እንደሆኑና እነማን በእጩ ተወዳደሪነት መቅረብ እንዳለባቸው ሳይቀር የሚወስን ዓይን አውጣ አጭበርባሪ ድርጅት ነው። ይህንን ከዚህ በፊት አይተነዋል፤ አሁንም በአንድነትና በመኢአድ ላይ እየተደገመ ነው። ህወሓት፣ በየአምስቱ ዓመታቱ በሚያደርጋቸው የሴራ ምርጫዎች በሚቀጥሉት አርባና ከዚያም በላይ ለሆኑ ዓመታት በሥልጣን ላይ የሚቆይበትን ስልት ቀይሶ የሚንቀሳቀስ፤ ኢትዮጵያን ለብዙ ዓመታት ለመግዛት ማድረግ የሚችለውን ክፋት ሁሉ ከማድረግ የማይመለስ አገር በቀል ቅኝ ገዥ ነው። ህወሓት የዘረጋው ሥርዓት ህገ-አልባነት፣ ፀረ-ሕዝብነት እና አምባገንነት ለማጋለጥ በሚል ርህራሄን በማያውቁ የሥርዓቱ አገልጋዮች ፊት ባዶ እጅ መጋፈጥ የሚፈጥረው የሞራል የበላይነትና የመንፈስ ጀግንነት ባያጠራጥርም የሚያስከፍለው ዋጋ ከሚገኘው ውጤት ጋር ማመዛዘን ግን እጅግ ተገቢ የሆነ የማይታለፍ ሥራ ነው ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ያምናል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ከህወሓት የሴራ ምርጫ ፋይዳ ያለው ውጤት ይገኛል ብሎ አይጠብቅም። ከምርጫው የሚፈልገው ውጤት አንድ ነገር ብቻ ነው፤ እሱም የመንግሥት ለውጥ ነው። ምርጫው በምርጫነቱ ወደ መንግሥት ለውጥ አያደርስም፤ ወደ መንግሥት ለውጥ ወደሚያመራ ሕዝባዊ አብዮት ሊያሸጋግር ግን ይችላል። ይህም ቢሆን የኢትዮጵያን ተጨባጭ ሁኔታ በተለይም የሠራዊቱን ዓይነትና አደራጀጀት እግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ መታቀድ ይኖርበታል።
አርበኞች ግንቦት 7 የራሱን ጥናት አድርጎ ለኛ አገር ተጨባጭ ሁኔታ እና ህወሓትን ለመሰለ ጠላት የሚመጥን የትግል ስልት ሁሉንም የትግል ስልቶች እንደሁኔታው ያዳቀለ – ሁለገብ – መሆን ይኖርበታል ብሎ ወስኖ ለተግባራዊነቱ እየተንቀሳቀሰ ነው። ሁለገብ የትግል ስልት ሕዝባዊ ተቃውሞን፣ ሕዝባዊ እምቢተኝነትንና ሕዝባዊ አመጽን እንደወቅቱ ተጨባጭ ሁኔታ ማፈራረቅና ማደባለቅን ይፈልጋል። ሰላማዊ ትግል በተለይም ሕዝባዊ እምቢተኝነት ሲባል ደግሞ ህወሓት ያወጣቸው አፋኝ ህጎች እያከበሩ የሚደረግ አለመሆኑም የኢትዮጵያ ሕዝብ ይረዳል። ሁለገብ ትግል በተቻለ መጠን የወገን ኃይል ራሱን ፈጽሞ መከላከል በማይችልበት ሁኔታ እንዳይገኝ ለማድረግ ይጥራል። በአርበኞች ግንቦት 7 እምነት ሁለገብ የትግል ስልት ሰፊ ተቀባይነት የሚያገኝበት ወቅት ደርሷል። ከዚህ በፊት “የሰላም በሮች ሲዘጉ የአመጽ በሮች ይከፈታሉ” ተብሎ በአንድ ታዋቂ ኢትዮጵያዊ ታጋይ የተነገረው “የሰላም በሮች ሲዘጉ የሁለገብ ትግል ስልት በሮች ይከፈታሉ” በሚል እንዲሻሻልና በዚህ ወለል ብሎ በተከፈተው በር ሁላችንም እንድንገባ አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል። በሁለገብ የትግል ስልት በሰላማዊ መንገድ የሚደረጉ የትግል ዓይነቶች አሉ፤ በሌላም መንገድ የሚደረጉ አሉ። ስለሆነም በሁለገብ ትግል እያንዳንዳችን እንደየዝንባሌዓችንና እንደየችሎታዎቻችን አስተዋጽኦ ልናበረክት የምንችልበት ሰፊ እድል ይከፍትልናል።
ስለሆነም፣ በዚህ አጋጣሚ አርበኞች ግንቦት 7፣ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለጦር ሠራዊትና ፓሊስ አባላት ወገናዊ ጥሪ ያደርጋል።
በህወሓት ዘረኛ አገዛዝ በሚደርስብን ውርደት፣ እንግልት፣ ስደት፣ ሥራ አጥነትና ድህነት የተማረራችሁ እና እኩልነቷ የተረጋገጠ፣ የበለፀገች ኢትዮጵያን ማየት የምትመኙ ሁሉ የሁለገብ የትግል ስልትን አዋጪነት እንድታጤኑ የዚሁ ስልት አካል ሆናችሁ እንድትታገሉ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።
የኢትዮጵያ የጦርና የፓሊስ ሠራዊት አባላት በግል ከሚደርስባችሁ ግፍ በተጨማሪ የገዛ ራሳችሁን ወገኖች መግደላችሁ፣ ማቁሰላችሁ፣ ማድማታችሁና መደብደባችሁ የህሊና እረፍት ሊነሳችሁ ይገባል። ህሊናችሁ እረፍት የሚያገኘው የሥርዓቱ እድሜ ሲያጥር መሆኑን በመገንዘብ ለገዛ ራሳችሁ ክብር፣ ለወገናችሁና ለአገራችሁ ስትሉ ፋሽስቱን ወያኔ ከድታችሁ ከአርበኞች ግንቦት 7 ኃይል ጋር ተቀላቀሉ።
እነዚህን ጥሪዎች ተግባራዊ ካደረግን ወገኖቻችን መሠረታዊ መብቶቻቸውን በመጠየቃቸው በመወደስ ፋንታ በፓሊስ ዱላ ሲደበደቡ የማናይበት ዘመን ይመጣል። ይህ ካልሆነ ግን “ውሀና መብራት አጣን” ብሎ አቤቱታ ማሰማት እንኳን በጥይት የሚያስገድልበት ቀን ይመጣል። ያ ከመሆኑ በፊት እንወስን፤ ራሳችንና አገራችን ከህወሓት ዘረኛ አገዛዝ ነፃ እናውጣ።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Mittwoch, 28. Januar 2015

ጋዜጠኞችና ጦማርያኑ ለጥር 26 ቀጠሮ ተሰጠባቸው። ∙ፍርድ ቤቱ ተሻሻለ በተባለው ክስ ላይ ብይን ሰጥቷል


∙ፍርድ ቤቱ ተሻሻለ በተባለው ክስ ላይ ብይን ሰጥቷል
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
የዞን ዘጠኝ ጦማርያንና ጋዜጠኞች ዛሬ ጥር 20 ቀን 2007 ዓ.ም ለ16ኛ ጊዜ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ ቀደም ብሎ ተሻሻለ የተባለውን ክስ አይቶ ብይን ሰጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት ከአራቱ ነጥቦች መካከል አንዱን ብቻ ውድቅ ሲያደርግ ሦስቱን እንደተሻሻሉ ቆጥሮ በክሱ ውስጥ እንደተካተቱ እንዲቀጥሉ በብይኑ አመልክቷል፡፡ 
ፍርድ ቤቱ በአቃቤ ህግ የክስ ማሻሻያ ላይ የሰጠውን ብይን በንባብ አሰምቷል፡፡ በዚህ መሰረት የፌደራል አቃቤ ህግ አሻሽየዋለሁ ያለውን ክስ ከአንዱ ነጥብ በስተቀር ቀሪዎቹ ሦስት ነጥቦች ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት አቃቤ ህግ አሻሽሏል በሚል ፍርድ ቤቱ በቀበሉን በብይኑ አመልክቷል፡፡ 
ስለሆነም በክሱ ላይ የተጠቀሰው የተከሳሾች የስራ ክፍፍል አለ በሚል የቀረበው ነጥብ ብቻ በአቃቤ ህግ እንዳልተሻሻለ በመውሰድ ፍርድ ቤቱ ውድቅ ሲያደርገው ሌሎቹ ነጥቦች፣ ማለትም ‹ቡድን› በሚል የተጠቀሰው፣ የ48000 ብሩን ጉዳይ እንዲሁም ተከሳሾቹ ስልጠና መውሰዳቸውን የሚገልጸው ነጥቦችን ፍርድ ቤቱ እንደተሻሻሉ ቆጥሮ ተሻሻለ በተባለው ክስ ውስጥ እንዲካተቱ ብይን ሰጥቷል፡፡ 
በክሱ ላይ ‹ቡድን› በሚል የተጠቀሰው ነጥብ ተከሳሾቹ በህቡ ያቋቋሙት ቡድን መሆኑን ፍርድ ቤቱ ተገንዝቧል ያለው ችሎቱ፣ የቡድኑ አጠቃላይ ሁኔታ በቀጣዩ በክርክር ወቅት በማስረጃ የሚረጋገጥ አልያም ውድቅ ሊሆን የሚችል ስለሆነ በክሱ ላይ መካተቱ ተገቢነቱን ተቀብሎታል፡፡ 
ስልጠና መውሰድን በተመለከተም ‹‹ተከሳሾች ከ2004 ጀምሮ እጃቸው እስከተያዘበት ጊዜ ድረስ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት በግንቦት 7 አመቻችነት ስልጠና መውሰዳቸውን የተሻሻለው ክስ አስፍሯል፡፡ ስለሆነም ጊዜውና በማን የሚለው ስለተጠቀሰ ክሱ መሻሻሉን ፍርድ ቤቱ ተቀብሎታል›› በሚል ነጥቡ በክሱ ላይ እንዲካተት በይኗል፡፡ የ48 000 ብሩን በተመለከተ ደግሞ ‹‹ብሩን ውጭ ሀገር ከሚገኙ የቡድኑ አባላት መቀበላቸውን የተሻሻለው ክስ ስለሚጠቅስ›› በሚል እንደተሻሻለ አድርጎ ፍርድ ቤቱ መቀበሉን በብይኑ አመልክቷል፡፡
በመሆኑም ፍርድ ቤቱ የሰጠውን ብይን ተከትሎ ተከሳሾቹ ከጠበቆቻቸው ጋር ተመካክረው በክሱ ላይ ‹‹የእምነት ክህደት ቃል ይሰጡ ከሆነ›› ውሳኔያቸውን እንዲያሳውቁ አጭር ቀጠሮ በመፍቀድ በቀጣዩ ማክሰኞ (ጥር 26/2007 ዓ.ም) ችሎት እንዲቀርቡ ውሳኔ አስተላልፏል፡

በኢትዮጵያ መንግስት በጥብቅ የሚፈለጉ 3 አርቲስቶች

Kibebeew geda

ከሮቤል ሔኖክ
እንዳለመታደል ሆኖ ኢትዮጵያ ውስጥ ሃሳብን በነፃነት ያለመግለጽ መብት አለመከበሩ ያጠቃው ጋዜጠኞችን ብቻ አይደለም። አርቲስቶችም ጋዜጠኞች ከሚከፍሉት መስዋእትነት ያልተናነሰ ትግል እያደረጉ ይገኛሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳለመታደል ሆኖ የሃሳብን የመግለጽ ነጻነት በመገደቡ ዛሬ እንደ ታላቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙና ተመስገን ደሳለን ያሉ ጋዜጠኞች ያልሆነ ክስ ተልጠፎባቸው በእስር ላይ ይገኛሉ። የእነዚ ታላላቅ ጋዜጠኞች ‘ወንጀል’ መንግስት እንደሚለው ሳይሆን የሕዝብን በደልና ብሶት ማሰማታቸው ብቻ ነው።
ዛሬ ዛሬ ደግሞ ላለፉት 23 ዓመታት ሃሳባቸውን በነጻነት ከሚገልጹት ጋዜጠኞች ባልተናነሰ በመንግስት ጥርስ እየተነከሰባቸው የሚገኙት የጥበብ ባለሙያዎች እየሆኑ ነው።
እንደሚታወቀው በስደት ዓለም ከ150 በላይ ጋዜጠኞች እንዳሉ ሁሉ ዛሬ ቁጥራቸው በዛ ያሉ አርቲስቶችም በስደት ይህንን ስርዓት በመሸሽ በስደት ላይ ይገኛሉ። ከነዚህ መካከልም የኢትዮጵያ መንግስት እንደታላቁ እስክንድር ነጋ አስሮ ለማሰቃየት ከሚፈልጋቸው ታላላቅ አርቲስቶች መካከል 3ቱ ዋነኞቹ ሲሆኑ ሌሎቹ ሁለቱ ደግሞ ገና መንግስት እያጎበጎበባቸው በመሆኑ የ3ቱን ገድል አሳይቻችሁ የሁለቱን እንስት አርቲስቶችን ማንነት አስተዋውቃችኋለሁ።
1ኛ. ታማኝ በየነ
ብዙዎች እንደስሙ ነው ይሉታል። አክቲቪስት ሆኗል ከአርቲስትነቱ በተጨማሪ። አላሙዲ ካደረገለት በላይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያደረገልኝ ይበልጣል በሚል ዛሬም ድረስ የያዘውን አቋም ባለማዋዠቅ ይህን ተራ መንግስት ማንነቱን በማጋለጥ ላይ ይገኛል። በብዙ ኢትዮጵያውያን ዘንድ “የሕዝብ ልጅ” የሚል ስያሜ የተሰጠው ታማኝ በየነ አሁን በስልጣን ላይ ያለው አንባገነን ስርዓት ከዚህ አርቲስት ጎን ፎቶ የተነሳ፣ የታየ፣ ሻይ የጠጣ አሸባሪ ነው የሚል ክስ እንደሚመሰርት አስታውቋል። ታማኝ በየነ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ክብርን ያገኘ በመሆኑና ክብሩንም ለገንዘብም ይሁን ለታይታ ያልቀየረ በመሆኑ ብዙዎች የሚያከብሩት ሲሆን የሕወሓት መንግስት ይህን ታላቅ አርቲስት በቁጥጥሩ ስር ለማዋል የማፈነቅለው ድንጋይ የለም።
ታማኝ የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ሳይሆን በግሉ በሕዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን ግፍ በነፃነት እያጋለጠ ዘረኛውን ስርዓት እርቃኑን እያስቀረው ሲሆን በተለይም መንግስትን የሚያጋልጠው ራሳቸው የመንግስት ባለስልጣናት በሚሰጡት እርስ በእርሱ በሚጣረስ በቪድዮ የታጀበ ቃለምልል መሆኑ በብዙሃን ዘንድ ተወዳጅነትን በሥርዓቱ ዘንድ ደግሞ ለመታሰር ከሚፈለጉ 3ቱ አርቲስቶች መካከል አንዱ ሆኗል።
2ኛ. ፋሲል ደመወዝ
አርቲስት ፋሲል ደመወዝን የማውቀው አዲስ አበባ ስድስት ኪሎ የሚባል ሰፈር በተለምዶው ሸለቆ የሚባል አካባቢ ነው። በሸለቆ አካባቢ ሲራመዱ ፋሲል ሙዚቃ በመለማመድ ላይ እያለ የሚያሰማውን እንጉርጉሮ ማድመጥ የተለመደ ነው። ይህ ታላቅ ድምፃዊ የጎንደር መሬት ለሱዳን ተላልፎ በሕወሃት/ኢሕአዴግ መንግስት በተሰጠበት ወቅት “አረሱት” የሚል ዘፈን ካወጣ በኋላ በስር ዓቱ ሰዎች ወፌ ላላ ተገርፏል። ፋሲል ታዝሎ እስኪሄድ ድረስ በዚህ ፋሽስት መንግስት የተገረፈ ከመሆኑም በላይ የዳነው በህክምና ብቻ ሳይሆን በጸበልም ጭምር ነው።
ፋሲል ደመወዝ አሁን ሰሜን አሜሪካ ከመጣ በኋላ ‘እንቆልሽ” በሚለው አልበሙ ‘ያውላችሁ’ የሚል ዘፈን ያወጣ ሲሆን በዚህም ዘፈኑ ሃገሪቱን ካለምንም ተቀናቃኝ በአፓርታይድ ስርዓት ለሚመሩት ሰዎች “ሰው አስተዳደራችሁን እና በደላችሁን ጥሎ ጥሏችሁ እየሄደ ነው” ሲል ነግሯቸዋል። ፋሲል ደሞዝ በአሁኑ ሰዓት በሕወሓት አስተዳደር ከሚፈለጉ ዋና አርቲስቶች መካከል አንዱ ነው።
3ኛ. ክበበው ገዳ
ኮሜዲያን ነው። በጣም ይወደዳል። በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያም ይቀልዳል – ክበበው ገዳ። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ እሱን የሚያል ኮሜዲያን አለ ብሎ ለመናገርም ይከብዳል ይላሉ በሙያው ውስጥ ያሉ ሰዎች እና ባለሙያዎች። ክበበው ገዳ በማንኛውም ማህበራዊ ሕይወት ዙሪያ በመቀልድ ይታውቃል። ይህ ኮሜዲያን ከኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ በመመላለስ የተለያዩ የኮሜዲ ሥራዎችን አቅርቦ ተመልሷል። የዘንድሮው ግን ለጉድ ነው። የሥርዓቱን ሰዎች በእጅጉ እስቆትቷል።
ባለፈው ኦገስት 2014 ላይ ክበበው ገዳ በዳላስ የኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ በዓል አስተናጋጅነት ትልቅ በዓል ላይ ተገኝቶ ነበር። ይህ ኮሜዲያን አሁን ባለው የኢትዮጵያውያን ነባራዊ ሁኔታ ዙሪያ በርካታ ቀልዶችን አቀረበ። በተለይም አሁን ባለው ስርዓት ዙሪያ ልክ እዚህ ሰሜን አሜሪካ ኮሜዲያን በመሪዎቻቸው እንደሚቀልዱት ሁሉ ቀለደ። የሕዝቡን ብሶትም በቀልዱ አሰማ። ስለሟቹ ጠ/ሚ/ር፣ ስለሟቹ ፓትሪያሪክ፣ አሁን ስላለው የመንግስት አካሄድ በቀልድ አዋዝቶ አቀረበ። ለዚህ ኮሜዲያን ከሕዝብ የቀረበለት አድናቆትን ቢሆንም ከ ስርዓቱ ግን የቀረበለት ማስፈራሪያና ዛቻ ነው። እንደውም ‘ሃገርህ ትገባታለህ” የሚሉ ዛቻዎች ከስርዓቱ ደርሶታል። ክበበው ሙያውን ተጠቅሞ ባስተላለፈው መልዕክት ከኢትዮጵያ መንግስት ተላላኪዎች የሚደርስበት ማስፈራሪያ ሃገርህ ብትገባ አለቀልህ የሚል ብቻ ሳይሆን አሁን ባለበት ሃገር ሳይቀር እንደማይለቁት የሚገልጹ ናቸው።
ማነህ ባለሳምንት?
ሜሮን ጌትነትና አስቴር በዳኔ።

ሁለቱም ሴት አርቲስቶች ናቸው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚደርሰውን የሴት ልጅ ተጽ ዕኖ ተቋቁመው አደባባይ የወጡ ሴቶች። ሁለቱም ያመኑመትን ይናገራሉ። ሁለቱም በተለይ ሃገር ቤት ካሉ አርርቲስቶች የሚለዩበት ነገር አላቸው። እነዚህ አርቲስቶች ስለ እውነት እውነትን ስለመሰከሩ ዛሬ በ ሥ ር ዓቱ ሰዎች እየተነከሰባቸው ያለውን ነገር አብረን እያየነው ነው።

Dienstag, 27. Januar 2015

አቶ ትግስቱ አወሉ በአንድነት የክልል አመራሮች ላይ በስልክ ዛቻ እየፈፀሙ መሆኑ ተገለፀ፡፡


የአንድነት ፓርቲ ሰሞኑን በኢህአዲግና ምርጫ ቦርድ ከፍተኛ ዘመቻ ተከፍቶበት እንደሚገኝ መላው ኢትዮጵያዊ እየተከታተለው ያለ እውነታ ነው፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ከምርጫ ቦርድ ጋር በመሆን አንድነት ፓርቲን ለመፈረካከስ ከሚሰሩት ግለሰቦች መካከል አቶ ትግስቱ አወሉ የተባሉና የቀድሞ የአንድነት አባል በአሁኑ ሰዓት እራሳቸውን ፕሬዝደንት አድርገው ከምርጫ ቦርድ ጋር በጋራ በመስራት ላይ ያሉ ግለሰብ በ16/05/2007 ዓ.ም ላደረጉት ህገ-ወጥ ጉባኤ ተልእኳቸውን ለማስፈፀም በየክፍለሀገሩ የሚገኙ የአንድነት ፓርቲ የጉባኤ አባላትን በስልክና በአካል በመሄድ ለዚህ ህገ-ወጥ አንድነት ፓርቲ ነኝ ባይ ጉባኤ እንዲገኙ በማግባባት፤ከመንግስት ፈሰስ በተደረገላቸው ገንዘብ በመደለል እንዲሁም እንቢ ያሉ ግለሰቦችን ‹‹መንግስት ከኔ ጎን ነው እንቢ ካልክ/ሽ እርምጃ እንወስዳለን፤…..ወዘተ›› ማስፈራሪያ ሲጠቀሙ እንደነበር በየአካባቢው የሚገኙ የአንድነት አባላት ሰሞኑን ሲገልፁ የነበረ ሲሆን ዛሬ በደረሰን መረጃ መሰረት ግለሰቡ በደቡብ ወሎ የአንድነት መዋቅር በሚገኝባቸው ሐይቅ፤ወረባቦ፤ደሴ፤ኮምቦልቻ፤ኩታበር …….የመሳሰሉት ወረዳዎች የሚገኙ የአንድነት የወረዳ አመራሮች ጋር ስልክ በመደወል ከፍተኛ መስፈራራትና ዛቻ የተቀላቀለበት ድርጊት መፈፀማቸውን ከየወረዳዎቹ ያሉ የአንድነት አመራሮች ሪፖርት አድርደዋል፡፡ ግለሰቡ አንድነት ፓርቲ የኔ ነው፤እኔም ነኝ የምመራው፤ በኔ አስተዳደር ስር ሆናችሁ ላለመሳተፍ ከወሰናችሁ፤ በመንግስት በኩል ከፍተኛ እርምጃ ለመውሰድ ዝግጅት ተደርጓል›› ….ወዘተ የሚል ማስፈራሪያ እንደሚያሰሙ ገልፀዋል፡፡ አባላቶቹ አያይዘውም ‹‹እኛ አንድነት አንድ እንጂ ሁለት አይደለም፤ህጋዊ የሆነው አንድነት ፓርቲ በተገቢው ሁኔታ እየተንቀሳቀሰ ባለበት አግባብ መንግስትና ምርጫ ቦርድ ፓርቲውን ለመበታተን ለሚያደርጉት ዘመቻ ተገዢ አንሆንም፤ሰላማዊ ትግላችን ተጠናክሮ ይቀጥላል›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ አቶ ትግስቱ አወሉ በህጋዊውና በትክክለኛው የአንድነት ፓርቲ የፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ እራሳቸውን እጩ አድርገው አቅርበው በመሳተፍ የራሳቸውን አንድ ድምፅ ብቻ አግኝተው መውደቃቸው የሚታወስ ነው፡

የህወሓት ገመና ሲጋለጥ:- ሰብአዊ መብቶች ያልተከበሩበት የልማት ጎዳና ጥቅሙ ለጥቂቶች ብቻ ነው – አክሎግ ቢራራ (ዶ/ር)

aklog
በማንኛውም አገር ቢሆን ድምፅ የሌለው፤ ነጻ የሆነ የዜና አገልግሎት የማያገኝ፤ ተቆርቋሪ የፖለቲካ ወይንም የማህበረሰብ ወይንም የሲቪክ ድርጅት፤ ወይንም በነጻነት የሚንቀሳቀስ የመገናኛ ብዙሃን አገልግሎች የሌለው ሕዝብ መብት የለውም። መብቱ በመንግሥት የተከለከለ ግለሰብ ሆነ ቡድን፤ ማህበረሰብ ሆነ ሕብረተሰብ ዘላቂነትና ፍትሃዊነት ያለው እድገት አይጎናፀፍም። ህወሓት ለሃያ አራት ዓመታት በበላይነት ሲገዛት የቆየች ኢትዮጵያ ፍትህ፤ ነጻነት፤ ሰብአዊ መብት፤ በሕግ ፊት የሁሉም እትዮጱያዊያን እኩልነት የማይስተናገድባት፤ ፍፁም አምባገነናዊ ስርዓት የሰፈነባት ሃገር ሆናለች። የህወሓት መስራቾች ስሌት መስራቾቹ ለሃያ ዓምስት ዓመታት፤ እነሱ ተንከባክበውና አስለጥነው፤ ልክ በፋብሪካ እንደተመረቱ “እቃዎች” የእነሱን ርእዮት፤ የፖለቲካና የኢኮኖሚ የበላይነት መስመር የሚከተሉ ተተኪዎቻቸው ዛሬ ሰላማዊ ሕዝብ ሕገ መንግሥቱ በሚፈቅደው መሰረት ሰላማዊ ሰልፍ ሲያደርግ በጅማል በዱላ እየደበደቡት ነው። ዲፕሎማቶችና ሌሎች ታዛቢዎች እያዩ፤ ባልቴት፤ ወጣት፤ ወንድ፤ ሴት፤ የክርስትና ወይንም የእስልምና ተከታይ፤ ኦሮሞ፤ ጉራጌ፤ አማራ፤ ትግሬ፤ ሳይለዩ እያሳደዱት፤ “እንደ እንሰሳ” በዱላ እየደበደቡት፤ እያፈኑትና እያሰሩት ነው። ድብደባውና ጭካኔው የአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ፤ ከቤተክርስቲያን ተሳልመው ሰልፉን የደገፉ የሰባ ዓመት እናት የሚደበድብ ፖሊስ አገልጋይነቱ ለሕዝብ ሳይሆን ለገዢው ፓርቲ የቆመ መሆኑ የአፍሪካን ብቻ ሳይሆን የዓለምን ሕዝብ ትዝብት ሸምቷል። ኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች መረገጫ መዲና መሆኗ ዙሮ ዙሮ ገዢውን ፓርቲ እንደሚያጋልጠው መገመት አያስቸግርም። በሰላም፤ ለሰላም፤ ለፍትህ፤ ለዲሞክራሲ የሚታገሉ የአንድነት፤ የሰማያዊና የመኢዓድ መሪዎችን፤ አባላትንና ደጋፊዎችን ሲደበደቡ ማየት “ወራሪ” እንጅ ለሃገርና ለሕዝብ የቆመ ገዢ ፓርቲ ነው ለማለት አይቻልም። ተከታታይ የሆነው ጭካኔ የሚያሳየው ህወሓት በራእዩና ፕሮግራሙ እንዳስቀመጠው ለሚቀጥሉት መቶ ዓመታት በኃይልና በጭካኔ ለመግዛት መወሰኑን ነው። ለዚህ የሚያዋጣው አገዛዙ ያስመረረው ምላተ ሕዝብ (አብዛኛው ማለት ነው)፤ ቆርጦና ደፍሮ አገር አቀፍ በሆነ ደረጃ መነሳት ይኖርበታል። በውጭና በውስጥ የሚገኘው ፍትህ ፈላጊ አብሮ ተባብሮ መስራት ግዴታው ሆኗል። ገዢው ፓርቲ የሚፈልገው በተናጥል የሚደረግ ትግልን ነው። ትግሉ የመኖር ያለመኖር፤ ማለትም የህልውና ስለሆነ አብሮ ተያይዞ መነሳት የውቅቱ መሪ ጥያቄ ነው።
የዚህ ጽሁፍ መሰረተ ሃሳብና ክርክር ሰብአዊ መብቶች ካልተከበሩ እንደልብ ለመንቀሳቀስ፤ አቤቱታ ለማቅረብ፤ የግል ድርጅት ለማቋቋም፤ ኑሮን ለማሻሻል የሚደረግ ጥረት ከምኞትና ከህልም አያልፍም የሚል ነው። ይኼን መብት ስኬታማ ለማድረግ የሚችለው ሕዝቡ ለራሱ ህይዎት መሻሻል፤ ወጣቱ ትውልድ ከስደት ይልቅ በሃገሬ ሰርቸ የመኖር መብቴን አስጠብቃለሁ ብሎ ሲነሳ ብቻ ነው። በተለይ በኑሮ ውድነት፤ ጥሮ ግሮ አዳሪና በድህነት የሚሰቃየው ክፍል እና ተምሮ ለስደት የተዳረገው ወጣቱ ትውልድ ለራሱ ሲል ደፍሮ መብቱን ማስከበር ግዴታ ይሆኗል። ማንም የውጭ መንግሥት ሊደርስለት አይችልም።
በቅርቡ በኢትዮጵያ ላለፍቱ ሃያ አራት ዓመታት በአንድ የአናሳ ጎሳ ቡድን ፓርቲ የበላይነት ሲገዛና ሲዳኝ በቆየው “እድገታዊ መንግሥት” ላይ በተለያዩ እውቅና ባላቸው የሰብአዊ መብቶች ተቆርቋሪና ለጋስ ተቋሞች የቀረቡ ዘገባዎች ትኩረት የሰጡት ለመብቶች መረገጥና መታፈን የኢትዮጵያ “ፈጣን” እድገት የጥቂቶች ጥቅም አገልጋይ መሆኑን፤ ዘላቂነትና ፍትሃዊነት ያለው የልማት መሰረት አለመመስረቱን ነው። ይኼን ተከታታይና እየባሰ የመጣ የመብቶች መረገጥና እድገት የጥቂቶች ሃብት መሰብሰቢያ የሆነ ክስተት አሳሳቢ ያደረጉት ሁለት አንኳር ጉዳዮች አሉ። አንዱ መጭው አጠቃላይ ምርጫና የፖለቲካው ምህዳር
(ምድር)ፍጹም በሆነ ደረጃ መዘጋቱ ሲሆን፤ ሁለተኛው ከብዙ ቢሊዮን ዶላር እርዳታ፤ የስደተኛው የገንዘብ ድጋፍ (ሬምታንስ የሚባለው)፤ የውጭ የካፒታል ፈሰስ፤ የመንግሥት ብድርና ብዙ ሚሊዮን ሄክታር ለም መሬትና ወንዝ ለውጭ አትራፊዎች መለገስ በኋላ ኢትዮጵያ አሁንም ድሃና ኋላ ቀር ከሆኑ አገርች መካከል አንዷ ሆና መገኘቷ ነው።
“እውነትና ጭስ መውጫ አያጣም” እንዲሉ፤ የእውነተኛ እድገት መለኪያው የአብዛኛው ሕዝብ ህይዎት መሻሻሉ፤ የአገር ሉአላዊነት መከበሩ፤ የኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሃብት ለኢትዮጵያዊያን አገልጋይ መሆኑ፤ የስራ እድል መፈጠሩ ወዘተ ናቸው። ህወሓት በቅርቡ አራት ብሄራዊ ፖሊሲዎች እንዳልተሳኩለት አምኗል።
አንድ፤ ህወሓት ፈቅዶና አመቻችቶ የኢትዮጵያን የባህር በር መዝጋቱ፤ ኤርትራን ከእናት አገር ማስገንጠሉ፤ በታሪኩ የተያያዘውን ሕዝብ መለያየቱ፤ ሁለት፤ የመንግስቱ ኃይለማሪያምና ከዚያ በፊት ተከታታይ መንግሥታት ለድርቅ፤ ለረሃብ፤ ለስደት፤ ለድህነት፤ ለሕዝብ መፍለስ ኃላፊዎች ናቸው ብሎ ካጥላላና ኢትዮጵያ ከርሃብ፤ ከምግብ እጥረት በአጭር ጊዜ ውስጥ “ነጻ” ትወጣለች ያለው ምኞች ስኬታማ አለመሆኑ፤ ዛሬ “ኢትዮጵያ በዓለም በተከታታይ የምግብ እርዳታ ጥገኛ ከሆኑ አገሮች የመጀመሪያውን ደረጃ ይዛ” መገኘቷ። ፍፁም ርሃብ (ፋሚን) አለ ተብሎ የማይነገረው ከውጭ በሚገኝ የምግብ እርዳታና መንግሥት በሚሸምተው ምግብ ድጎማ ነው።
ሶስት፤ “ልማታዊው መንግሥት” የኢትዮጵያን መሰረታዊ የኢኮኖሚ ችግሮች ለመወጣት አለመቻሉ፤ ዘላቂነትና ፍትሃዊነት ያለው የልማት መሰረት አለመጣሉ፤ የሃገሪቱ ዘመናዊ የኢንዱስትሪና የምርት ክፍሎች/ምሰሶዎች በውጭ ኢንቬስተሮች መያዛቸው፤ የኢትዮጵያ የግል ክፍሉ ጫጩት መሆኑ፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ ስርጭት የሚያመለክት የግል ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ አለመመስረቱ፤ ጉቦ፤ በጎሳ የተመሰረተ አድልዎ፤ ሙስና፤ ከሃገር ተሰርቆ የሚሸሸው የውጭ ምንዛሬ ከፍተኛና አሳሳቢ መሆኑ፤ ወጣቱ ትውልድ ተምሮ ለስደት መዳረጉ፤ የገቢና የኑሮ ልዩነቶች አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሳቸው።
አራት፤ የወታደራዊው ሶሻሊስት መንግሥት ፀር-ዲሞክራሲ፤ ፀረ-ሕዝብ፤ ፀረ-ሰብአዊ መብት ወዘተ ነው ብሎ የምኒልክ ቤተ መንግሥት የገባው ህወሓት ዲሞክራሳዊ ስርዓት በመገንባት ፋንታ፤ ራሱ ፍፁም የሆነ አምባገነናዊ ስርዓት መመስረቱ፤ ሰብአዊ መብቶችን ፍፁም በሆነ ደረጃ ማፈኑ፤ ለእውነተኛ ሽብርተኞችና ለኢትዮጵያ ጠላቶች ሴራ ምክንያት መሆኑ። እነዚህን በቀጥታም ባይሆን በአጠቃላይ ያመነ ይመስላል። አምኖ ግን ራሱን ለመለወጥ አልተዘጋጀም፤ አልፈቀደም። ጨካኝነቱ ብሷል።
ያላመናቸውና ያልተቀበላቸው ብዙ የፖሊሲ ጥያቂቆች አሉ። ለምሳሌ፤ አንድ፤ የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ሃብት–ለም መሬትና ወንዝ–በገፍ ለውጭ አገር ኢንቬስተሮች ማስተላለፉ፤ ነዋሪዎችን ከቀያቸው በገፍና በግፍ ማስወጣቱ፤ ሰላምና እርጋታን ማደፍረሱ። ሁለት፤ “ከፋፍለህ ግዛው” የሚለውን የቅኝ ገዢዎች ፈለግ ተከትሎ ሕዝብን ከሕዝብ ማናከሱ፤ የዘር ማፅዳት ዘመቻ በቀጥታም ሆነ በድብቅ ማካሄዱ። ሶስት፤ በቋንቋ የተመሰረተ ፌደራሊዝም ዘርግቶ አዲስ “የመሳፍንት ዘመንን” የሚያስታውስ ጥቂቶችን ብቻ የሚያገለግል አስተዳደርና ኢኮኖሚ መመስረቱ። የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ከመቸውም በበለጠ ደረጃ በጎሳ ተከፋፍላለች። ለዚህ በሃላፊነት የሚጠየቀው ህወሓት ነው።
የማይካዱ ክስተቶች ብዙ ናቸው። የሕዝብ ለሕዝብ ሰንሰለት ተበጥሷል፤ የዘመናዊ ኢኮኖሚና የማህበረሰብ ግንኙነት (economic and social cohesion) አልተመሰረተም። የሃገር ፍቅር ወድሟል። ከመቶ ዓመታት በላይ የቆዩ ብሄራዊ ተቋሞች ፈርሰዋል። ሆነ ተብሎ።
ለኢኮኖሚው መዛባት ዋና ዋቢ ሆኖ የምናገኘው የተባበሩት መንግሥታት ተቋም አንክታድ (UNCTAD) ያቀረበው ዘገባ ነው። አትኩረን ስናነበው፤ ኢትዮጵያ ስር ነቀል የሆነ፤ የመላውን ሕብረተሰብ ኑሮ የሚያሻሽል፤ አገሪቱን ወደ ዘላቂና ፍትሃዊ ልማት የሚያሸጋግር የእድገት መንገድ ወይንም እቅድ አትከተልም የሚል ነው። የኢትዮጵያ መሰረታዊ ችግር ተፈጥሮ፤ እምቅ የተፈጥሮ ሃብት አለመኖር ወይንም የሕዝብ ስንፍና አይደለም። የስርዓት ማነቆነት ነው። በቅርቡ ዓለም ባንክ ያቀረበው ዘገባ ፍፁም ድህነት እንደቀነሰ ያሳያል። እድገት አለ በሚባልበት የብዙ ቢሊዮን ዶላር እርዳታ ድጋፍ በአገኘ አገር ፍፁም ድህነት መቀነሱ አያስደንቅም። ይኼን የፈጠራ ማስረጃ ይዘን ወደ ዋናው ችግር እንሂድ። አነጋጋሪ መሆን ያለበት፤ ወደ ባሰ ድህነት የገባውና የሚገባው ሕዝብ ብዛት፤ ጥልቀትና ስፋት ነው። መንግሥት የሚሰጠውን ማስረጃ ብቻ ብንቀበል፤ ሰላስ ሰባት ሚሊዮን (በአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት ጊዜ የነበረውን ሕዝብ ቁጥር የሚበልጥ) ኢትዮጵያዊያን ፍፁም ድሃ ወይንም ወደ ፍፁም ድህነት የሚገቡ ናቸው። “Thirty-seven (37) million Ethiopians (almost a third of the population) remain either poor or vulnerable to falling into poverty. The very poorest in Ethiopia have become even poorer…The potential for migration (structural) and non-agriculture growth has been largely missed.” ዓንክታድ ያለውም ይኼን ነው። ይህ መዋቅራዊ ድህነት የፖሊሲ ለውጥ ከሌለ ሊቀየር አይችልም። ድሃ ሆኖ የተወለደ ህፃን ድሃ ይሆናል ማለት ነው። ዓለም ባንክ ማነቆዎቹ ምን እንደሆኑ አልገለፀም፤ ፖለቲካ ነክ ስለሆኑ።
የችግሩን ገፅታ በምሳሌ እንየው።
የሁለት ድሃ እናቶችን ኑሮ እናስብ፤ አንዷ በገጠር ሌላዋ በከተማ የሚኖሩ፤ በስደት የሚኖር፤ ከመቶ እስከ አንድ መቶ አምሳ ዶላር በዓመት አምስት ጊዜ የሚልክ/የምትልክ ልጅ የሌላቸው የገቢ ድሃ እናቶች ኑሮን ማለቴ ነው። በከተማ አምስት ወይንም ስድስት ልጆች የምታስተዳድር የቤት ሰራተኛ ወይንም መሸታ በመሸጥ የምትኖር፤ ወይንም የቢሮ ፅዳት ስራ ወይንም ሌላ ዝቅተኛ ገቢ ያላት እናት ልጆቿን በቀን ሶስት ምግብ ለመመገብ አትችልም። እንደሚባለው ከሆነ፤ የቤተሰቡ አባላት ምግብ በመፈራረቅ ይበላሉ፤ ህይዎታቸው አለ፤ ኑሯቸው ግን አሰቃቂ ነው። በተለይ የቤት ኪራይ የሚከፍሉ ከሆነ። ለዚህ ቤተሰብ ንፁህ ውሃ፤ መፀዳጃ፤ መብራት፤ የጤናና የትምህርት አገልግሎልት፤ መጓጓዣ ህልም ነው። ልጆቹ ለመማር ካልቻሉ ደግሞ መዋቅራዊ ወደ ሆነ፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ ወደሚተላለፍ ድህነት ገቡ ማለት ነው። በአዲስ አበባ ብቻ እስከ አንድ ሚሊዮን የሚገመት ሕዝብ–እናቶች፤ ሺማግሌዎች፤ እናት የሌላቸው ህጻናት፤ ወጣት ወንድና ሴቶች በመንገድና በጠለላ ይኖራሉ፡፡ ይሕ በ November 8, 2012 በአንድ የውጭ አገር ታዛቢ ተቀርጾ የተላለፈ ቢዲዮ የድህነትን አሰቃቂ ገጽታ ያሳያል። እድገት በጦፈባት አዲስ አበባ፤ አንድ ሚሊዮን ሕዝብ ማለት የአዲስ አበባ ሕዝብ አንድ አስረኛ ማለት ነው። የሰዎቹ በጠለላ መኖር ብቻ አይደለም አሰቃቂነቱ። እናቶችና ወጣቶች ኮራ በተባለው አካባቢ የሚጣለውን ቆሻሻ ምግብ እየለቀሙ መብላታቸው ጭምር ነው። ለበሺታ የሚዳርገው የቆሻሻ መሰብሰቢያ አይጥ፤ ልዩ ልዩ ተባዮች ተሰማርተውበታል። በተላላፊ በሺታዎች መበከል አይቀሬ ነው። በጠለላ ተጨናንቀው የሚኖሩት ኢትዮጵዊያን የአባለ ዘርእ በሺታ፤ ኤች አይ ቢ አኤድስ፤ የተስቦ በሺታ፤ ቲቪ ወዘተ ያሰቃያቸዋል። አዲስ ባለሃብቶች “ለቃተኛ” ምግብ በሚሰለፉባት አዲስ አበባ እነዚህን ድሃዎች ዞር ብሎ የሚያያቸው የለም። ሰብእነታቸው ሙሉ በሙሉ ተገፏል ለማለት እንችላለን። ይኼ ብዙ ሕዝብ ጤናው ከመታወኩ ሌላ ልጆቹና የልጅ ልጆቹ ወደ ፍፁም ድህነት ገብተዋል ማለት ነው። በዚህ ሁኔታ ተወልደው የሚያድጉት ወጣቶች እንደሌላው ወደ ውጭ ለመሰደድም ተስፋ አይኖራቸውም። ከጥቂቶች በስተቀር።
ከላይ የተጠቀሰችው እናትና በጠለላ የሚኖሩ የተወሰኑ እናቶች ልጆች አማራጭ ስለሌላቸው ወደ ውጭ ይሰደዳሉ። የድሃ አናት ሴት ልጇ “በዚህ አይነት ኑሮ አልኖርም፤ እድሌ ያውጣኝ፤ ወደ አረብ አገሮች ወይንም ወደ ማላዊ እሰደዳለሁ” ብትል እናቷ ልታቆማት አትችልም። በገጠር የምትኖረው ስድስት ልጆች የምታስተዳድር እናት የተሻለ ኑሮ ትኖራለች። ልጆቿ ከቆሻሻ ምግብ አውጥተው አይበሉም። የእርሷ ችግር ለየት ያለ ነው። ቤተሰቧ አንድ ሄክታር መሬት አለው እንበል። የእርሻው ስራ ለራሳቸው ምግብ በቂ ነው፤ ቅጠላ ቅጠል፤ ድንች ወዘተ በጓሮ ያመርታሉ፤ ስለዚህ ራሳቸውን ችለዋል የሚለውን እንቀበል። ይህ ቤተሰብ ገቢው ከፍ ስላለ ጥራ ጥሬ ወይንም በግ ሽጦ ልብስ፤ ጫማ፤ የተሻለ የእርሻ መሳሪያ ወዘተ ለመግዛት እናት ወደ ገበያ ብቅ ስትል ከገቢዋ ጋር ተመጣጣኝ የሚሆን የአገር ውስጥ ሆነ የውጭ እቃ ለመግዛት አልቻለችም፡፡ “እግዚዖ፤ ምን ጉድ መጣ፤ እድገት አለ እያሉ እንዴት ምርት ለማቅረብ አልቻሉም” ብላ ራሷን ከመጠየቅ አታልፍም። በአገር ውስጥ የሚመረተው ከፍላጎት ጋር አልተመጣጠነም ማለት ነው። የከተማ ነዋሪዋ በቂ ምግብ የላትም፤ የገጠሯ ለኑሮዋ መሻሻል የሚያስፈልጋትን ለመሸመት አልቻለችም። መዋቅሩ አልተለወጠም የሚባልበት መሰረታዊ ምክንያት ከምርት ጋር፤ ከእርሻ ዘመናዊነት ጋር፤ ከአቅርቦት ጋር፤ ከኢንዱስትሪ መስፋፋት ጋር፤ ከስራ እድል ጋር፤ ከኑሮ መሻሻል ጋር የተያያዘ ባለመሆኑ ነው። “መንገዱ እኮ ምግብ አይሆነኝም” ያለውን ኢትዮጵያዊ በአእምሯችን እንቅረፀው። በልቶ ማደር የሰብአዊ መብት ነው። የቀድሞው የብራዚል ፕሬዝደንት ዳ ሲልቫ የተናገሩት ትዝ ይለኛል። “ርሃብ ከማንኛውም አሰቃቂ እልቂት የባሰ ነው፤ ርሃብን፤ ድህነትን ማጥፋትና ዘላቂነትና ፍትሃዊነት ያለው የልማት እቅድ መከተል ለሰላም ወሳኝ ነው” ያሉት። መዋቅራዊ ለውጥ ከዚህ ተለይቶ አይታይም።
ኡኑክታድ እድገት ያሳየችው ኢትዮጵያ እድገቷን ተጠቅማ መዋቅራዊ ለውጥ አልመሰረተችም ሲል በፍጥነት ካደጉ፤ ለምሳሌ ከምስራቅ ኤዝያና ፓሲፊክ ሃገሮች ጋር በማነጻፀር ነው። እነዚህ አገሮች ዘመናዊነትና ሃብታምነትን የተጎናፀፉት ሁለገብ የሆነ፤ አንዱ ሌላውን የሚደግፍ፤ በሕዝብ ተሳትፎ፤ ደህንነትና የኑሮ መሻሻል የተመሰረተ የልማት መንገድ በመከተላቸው ነው። አገር ወለድ የሆነ። መንግሥቶቻቸው ለሃገራቸው ተቆርቋሪነትና ሃላፊነት፤ ለመላው ሕዝባቸው ፍቅር ያሳዩ፤ ከሁሉ በላይ አገሮቻቸውና ህብረተሰቦቻቸው ከድህነትና ከኋላ ቀርነት መጥቀው የምእራብ አገሮች ከደረሱበት ለመድረስ ቀን ከሌት የሰሩ ናቸው። የተፈጥሮ ሃብታቸውንና ሃገራቸውን እንደ ተራ ሸቀጥ አልነገዱበትም። ጃፓንና ደቡብ ኮሪያ ምሳሌ ናቸው።
እንደ ደቡብ ኮሪያ ድሃና ኋላ ቀር የነበሩ አገሮች የውጭ ብድር ተጠቅመው፤ ግን በአብዛኛው በራሳቸው ጥረትና በመንግስቶቻቸው አገር ወዳድ አመራር፤ ደቡብ ኮሪያን በሃያ አምስት ዓመታት ከበለፀጉ አገሮች አንዷ እንድትሆን አድርገዋል። ደቡብ ኮሪያ ከእርዳታ ነጻ የሆነችው ከሃያ እስከ ሃያ አምስት አመታት በሚገመት የጊዜ ገደብ ነው። የውጭ እርዳታ ጥገኝንትን እንደሚያስከትል የተረዱ መሪዎች ነበሩ። በፍጥነት አስደናቂ የልማት ውጤት ስኬታማ ያደረገችው በአገር ወዳድ መሪዎቿ፤ ዘመናዊ ከፓርቲ ቁጥጥር ውጭና ብሄራዊ በሆኑ ተቋሞቿ፤ በሰለጠኑ የመንግሥት ሰራተኞቿ አገልግሎትና መላውን ሕዝቧን አሳታፊ በሆኑ ህጎችና መመሪያዎች ነው። ለዘላቂና ፍትሃዊ ልማት የሃገር ፍቅር ሚና አለው፤ ተቋሞች ሚና አላቸው፤ የህግ የበላይነት ሚና አለው፤ ሃላፊነትና ግልፅነት ሚና አላቸው። ደቡብ ኮሪያ፤ ቻይና፤ ቬትናምና ሌሎች አሳይተዋል። አምባገነን መንግሥታት ቢኖሯቸውም አገር ወዳድነታቸው አያከራክርም። ከሁሉም በላይ ቅድሚያ የተሰጠው ኮሪያን በፍጥነት ማሳደግና የኮሪያን ሕዝብ ከድህነት፤ ከርሃብ፤ ከስራ አጥነት፤ ከድንቁርና፤ ከበሽታ ወዘተ ነጻ ማውጣት ነበር። ሴቶች፤ ወጣቶችና የገጠሩ ሕዝብ የእድገቱ ሙሉ ተሳታፊ ነበሩ። በዚህ ስሌት ይሆን ለሃገርና ለመላው ሕዝብ ፍቅር አለኝ ለማለት የማይችለው፤ አሁንም ራሱን የ “ትግራይ ነጻ አውጭ ግንባር” ብሎ የሚጠራው ህወሓት ተጨማሪ አምስት ዓመታት መግዛት አለብኝ እያለ አፈናውን ያባባሰው። ለምን ይሆን ብሎ መጠየቅ ሞኝነት ቢመስልም፤ ጥያቄውን ማቅረብ ተገቢ ነው። ከጅምሩ፤ ህወሓት ለኢትዮጵያ ታላቅና ረጂም ታሪክ ግምትና እውቅና አልሰጠም፤ የኢትዮጵያን ዘላቂ ጥቅሞችና ሉአላዊነት ደምስሧል፤ ሕዝቦቿ እየተወያዩና እየተናበቡ አብረው ችግሮችን መፍታትና ተቻችሎ መኖርን መመሪያቸው እንዳያደርጉ በተግባር አሳይቷል፤ የደርግን መንግሥት ጨካኝነት፤ ኢሰብአዊነትና ፀረ-ዲሞክራሳዊነት በማስተጋባት፤ “ህወሓት/ኢህአዴግ አዲስ የዲሞክራሲ ምእራፍ ይዤ መጥቻለሁ፤ የምስራች ለኢትዮጵያ ሕዝብ” ብሎ ስልጣኑን ካመቻቸ በኋላ ከደርግ ያላነሰ ፀረ ዲሞክራሲ፤ ፀረ-ሕዝብ ሆኗል። ሕዝቡ ዲሞክራሳዊ ስርዓትን ለመገንባት ያለውን ምኞትና ተስፋ የውሃ ሺታ አድርጎታል። ያለፉትን መንግሥታት እየወነጀለ ጠባብና ጎሰኛ አድሏዊነትን የመንግሥት መመሪያ አድርጓል። በጥላቻና በቂም በቀል የተመራበት መርህ ታላቋን ትግራይ መመስረት የሚል፤ ለዚህ እንዲጠቅም የጎንደርንና የወሎን መሬቶች በኃይል ነጥቆ ወደ ትግራይ ክልል አጠቃሏል። የትግራይን ወሰን ከሱዳን ጋር ኃይል ተጠቅሞ ዘርግቷል። በታሪኩ ኢትዮጵያዊ የሆነውን የትግራይን ሕዝብ ከሌሎቹ ወንድሞቹና እህቶቹ ለመለየት ሞክሯል። ጥላቻንና ቂም በቀልነትን አንግቦ “ኦሮሞውን አማራው ተመልሶ ስልጣን ሊይዝ ነው፤ ተጠንቀቅ፤ አማራውን ኦሮሞው ስልጣን ከያዘ ወዮልህ፤ እልቂት ይከተላል፤ ትግሬውን፤ አማራውም ሆነ ኦሮሞ ስልጣን ከያዘ ትግሬዎችን በያሉበት ይጨፈጭፋል፤ የሩዋንዳ አይነት እልቂት አይቀርም” ወዘተ የሚል ቡድን ነው። ይኼ ለብሄራዊ እድገትና ሰላም ፀር ነው።
ይኼ ሁሉ በድምሩ ለመብቶች መገፈፍና ለኢትዮጵያ ሕዝብ መከፋፈል አስተዋፆ አድርጓል። ሕዝብ ለሕዝብ አለመተማመን የጠቀመው ለዚህ ቡድን ነው። “ከፋፍለህ ግዛው” የቡድኑን አምባገነን ስርዓት አራዝሞለታል፤ ለሰብአዊ መብቶች መታፈን መሰረት ሆኗል። ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና “ተባበሩ ወይንም ተሰባበሩ” ሲል ይኼን አይቶ ይመስለኛል። በምን ላይ እንተባበር? የሚለው የአንዳንድ ተቃዋሚ ክፍሎች ትርጉም የለሽ ጥያቄ ከተመለሰ ቆይቷል። ፈቃደኛነት፤ መተማመን ወዘተ ስለሌለ መተባበር የሚለውን ቃል ሰምተን እንዳልሰማን እያለፍነው ነው። እድል እያመለጠን ነው። ቢያንስ፤ በኢትዮጵያ ሉአላዊነትና ግዛታዊ አንድነት–አገርን በማዳን፤ በሰብአዊ መብቶች መከበር፤ ሕዝብን ከመገረፍ በማዳን፤ በሕግ የበላይነት፤ ለሕዝብ ታዛዢ የሆነ መንግሥት በመመስረት፤ በነጻና ፍትሃዊ ምርጫ፤ በፀረሙስና፤ በፀረየመሬት ነጠቃ ወዘተ ለመስማማትና አብሮ ለመስራት ይቻላል። መተባበር ከሌለ በተናጠል የፖለቲካ ጩኸቱ ዋጋ ቢስ ነው፤ የትም አያደርስም። ከአርባ ዓመታት በኋላ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከተቃዋሚው ክፍል የሚጠብቀው መጠላልፍን አይደለም። መተባበርን፤ መተሳሰብን፤ ለጋራ ዓላማዎች መቆምን ወዘተ ነው። “ለመተባበር የሚያስችሉ ሁኔታዎች የሉም፤ በተናጠል የምንታገለው ለዚህ ነው” የሚሉ ግለሰቦችና ቡድኖች የሚያገለግሉት ራሳቸውንና ገዢውን ፓርቲ ነው ለማለት ከምንደፍርበት ጊዜ ደርሰናል። ህወሓት በበላይነት የሚመራው ስርዓት አገሪቱን ለማስተዳደር፤ አንድነቷን ለመጠበቅ፤ የህዝቧን ሕይዎት ለማሻሻል ከማይችልበት ደረጃ ላይ እንደ ደረሰ ብዙ ተመልካቾች ይናገራሉ። አስተዳደር ፍፁም ተበላሽቷል። የሕዝብ አመፅ በየቦታው ብቅ ብቅ ማለት ጀምሯል። በሰራዊቱ ውስጥ ሹክቻው ተስፋፍቷል ወዘተ። ስለሆነም ነባራዊ ሁኔታው በፍጥነት እየተለወጠ ነው። ለዚህ ጠንካራ ድርጅትና መተባበር ወሳኝ ነው። አንዱ ሲነሳ ሌላው መነሳት፤ አንዱ ሲደበደብ አለሁልህ ማለት ወዘተ አስፈላጊ ነው።
በብዙ ተመልካቾች ዘገባ ተጨማሪ አምስት ዓመታት ሆነ አስር ቢገዛ ህወሓት የኢትዮጵያን መሰረታዊ ችግሮች በጋራ ለመፍታት የሚቻለው የኢትዮጵያ ሕዝብ የስልጣኑ ባለቤት ሲሆን ብቻ ነው። ባለፉት ሃያ አራት ዓመታት ሊፈቱ ያልቻሉ የፖሊሲና መዋቅራዊ የሆኑ የማህበረሰብ ችግሮች፤ ለምሳሌ የስራ እድል አለመኖር፤ የኑሮ ውድነት፤ የመጠለያ እጥረት፤ ጉቦ፤ አድልዎ፤ ሙስና፤ የመሬት ነጠቃ፤ ከህግ ውጭ ከአገር የሚወጣው ብዙ ቢሊዮን ዶላር፤ የኢትዮጵያዊነት መታወቂያ ቅርሶች መውደም፤ ወዘተ፤ወዘተ በህወሓት/ኢህአዴግ መሪዎች አርቆ አስተዋይነት ይፈታሉ ብሎ ማሰብ አይቻልም። ለጠባብ ቡድን ጥቅም የቆመ አገዛዝ ጥቅሙን የሚያስተናግደው የፖለቲካና የኢኮኖሚ የበላይነትን በመያዝ ብቻ ነው። እርግጥ፤ የአሁኑን የአምስት ዓመት እቅድ አሻሽለናል፤ በስራ እድል ፈጠራ፤ በእርሻና በኢንዱስትሪ ልማት ላይ ወዘተ ትኩረት እናደርጋለን ወዘተ ሊል ይችላል። ይህ መሰረታዊ ለውጥ አያመጣም፤ የመቆያ ዘዴ ነው። መሰረታዊ ለውጥ ከሕዝብ መብቶችና ስልጣን ጋር የተያያዘ ነው። የሚተካው ነገር የለም።
ዛሬ ፍጹም በሆነ ደረጃና ከድሮው በባሰ ሁኔታ የሰብአዊ መብቶች መረገጥ የሚያሳየው ገዢው ፓርቲ የሃብት ጥቅም ያጎናፀፈውን የብቸኛነት የፖለቲካ ስልጣን ለማንም አሳልፎ እንደማይሰጥ ነው። የፍራቻው መንስኤ ይኼው ነው ለማለት ያደፋፍራል። ለፍርሃት መልሱ ደግሞ አፈና ነው። ህወሓት የሚፈራውና የሚሰጋበት አበይት ነገር አለ ማለት ነው። እመርታዊ የሆነ መላውን መቶ ሚሊዮን ሕዝብ የሚያገለግል የልማት መሰረት ከጣለ ህወሓት/ኢህአዴግ የሰብአዊ መብቶችን መከበርና የተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ተሳትፎ የሚፈራበት ምክንያት የለም፤ ለምን ይፈራል? የሃሳብ ልዩነቶችን ለምን ይፈራል? የአብዛኛውን ኢትዮጵያ ሕዝብ ህይዎት ካሻሻለ፤ ለወጣቱ ትውልድ የስራ እድል ከፈጠረ፤ የአስተዳደር አግልግሎቱ ቀልጣፋና ከጉቦና ከአድልዎ ነጻ ከሆነ ሕዝቡ ያምነዋል ማለት ነው። ካመነው ይመርጠዋል ማለት ነው። ያለምንም ማጭበርበር። ሁኔታው ከዚህ የተለየ ነው። አፈናው በስርዓቱ ውስጥ ያለውን ፍራቻ ያመለክታል። “ከፈራን እኮ ኢትዮጵያን እንደ ኤርትራ ለማድረግ እንችል ነበር” የሚል አነጋገር ይሰማል። ኢትዮጵያ እንደ ኤርትራ ብትሆን ኖሮ ለጋሶች ለልማታና ለምግብ ድጎማ ወደ አርባ ቢሊዮን ዶላር፤ ለልማት ድጎማ ብቻ በዓመት አራት ቢሊዮን ዶላር አይለግሱም ነበር። ባይለግሱ ኖሮ አዲስ ስርዓት ወለድ ሚሊዪኔሮች አይፈጠሩም ነበር። ጀኔራሎች የሚያከራዩት ሰማይ ጠቀስ ፎቅና የመኖሪያ ቪላዎች ለመስራት አይችሉም ነበር። ወዘተ. ወዘተ. አፈናው ይኼ ሁሉ እንዳይታወቅ ጭምር ነው።
የነጻ ተቋሞች ፍፁም መደምሰስ
ህወሓት ትኩረት ያደረገው ተፎካካሪ/ተወዳዳሪ በሆኑ፤ ለሕብረተሰቡ ነጻነት፤ መብትና ፍትህ በቆሙ ህብረ ብሄር የፖለቲካ ፓርቲዎችና የነጻ መገናኛ ብዙሃን ላይ ነው። ሁለቱን ክፍሎች ያያቸውና የፈረደባቸው እንደ ተወዳዳሪና አማራጭ ሰጭ ሳይሆን እንደ ጠላት ነው። ሕብረ-ብሄር የፖለቲካ ድርጅቶች፤ በተለይ አንድነት፤ መኢአድና ሰማያዊ በሕዝብ በኩል ተሰሚነትና ታማኝነት ስለተቀዳጁ ለገዢው ፓርቲ አስጊ ናቸው ከሚል ድምዳሜ ላይ የደረሰ ይመስላል። ስለሆነም፤ እነዚህን ተቀናቃኞች የመንግሥት ስልጣንና ገንዘብ ተጠቅሞ፤ የሕጋዊ ሽፋን–የምርጫ ቦርድ፤ ፍርድ ቤቶች፤ ፖሊስ–(the veneer of legality, for example, the political machine of the Election Board) ተጠቅሞ ማዳከም፤ ማግለል፤ ቢቻል ዋጋ ቢስ ማዳረግ የመንግሥት ስራ ሆኗል። ዓላማው እነዚህ ተቀናቃኞች በምርጫው እንዳይሳተፉ ለማድረግ ነው። ፈቃድ የሚሰጣቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች ለገዢው ፓርቲ ታማኝ የሆኑት ብቻ ይሆናሉ ማለት ነው። ከሆነ፤ ገዢው ፓርቲ የዛሬ አምስ ዓመስት ካገኘው የበለጠ ወይንም ያላነሰ ድምፅ አገኘሁ ብሎ የበላይነቱን ይቀጥላል ማለት ነው። የአውሮፓ የጋራ ማህበር እንዳለፈው ወደ ኢትዮጵያ የምርጫ ተመልካቾች ወይንም ታዛቢዎች አልክም ብሎ የወሰነበት ምክንያት በነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ሂደት ምንም እምነት ስለሌለው ነው። አግባብ ያለው አቋም። አሜሪካም ይኼን መንገድ መከተል አለባት።
ህወሓት ሌላ ትኩረት የሰጠው ተቋም በነጻነት የሚንቀሳቀሱ መገናኛ ብዙሃንን ማጥፋት ነው። ነጻ የሆኑ ጋዜጠኞችን ለምን በጅምላ አሰረ ወይንም ከሃገር እንዲወጡ አስገደደ፤ ወይንም ራሳቸውን እንዲያግቡ (Self-censorship) አስገደደ? የፖለቲካ ውድድር አማራጮችን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ለማቅረብ የሚደረገው ጥረት የህወሓትን የበላዮች ለምን አስፈራቸው? ወዘተ. ወዘተ. ህወሓት/ኢህአዴግ በነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ተወዳድሮ ቢያሸንፍ የሕዝብን ልብ ሊማርክ፤ የዓለምን ሕዝብ አክብሮት ሊቀዳጅ ይችላል። ይኼ ከሆነ ሽብርተኞች ቀዳዳና ቦታ አያገኙም። ሕዝቡ መግቢያ ይነሳቸዋል። የገዢው ፓርቲ እምነት በጠበንጃ ሳይሆን በሕዝብ መብት ላይ የተመሰረተ ቢሆን ሰላምና እርጋታ አስተማማኝ ይሆናሉ፤ አሁን አይደሉም። የነጻነታቸውን መብት ተጠቅመው የሚንቀሳቀሱ ጋዜጠኞችና ተወዳዳሪ ፓርቲዎች ተመሳሳይ የሆነ አቋም አላቸው። ሰብአዊ መብቶች፤ ፍትህ፤ የሕዝብ ድምፅ ይከበሩ ወዘተ የሚል። ስለሆነም፤ እንደ ጠላት ተቆጥረዋል። ህወሓት ተወዳዳሪ ጠላቱ ነው።
ህወሓት የተወዳዳሪ ፓርቲዎች አባላትንና መሪዎችን፤ ነጻነታቸውን ጠብቀው ለሕዝብ የሚያገለግሉ ጋዜጠኞችን፤ ብሎገሮችን፤ የማህበረሰብ ድርጂት መሪዎችን ወዘተ እያሰረ፤ እያሳደደ፤ እያስፈራራ፤ እያባበለ፤ ሰርጎ ገብቶ እየከፋፈለ ተቃዋሚ—ተወዳዳሪ ብሎም አይጠራቸውም– የለም ይላል። የፖለቲካ ምድሩ (ምህዳሩ) ዝግ ከሆነ፤ መናገር፤ መሰብሰብ፤ ሕዝብን ማነጋገር፤ ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄድ ወንጀል ከሆነ ተቃዋሚ ወይንም ተወዳዳሪ ፓርቲ ሊኖር አይችልም። እያፈኑና እያሳደዱ ተወዳዳሪ የለም ማለት ለህሊና ተቀባይነት የሌለው አጭበርባሪነት ነው። የማይካደው ህወሓት ተቃዋሚውን የሚያየው በጥላቻና በጥርጣሬ መነፅር ነው። እንደ ጠላት። በዚህ ፓርቲ ስሌት ጠላትን መወንጀል፤ ማሳደድ፤ በድብቅ መግደል፤ መደብደብ፤ ማዋረድ፤ ማሰር፤ መንቀሳቀሻ ማሳጣት፤ ወንጅሎ ቤተስብና ወዳጅን መከታተል፤ አስፈላጊ ሲሆን ንብረትን መቀማት መሆኑ ለሰላም፤ ለእርጋታ፤ ለዘላቂና ፍትሃዊ እድገት ማነቆ ሆኗል። አማራጩ አሁንም በጥላቻ ፖለቲክ አዙሪኝ መጓዝ አይመስለኝም። ለህወሓት/ኢህአዴግም አይበጅም። የሚበጀው በሰከነ አእምሮ፤ አገሪቱን ከመበታተን አደጋ ለማውጣት የሚያስችል፤ ሁሉንም ዜጎች የፖለቲካው ስልጣንና የእድገቱ ተካፋይ የሚያደርግ፤ ሙስናን የሚቆጣጠር፤ የጠፋውን ግዙፍ ሃብት ተከታትሎ ለማስመለስ የሚያስችል፤ በጎሳ የተመሰረት አድልዎን የሚያስወግድ፤ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን በሕግ ፊት እኩለነት እንዳላቸው የሚያስተጋባ፤ የፖለቲካ ተወዳዳሪነት ጠላትነት ሳይሆን ለሃገሪቱና ለሕብረተሰቡ ፍትህ-ርትህ ወሳኝ መሆናቸውን የሚያስተጋባ ባህልና ልምድ፤ ኢትዮጵያዊያን በመፈላለግ፤ በመወያየት ችግሮቻቸውን በእርቅና በሰላም ለመፍትት የማመቻቸት ብቃት እንዳላቸው የሚያመልክት፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ የስልጣኑ ባለቤት መሆኑን የሚያንፀባርቅ አገዛዝ ለመመስረት እንደሚችሉ የሚያሳይ፤ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ለዚህ ዲሞክራሳዊ ስርአት ወሳኝ መሆኑን ተቀብሎ አዲስ የፖለቲካ ምእራፍ መክፈት ነው። አዲስ ለሕዝብ ተገዢና ተጠሪ የሆነ አገዛዝ ይመስረት ማለት እንዳለፈው ለመወነጃጅል፤ ለቂም በቀልነት መሆን የለበትም። ፍትህ እንዲሰፍን፤ ሕብረተሰቡ ከአስቃቂ የኑሮ ችግር መጥቆ እንዲወጣ፤ አገሪቱ እንዳትፈራርስ፤ የውጭ ጠላቶችና ሽብርተኞች መግቢያ ቀዳዳ እንዳይኖራቸው ነው። ይኼ በምኞት አይመጣም። የሰብአዊ መብቶች መከበር ለዚህ የተቀደስ አቅጣጫ ወሳኝ ነው።
ሰብአዊ መብቶች ነገ ሳይሆን ዛሬ ካልተከበሩ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ በምንም አይታሰብም። እንዲያውም እድሉ አምልጧል ለማለት ያስደፍራል። በህወሓት ስሌት አሸናፊው በቅድሚያ ተወስኗል። የፖለቲካ አካልና መሳሪያ የሆነው የምርጫ ቦርድ ዋና ስራው ተወዳዳሪ የሆኑ፤ በተለይ እንደ አንድነት፤ መኢአድ፤ ሰማያዊና ሌሎች ህብረ ብሄር የፖለቲካ ፓርቲዎች በረባ ባልረባው ተወጥረው፤ ለምርጫው ዝግጅት እንዳያደርጉ፤ አቤቱታ አቅራቢ እንዲሆኑ አስገድዷቸዋል። የምርጫ ቦርድ፤ የህወሓት ካድሬዎች፤ የፖሊስ፤ ደህንነትና ፍርድ ቤቶች ተቆራኝተው የምርጫ ቦርድ የገዢው ፓርቲ፤ በተለይ የህወሓት መሳሪያ መሆኑ በኢትዮጵያ ሕዝብ በኩል አመኔታ እንደሌለው ካሳየ ቆይቷል። የውጭ የሰብአዊ መብቶች ተቋሞችና መንግሥታት ይህ ሁኔታ በጣም አደገኛ መሆኑን በተደጋጋሚ ተናግረዋል። እነዚህ ድርጅቶች በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ የሚያቀርቡት ሂስ የራሳቸው ፈጠራ አይደለም። በተጨማሪ፤ አንዳንድ መንግሥታትን ያሳሰባቸውም ከራሳቸው ጥቅም ጋር ሲመለከቱት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጠር የእርስ በርስ ግጭት ሰላምና እርጋታ ለሌበት ለመላዉ የአፍሪካ ቀንድ አደገኛ መሆኑን ስላወቁት ነው። በተጨማሪም፤ የውጭ ኢንቬስተሮች ቀስ በቀስ የሰብአዊ መብቶች መረገጥ አደገኛ መሆኑን እየተረዱ ናቸው። የራሳቸው ሕዝብ እየጮኸባቸው ነው። የሰብአዊ መብት ተቋሞች የሚያስመሰግን አስተዋፅዖ አድርገዋል። በቅርቡ የጀርመኑ የግል ድርጂት ችቦ (Tchibo)፤ የቱርኩ Ayka Investment፤ የስዊድኑ H&M በኦሞ ሸለቆ የሚመረት ጥጥ ለጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ስራቸው አንጠቀምም ብለው አስታውቀዋል። ለምን? የኦሞ ሸለቆ ልማት የሚካሄደው ነዋሪውን ሕዝብ ከመሬቱ አስገድዶ በማስወጣት ነው።
የመሬት ነጠቃ የሚባለው በኢትዮጵያ ስር የሰደደው የገዢው ፓርቲ የልማት አካል መብቶችን አፍኗል። ልክ ጋምቤላ እንደሚደረገው የመሬት ነጠቃ የኦሞ ሸለቆን ነዋሪ ሕዝብ አግልሎታል፤ መድረሻ አሳጥቶታል፤ኑሮውን አፍሮሶበታል። ለጭቁን ሕዝቦች ቆሜያአለሁ የሚለው ህወሓት በኢትዮጵያ ዜጎች ላይ ያካሄደውና የሚያካሂደው በደል ይዘገንናል። ከቡድኑ ጥቅም በላይ አሻግሮ ለማየት አልቻለም። ነዋሪዎች ከመሬታቸው ተገደው እየፈለሱ ከድህነት ወደ ፍፁም ድህነትና ስደት እንዲሸጋገሩ ተደርጓል።
ይኼ የሚካሄደው በልማት ስም ነው፤ ልማቱ የሚያገልግለው የኦሞ ሸለቆን ነዋሪዎች ሳይሆን የገዢውን ፓርቲና አጋሮቹን ነው። የእነዚህ ወገኖቻችን መብት ከተገፈፈ የራሳችንም መብት ተገፈፈ ማለት ነው። ህወሓት ይኼን የሚያደርገው ዓለም የተቀበለውን ሕግና መመሪያ ጥሶ ነው። አከራካሪው የህወሓት መብቶችን ማፈኑ ብቻ አይደለም፤ የውጭ እርዳታ ሰጭዎች ተባባሪነት መኖሩ ጭምር ነው።
በ January 19, 2015, Guardian ያወጣው ዘገባ የመሬት ነጠቃን አደጋ ያሳያል። ዓለም ባንክና የእንግሊዝ መንግሥት የእርዳታ ክፍል ለአዲስ መንደሮች ግንባታ የሰጡት ድጋፍ ሰብአዊ መብቶችን የጣሰ መሆኑን አስምሮበታል። የዓለም ባንክ የውስጥ ቁጥጥር ክፍል ባንኩ የሰጠው እርዳታ “በቁጥጥር፤ በዖዲት፤ በባንኩ የውስጥ ደንብ” ስላልተደገፈ እርዳታው “የኢትዮጵያ መንግሥት የፖለቲካ መሳሪያ ሆኗል” የሚል ትችት ነው። በዚህ የተነሳ “ብዙ ሺህ ኢትዮጵያዊያን ከመሬታቸው በኃይል ተወግደው ለድህነት ተዳርገዋል፤ ብዙዎች ተሰደዋል፤ ኑሩቸው ተናግቷል።” ጥልቀት ያለው ጥናት ያደረገው ዖክላንድ ኢንስቲቱት “ዓለም ባንክ ራሱን አልገሰፀም” ብሏል። በማንኛውም የእርዳታ ክፍል ዓለም ባንክ ራሱን ስህተት ሰርቻለሁ ብሎ አያውቅም። አኑራዳህ ሚታል፤ የተቋሙ መስራችና ፕሬዝደንት እንዲህ ብላለች። “Along the World Bank and other donors, DFID (UK) support constitutes not only financial support but a nod of approval for the Ethiopian regime to bring about economic development for the few at the expense of basic human rights and livelihoods of its economically and politically most marginalized ethnic groups.” ለህወሓት መንግሥት የሚሰጠው ማንኛውም እርዳታ ነጻ የሆነ ቁጥጥር የለውም፤ ገንዘቡ የሚሰጠው ለገዢው ፓርቲ ነው። ማስረጃው የሚመጣው ከራሱ ነው። የድሃው ቁጥር ብዛት በትክክል አይታወቅም። እድገቱ ለማን እንደጠቀመ ይታወቃል፤ ማንን እንደጎዳ ይታወቃል። ዓለም አቀፍ ሁሉን ዓቀፍ ተቋም የሚመራው ዴቪድ ፕሬድ እንዳለው “ዓለም ባንክ ኢትዮጵያዊያን ከቀያቸው በኃይል እንዲባረሩ አድርጓል…ሰብአዊ መብቶች እንደተገፈፉ አይቶ እንዳላየ ዝም ይላል። The Bank today just does not want to see human rights violations, much less accept that it bears some responsibility when it finances those violations.” ባጭሩ፤ አበዳሪዎችና ለጋሶች ለሰብአዊ መብቶች መገፈፍ ሃላፊነት አለባቸው። ለህወሓት የሚለግሱት የማፈኛ መሳሪያ ሆኗል።
ዓለም ቸል ያለው አፈና
ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የተቀበላቸውን የማህበረሰብና የፖለቲካ መብት ህግ፤ ደንብና መመሪያ ፈርማለች (The International Covenant on Civil and Political Rights (ICCPR). አንቀፅ አስራ ዘጠኝ እንዲህ ይላል። “ማንኛውም ግለሰብ የማንም እጅ (የመንግሥት ወይንም ሌላ) ሳይገባበት የራሱን ነጻ ሃሳብ/አስተሳሰብ ለመናገር ይችላል፤ ማንም ግለሰብ የመናገር፤ ራሱን የመግለፅ መብቱ የተጠበቀ ነው፤ ይህ መብት ዜና የመፈለግ፤ የመቀበልና የማስተላለፍ መብትን ይጨምራል፤ ዜናው ገደብ የለውም፤ ወሰን የለውም፤ በቃል፤ በጽሁፍ፤ በመፅህፍ፤ በመፅሄት፤ በስእል፤ በሙዚቃና በሌላ የመገናኛ ዘዴ ሊገለጽ ይችላል።” እነዚህ መብቶች በአብዛኛው ዓለም የተከበሩ ናቸው። ህወሓት እነዚህን መብቶች በምንም አይቀበልም፤ እንዲያውም “ሺሙጥ” የመሰሉ ወይንም ውስጠ ወይራ የሆኑ የህወሓትን መሪዎች የሚመለክቱ ነገሮች ሲወሩ ወይንም ሲነገሩ፤ ወይንም ሲጻፉ፤ “የግለሰብ ክብር ነክታችኋል” ብሎ ይከሳል። የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ኮሚቴ ያወጣውን መመሪያ ዋጋ አልሰጠውም ማለት ነው። “States have the responsibility to ensure that defamation laws must be crafted with care to ensure that they do not serve, in practice, to stifle freedom of expression… መንግሥታት መጠንቀቅ ያለባቸው የግለሰብ ክብር የሚነኩ ህጎችን ሲያወጡ፤ ህጉን የፖለቲካ መሳሪያ አድርገው የሰብአዊ መብቶችን እናዳያፍኑ ነው” ይላል። ህወሓት ያወጣው የፀረ-ሽብርተኛ ሕግ የሚያገለግለው ሰብአዊ መብቶችን ለማፈን ሆኗል። ማንኛውም ተቃውሞ ወንጀለኛነት ሆኗል። ማንም ተቃዋሚ ግለሰብ በዚህ ሕግ ሊከሰስ፤ ሊፈረድበት ይቻላል ማለት ነው። ሕጉ የገዢው ፓርቲ የፖለቲካ መሳሪያ መሆኑ ምንም አያከራክርም። የህወሓት መንግሥት ዓለም አቀፍ ህጎችን አክብሮ አያውቅም። ራሱ ከሳሺ፤ ራሱ ማስረጃ አቅራቢ፤ ራሱ ዳኛና ፈራጂ፤ ራሱ አሳሪ ነው።
የታወቀው የሰብአዊ መብት ጠበቃ ድርጂት (Human Rights Watch) በቅርቡ ባወጣው “Journalism is not a crime: violations of media freedom in Ethiopia, January 22, 2015, እንዲህ ይላል “የኢትዮጵያ መንግሥት በነጻነት (ከመንግሥት ቁጥጥር ውጭ) የሚንቀሳቀሰውን የመገናኛ ብዙሃን ፍጹም በሆነና በረቀቀ መንገድ አውድሞታል። ስለሆነም የፖለቲካና የመናገር፤ የመጻፍና የማሳተም ነጻነት ምህዳር (ምድር) ጨለማ ሆኗል።” ይኼ ሰርዓት ወለድ ውድመት “የመጣው ከመጭው ምርጫ በፊት ነው። ባለፈው ዓመት ብቻ ስድስት በግል ባለቤትነት ይካሄዱ የነበሩ ማተሚያዎችና የሚያበረክቷቸው ጽሁፎች ተዘግተዋል። ገዢው ፓርቲ እየተከታተለና እያስፈራራ አላሰራቸው ስላለ። ሃያ ሁለት ጋዜጠኞች፤ ብሎገሮች (የኢንተርኔት ጋዜጠኞች) እና አሳታሚዎች በወንጀለኛነት ተከሰዋል። ከሰላሳ በላይ የሚሆኑ ጋዜጠኞች ከመያዛቸውና ከመታሰራቸው በፊት ከሃገር ወጥተዋል።” ይሕ ተቋም ከዚህ ድምዳሜ ላይ የደረሰው በብዙ ማስረጃ ነው። ከ May 2013 እስከ December 2014 ባለው ጊዜ ውስጥ ሰባ የሚንቀሳቀሱና በስደት ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞችን አነጋግሯል። አስራ ዘጠኝ ጋዜጠኞች እንደታሰሩ፤ ስድሳዎቹ እንደተሰደዱ አረጋግጧል። ይኼን ማስረጃ በመጠቀም በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ከኢራን ጋር “ከፍተኛውን የጋዜጠኞች እስር ቤት መሆን ዝና አስመክራለች” ይላል። በነገራችን ላይ፤ ኢትዮጵያ የጋዤጠኞች ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ ተወዳዳሪዎችም እስር ቤት ናት። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቢያንስ አራት መቶ የፖለቲካ እስረኞች እንዳሉ ተቀብሏል። ቁጥሩ ከዚህ በላይ መሆኑን አምኔስቲ ኢንተርናሺናል ባወጣው ዘገባ ተመልክተናል፤ ለምሳሌ አምስት ሺህ የኦሮሞ ብሄረሰብ አባላት መታሰራቸውን። በየጎራው የታሰሩት የፖለቲካ እስረኞች ከስሌቱ መግባት አለባቸው።
ከመንግሥት ቁጥጥር የሆነ (ነጻ) ሜዲያ የሚባለው ለሰብአዊ መብቶች መከበር፤ ለነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ሂደት ወሳኝ ነው። ያልተበረዘ፤ ያልተደለዘ ዜና ለሕዝብ ተሳትፎ ቁልፍ ነው። በመንግሥት ቁጥጥር የተያዘው መገናኛ ብዙሃን ለሕዝብ የሚያቀርበው ዜና የገዢውን ፓርቲ ታላቅነት፤ የልማትን አስደናቂነትና ህይወት ለዋጭነት፤ የተቃዋሚውን ኃይል ደካማነት፤ የነጻ ጋዤጠኞችን አክራሪነት፤ ሽብር ቀስቃሽነት፤ ፀረ- ሕገ መንግሥትነት ወዘተ ነው። ልክ እንደ ምርጫ ቦርዱ የገዢው ፓርቲ አገልጋይ ነው። የመንግሥት ጋዜጠኛ እድገትና የደሞዝ ጭማሬ ከፈለገ ለህወሓት ታዛዢ መሆን ግዴታው ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ አስተምሮና አሰልጥኖ ሊያገለግሉት የሚችሉ ጋዜጠኛች በእስር ቤት ወይንም በስደት እንዲኖሩ ከተገደዱ የህወሓት የጨለማ አገዛዝ ይቀጥላል ማለት ነው። የሂውማን ራይትስ ዋች ምክትል ሃላፊ እንዲህ በማለት እውነቱን አስቀምጣዋለች። “የኢትዮጵያ ከመንግሥት ቁጥጥር ውጭ የሆነ መገናኛ ለመጭው ምርጫ ቁልፍ የሆነ ሚና ሊጫወት ይችል ነበር፤ ሆኖም የኢትዮጵያ መንግሥት መንግሥትን የማይደግፉ ጋዜጠኞች አንድ ሃተታ ቢያቀርቡ የሚከተለው ውጤት እስር ቤት እንደሚሆን ያውቃሉ።” ተወዳዳሪ ፓርቲዎችም የገጠማቸው ችግር ተመሳሳይ ነው። እንደ ልብ ለመንቀሳቀስ፤ ለመሰብሰብ፤ ሕዝብን ለመቀስቀስ አለመቻል። “ነጻ የሆነ ድምፅን በፀረ-ሽብርተኛነትና ሌላ የተፈጠረ ምክንያት ማፈን ኢትዮጵያ የነጻ ሃሳብ ሲኦል እንድትሆን አድርጓታል። Ethiopia’s government has systematically assaulted the country’s independent voices, treating the media as a threat rather than as a valued source of information and analysis….Muzzling independent voices through trumped-up criminal charges and harassment is making Ethiopia one of the world’s biggest jailers of journalists.” በተመሳሳይ፤ የህወሓት መንግሥት ተወዳዳሪ የፖለቲካ መሪዎችንና አባላትን እያሳደደ፤ የፈጠራ ማስረጃ እየተጠቀመ አስሯል፤ እንዲሰደዱ አድርጓል። የሚፈልገው ግልፅ ነው። ለኢትዮጵያና ለመላው ሕዝቧ ተቆርቋሪ፤ ተሟጋች፤ ታጋይ እንዳይኖር ለማድረግ። የኢትዮጵያዊያን በገፍ መሰደድ ለህወሓት በገንዘብ የማይገዛው ክፍተት ፈጥሮለታል። ተቆርቋሪ ከሌለ አምባገነናዊነት፤ ድርጂታዊ ምዝበራ ወዘተ ይቀጥላል። የሩቅ አቤቱታ ብቻውን አገርን አይታደግም። ስደተኛው ቢያንስ ለሃገሩ፤ ለወገኑ፤ ለክብሩና ለህሊናው ሲል አገር ቤት የሚንቀሳቀሱትን፤ የታሰሩትን፤ የተሰደዱትን ወገኖቹን መርዳት አለበት፤ ቢያንስ በውጭ ድምፁን ማሰማት አለበት፤ አለበለዚያ የታሪክ ተጠያቂ መሆኑ የማይቀር ነው፤ በሃገሩ ሕዝብ መናቁ የማይቀር ነው፤ “ለራሱ ጥቅም ቋሚ” መባሉ የማይቀር ነው። አገሪቱ ከፈረሰች የሰራውን ቤት ሊጠቀምበት አይችልም። አደጋው እስከዚህ ደርሷል።
የህወሓት መንግሥት የማስፈራሪይ ዱላው ብዙ ነው። ለምሳሌ፤ ስራ ለማግኘት፤ የመሬት ምሪት ፈቃድ ለማግኘት ወዘተ የፈለገ ግለሰብ ለህወሓት ታማኝ መሆን ግዴታው። በአንዳንድ ታዛቢዎች አነጋገር፤ የግል ጥቅምን ለማስተናገድ “ወያኔ መሆን” አስፈላጊ ነው፤ ራስን ለጥቅም መለወጥ ማለት ነው። “ወያኔ ያልሆነ ወይንም የወያኔን ዓላማ ያልተቀበለ በመንግሥት መስሪያ ቤት ሊቀጠር አይችልም” የሚሉ ብዙ ናቸው። “አልሆንም፤ ከጥቅሜ ነጻነቴን፤ ክብሬን፤ ህሊናየን፤ አገሬን፤ ወገኔን እመርጣለሁ” ያሉ ግለሰቦች በሰላም ለመኖር አይችሉም።” ጋዜጠኞች በተለይ። የሚፅፉት ነገር ህወሓትን የሚገስፅ ከሆነ የጻፉት ይቃጠላል። ህወሓት በአንድ ወቅት ብቻ አርባ ሺህ እትሞችን አቃጥሏል፤ ፀሃፊዎችን በወንጀለኛነት ከሷቸዋል፤ አስሯቸዋል። በጋዜጠኞች የደረሰው ፍዳ በማህበረሰብ ድርጂቶች ላይ ተፈጽሟል። The Charities and Societies Proclamation of 2009 is a prime example of a blunt political instrument that decimated civil society in Ethiopia. የመንግሥት ያልሆኑ አገልግሎት የሚሰጡ የማህበረሰብ ድርጅቶች ተደምስሰዋል። በምትካቸው ለህወሓት የሚያገለግሉ ድርጅቶች ተቋቁመዋል። ከላይ በተጠቀሰው ድርጂት አባባል “Unfortunately, what little space there was for independent coverage and political expression and analysis of news and political events has shrunk even further in 2014.” ኢትዮጵያዊያን ልዩ ልዩ ሰላማዊ አማራጮችን ለማስተናገድ ያላቸው እድል ተዘግቷል። ይኼ የህወሓት ጭፍን አፈና ለእድገትና ልማት ማነቆ መሆኑን አሳይቻለሁ። ሂውማን ራይትስ ዋች እንደደመደመው፤ “የኢትዮጵያ መሪዎች ማስተዋል ያለባቸው ህያውና ነጻ የሆነ የመገናኛ ብዙሃን፤ ጎልማሳና ነጻ የሆነ የማህበረሰብ እንቅስቃሴና ተወዳዳሪ የፖለቲካ ድርጅት (ድርጅቶች) ለሃገሪቱ እድገትና ልማት ወሳኝ ናቸው።” የሰብአዊ መብቶች መከበር የፖለቲካ ስልጣን ከመካፈል በላይ ነው፤ ለእድገትና ልማት፤ ለሳልማ እርጋታ፤ አብሮ ለመኖርና አብሮ ለማደግ ወሳኝ ነው።
ምን ይደረግ?
ሒውማን ራይትስ ዋች የሰብአዊ መብቶች መታፈን አደጋ በትንተና ብቻ አልተወም፤ ለውጦችን ሰንዝሯል፤
የህወሓት መንግሥት የተጠየቀው
1. በጋዜጠኞች፤ የኢንተርኔት ፀሃፊዎች (ብሎገርስ) ላይ የቀረበው ክስ ይነሳ፤ የታሰሩት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ይፈቱ፤
2. የፀረ-ሽብርተኛው ሕግ ይወገድ፤ የመገናኛ ብዙሃን ነጻነት ይከበር፤ ይኼን የሚያግቡ መመሪያዎች ይነሱ፤
3. የወንጀለናነት አንቀፅ ስድስት መቶ አስራ ሶስት፤ በተለይ፤ ማዋረድ (ዲፌሜሽን) የሚለው አከራካሪ ሕግ ይነሳ፤
4. መንግሥት በመገናኛ ብዙሃን–ሬዲዮ፤ ቴሌቪዢን፤ ማተሚያ ቤት–ያለው ድርሻ ይቀነስ፤
10
5. የጋዜጣ፤ የሬዲዮ፤ የህትመትና ሌሎች ስርጪቶች ደንቦች ከፖለቲካ ቁጥጥር ውጭ ይሁኑ፤ 6. የኢትዮጵያ ዜና ማስራጫ ድርጅት አመራር ይለወጥ፤ ነጻ ብሄራዊ አገልግሎት ይስጥ፤
7. ገዢው ፓርቲ በነጻ የአገር ውስጥና የውጭ ጋዜጠኞች እንቅስቃሴ ላይ የሚያደርገውን መከታተል፤ አፈና ያቁም፤
8. መንግሥት በድህረ ገጾች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች፤ ጋዤጠኞች፤ ብሎገሮች ላይ የሚያደርገውን አፈና ያቁም፤ እንዳይደገም ለኢትዮጵያዊያንና ለዓለም ሕዝብ ቃል ይግባ፤
9. በውጭ ሬዲዮ፤ ቴሌቪዢንና ሌሎች መገናኛ ብዙሃን ላይ የሚደረገው ገደባ ይቁም፤ መንግሥት ይኼን እንዳያደርግ ቃል ይግባ
10. መንግሥት እስካሁን እምቢ ያለውን የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ካውንስል ልዩ ፀሃፊ ወይንም ራፖርተር ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጣ ይጋብዝ፤ የመብቶችን ጉዳይ በሚመለከት እንደልቡ እንዲንቀሳቀስ ቃል ይግባ። ዘገባውን በይፋ ያውጣ።
ለጋስ ድርጅቶች፤ ተቋማትና መንግሥታት፤ የአውሮፓ የጋራ ማህበርና አሜሪካ
1. በይፋና በግል የታሰሩ ጋዜጠኞች፤ ብሎገሮችና የፖለቲካ ተቃዋሚ እስረኞች እንዲፈቱ መወትወት፤
2. የፖለቲካ ፍርድ አሰጣጥን፤ ሂደትን በቅርብ መከታተል፤ የዓለም ሕግ እንዳይጣስ ማሳሰብ፤
3. እስር ቤቶች ለታዛቢዎች ክፍት እንዲሆኑ ማሳሰብ፤ መከታተል፤ ተግባራዊ እንዲሆኑ ጫና ማድረግ፤
4. በይፋ ሆነ በግል ለመንግሥት ባለስልጣናት የመናገርና ሌሎች መብቶች መታፈን ለልማት፤ ለሰላም፤ ለደህንነት፤ ለእርጋታ ማነቆ መሆናችውን በግልፅ መናገር፤
5. ከመንግሥት ቁጥጥር ውጭ ለሆኑ መገናኛ ብዙሃን፤ የማህበረሰብ ድርጅቶች የአቅም ግንባታ ድጋፍ መስጠት፤
6. ከመንግሥት ቁጥጥጥር ውጭ የሆኑ ጋዜጦች፤ መፃህፍት፤ የማሳተሚያ ተቋሞችን የመጠቀም መብታቸው እንዲከበር ጫና ማድረግ።
ለትንተናውና ለቀረቡት የለውጥ ሃሳቦች የረዱ ሂደቶች፤ ትንተናዎች
1. የመገናኛ ብዙሃኑን መስክ ወይንም ሜዳ መፈተሽ፤
2. ገዢው ፓርቲ በሚዲያው ላይ ያደረገውን አፈናና ማፈራረስ መመርመር፤
3. ከህግ ውጭ ማሳደድ፤ መክሠስ፤ መደብደብ፤ ማሰር እንዴት እንደሚካሄድ ማስረጃ መሰብሰብ፤
4. መረጃ የሚሰጡ ግለሰቦችን መሰብሰብ፤ ማነጋገር፤ ሰላዮች ለፖሊስ፤ ለደህንነት የሚሰጡት የፈጠራ መረጃ እንዴት እንደሚሰበሰብ መፈተሽ፤ ማመሳከር፤
5. የተቃዋሚ ፓርቲዎች የህወሓት አፈ ቀላጤ ናችው የሚሏቸውን እንዴት እንደሚያስፈራሩ፤ ለምን እንደሚያስፈራሩ መገምገም፤
6. የመገናኛ ብዙሃን ህጎች፤ ደንቦችና መመሪያዎች ምን ያህል የፖለቲካና የጎሰኛነት መሳሪያ እንደሆኑ ማመዛዘን፤
7. ህወሓት ለማስፈራሪያና ለማቫበያ የሚጠቅምባቸውን መሳሪያዎች መመርመር፤ ለምሳሌ፤ አንድ ቃሉን የሰጠ ጋዜጠኛ የፖለቲካውን ማቫበያ እንዲህ ሲል ገልጾታል። የፓርቲው አባል ከሆነክ “የተሻለ ስራና ደሞዝ ይከፈልሃል።” ታማኝነት ለስራ ማለት ነው።
8. የግል መገናኛ ብዙሃንን ገንዘብና ትርፍ መፈተሽ፤ ህወሓት አትራፊ የሆነው ሰው ወይንም ተቋም “ተጨማሪ ቀረጥ መክፈል አለብህ፤ ካልከፈልክ ተቋምህ ይዘጋል” ብሎ ያስፈራራል፤ ካፒታልም ከየት እንዳገኘ ይጠይቃል። ይኼን መፈተሽ።
9. የዜና ምንጮችን የማፈን ዘዴዎችን መመርመር፤ ህወሓት “ማን ከየት ዜና እንዳገኘ ይከታተላል።”
10. ህወሓት ጋዜጠኞች እውነቱን እንዳይፅፉ ራሳቸውን እንዲያግቡ ያስገድዳቸዋል (Self-censosrhip). “If you are a journalist, you censor everything you do. If you don’t, you become a prisoner or flee.”
11. ህወሓት ከውጭ የሚሰራጩ የሬዲዮ፤ የቴሌቪዢንና የድህረገፅ ትንተናዎችና ሃሳቦችን በተከታታይ ያግባል፤ እነዚህ እንዴት እንደሚታገቡ መመርመር፤
12. ህወሓት በሶሻል (ማህበረሰብ) የሚተላለፉ ዜናዎችን፤ ትችቶችን ይከታተላል፤ ክትትሉ በምን ዘዴ እንደሚካሄድ መመርመር፤ ማስረጃ መሰብሰብ፤
13. ጋርዲያን እንዳለው በሃገር ቤትና በውጭ በየዓመቱ ብዙ መቶ ሚሊዮን ዶላር ወይንም በብዙ መቶዎች የሚታሰብ ብር ፈሰስ እያደረገ ስለላ ስለሚያካሂድ ይኼ በሰብአዊ መብቶችን ላይ ያለውን ጫና መመርመር፤ ማስረጃ መሰብሰብ የሚሉ ናቸው።
ለመጨመር የምፈልገው የካናዳ መንግሥትና የአውሮፓ የጋራ ማህበር ለህወሓት መንግሥት ያቀርቧቸውን ከላይ ያልተጠቀሱትን ነው።
1. የፖለቲካ ምህዳሩ በአስቸኳ መከፈት አለበት የሚል፤
2. የፖለቲካ እስረኞች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ይፈቱ የሚል፤
3. የመንግሥት ሜዲያ ለሁሉም ተቃዋሚ ፓርቲዎች ይለቀቅ የሚል፤
4. የምርጫ ቦርዱ የገዢው ፓርቲ መሳሪያ መሆኑ አቁሞ በዓለም በተለመደው መንገድ አድሏዊ የሆነ ስራ እንዳይሰራ፤ ሁሉንም ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ያገልግል የሚል፤
5. ፖሊስ፤ መከላከያና ፍርድ ቤቶች በምርጫ ሂደት ጣልቃ ገብተው የፓርቲው አገልጋይ መሆናቸውን እንዲያቆሙ የሚል፤
6. ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ከተካሄደ የአገር ውስጥና የውጭ ታዛቢዎች ያለምንም ገደብ ለመንቀሳቀስ እንዲችሉ የሚል ይገኙበታል።
መደምደሚያ
የኢትዮጵያ ሕዝብ እድለኛ ከሆነ መብቶቹ እንዲከበሩ ከተፈለገ፤ ህወሓት ከላይ የውጭ ታዛቢዎች ያቀረቧቸውን ምክሮች ሰምቶ ለሰብአዊ መብቶች መከበር አስፈላጊነትና ተቀዳሚነት ትኩረት ይሰጥ ነበር። ራሱ የሶቨሪን ቦንድ ፕሮጀክት ለዓለም ገበያ ሲያቀርብ እንዳሳሰበው፤ መጭው ምርጫ ነጻና ፍትሃዊ ካልሆነ ለማንም የማይጠቅም፤ የእርስ በእርስ ግጭት ሊነሳ ይችላል። ይኼን የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆነ የዓለም ሕዝብ፤ በተለይ ተደማጭነት ያላቸው አበዳሪ ድርጅቶችና የገዢው ፓርቲ ወዳጅ መንግሥታት በፍጥነት ሊያስቡበት ይገባል። ዛሬ ህወሓት የሚያደርገው ጭካኔ ለሃገሪቱና ለመላው ሕዝቧ በጣም አደገኛ ነው። ለጋስ ድርጅቶችና የምእራብ መንግሥታት፤ በተለይ አሜሪካና እንግሊዝ ለራሳቸው ዘላቂ ጥቅም ሲሉ የኢትዮጵያን ሕዝብ የፍትህ፤ የነጻነት፤ የሕግ የበላይነት፤ የዲሚክራሲ ጥያቄዎች መደገፍ ግዴታቸው ነው። ሂውማን ራይትስ ዋች ለኢትዮጵያ ሕዝብ መብቶች መከበር የተቀደሰና ታሪክ የመዘገው አስተዋፆ አድርጓል። ይኼን እንደ ተራ ጉዳይ ማየት የለባቸውም።
መጭው ምርጫ አራት ወራት ብቻ ቀርቶታል። “ተአምር” ካልመጣ በስተቀር፤ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች (በምርጫ የሚያምኑ የፖለቲካ ድርጅቶች) የደረሰባቸውን አፈና፤ ማሳደድ፤ እስራት ወዘተ ተወጥተው በምርጫው ለመሳተፍ በጣም አስቸጋሪ ይሆንባቸዋል። ቅድመ ሁኔታዎቹ አመች አይደሉም። አፈናው ከመቸውም በበለጠ ደረጃ በመካሄድ ላይ ነው። ስለሆነም፤ ባለው “ጨለማ” በሆነ የፖለቲካ፤ የመገናኛ ብዙሃን፤ የማህበረሰብና ሌሎች የሰብአዊ መብቶች ፍፁም በሆነ አፈና ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ ነው።
ተወዳዳሪ ፓርቲዎች ሌላ ቀርቶ ሕገ መንግሥቱ የሚፈቅደውን የሰላማዊ ሰልፍ መብት ተጠቅመው ለመንቀሳቅስ አልቻሉም። እንዲያውም ሰልፉ ከመካሄዱ በፊት የተቃዋሚ ፓርቲዎች መሪዎችንና አባላትን ማፈን፤ በዱላ መደብደብና ማሰር የባሰ ሆኗል። ህወሓት ተጠላፊ ድርጅቶችን እየፈጠረ የሚያደርገውን ሴራ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያውቀዋል። ሆኖም፤ ሕዝቡን ንቆታል ለማለት ያስደፍራል። ይኼ ህብረ ሕዝብ የሆኑ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ለማዳከምና ለማፍረስ የሚደረግ ሴራ መሆኑ ግልፅ ነው። እነዚህ ተወዳዳሪዎች አገር አቀፍ የሆነ ተደማጭነት ባይኖራቸው ህወሓት የምርጫ ቦርዱን እየተጠቀመ፤ የተቀጥላ ድርጅቶች እየፈጠረና ሰርጎ እየገባ ሊያፈራርሳቸው ባልወሰነም ነበር።
የምርጫ ቦርዱ ዓለም የሚቀበለውን መመሪያ አይከተልም፤ የህወሓት አገልጋይና የተወዳዳሪ/ተቃዋሚ ድርጅቶች አፍራሽ ክንድ ሆኗል። የሚሰራው ህወሓት የሚሰጠውን ፍፃሜ ላይ ማድረስ ነው። ምርጫው ሳይካሄድ እንደዚህ ከሆነ በሰላም የሚደረገው “ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ” ፍጹም ቀልድና ጨዋታ ሆኗል ማለት ነው። ለሃገሪቱ አደገኛ የሚሆነው የሰላሙ አማራጭ ዝግ ከሆነ፤ የመግቢያ ቀዳዳ ለሚፈልጉ ለኢትዮጵያ ጠላት መንግሥታት ክፍተት ይፈጥራል። ዙሮ ዙሮ የሰብአዊ መብቶች መከበር የሚያገለግለው የተቃዋሚውን ኃይልና የኢትዮጵያን ሕዝብ ብቻ አይደለም። ህወሓት/ኢህአዴግን ጭምር ነው።
January 26, 2015

Montag, 26. Januar 2015

ህወኃት ፀገዴ ላይ ያካሄደው ስብሰባ ከሸፈ

የትግራይ ነፃነት ግንባር /ህወኃት/ ገና ከፅንስሱ ሲነሳ ለሙን የሰሜን ወሎን፣ ምዕራባዊ ጎንደርን እና ምዕራባዊ ጎጃምን በማካተት ታላቁን የትግራይ ሪፐብሊክ መመስረት ግብ አድርጎ መመስረቱና ለዚህም አላማው ስኬት የቻለውን ሁሉ በማድረግ ላይ እንድሚገኝ የሚታወቅ ነገር ነው።
welkaiytበተለይም በወልቃይት፣ ፀገዴና አርማጭሆ ያካሄደው መስፋፍት በአካባቢው ነዋሪ ህዝብ ላይ ትውልድ ይቅር የማይለው ግፍ ፈጽሟል፡ አሁንም የመስፋፋት ህልሙን እውን ለማድረግና ቀሪ የአማራን መሬት ለመቆጣጠር ያለማቁአረጥ ጥረት እያደረገ ነው። ከላይ በተጠቀሱት አካባቢወች የሚኖረውን የአማራን ህዝብ በማንበርከክ እኩይ ፍላጎቱን ለማስፈፀም ቀደም ሲል የጎንደር አስተዳደር ከተሞች በነበሩና አሁን በጉልበት ወደ ትግራይ በተወሰዱ ሁመራ፣ ማይካድራ፣ ማይፀብሬ፡ ዳንሻ፣ ማክሰኞ ገበያ/ ንጉስ ከተማ/ና ዲቪዥን የተባሉ ከተሞችን ማዕከል በማድረግ በአካባቢው የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆችን በተለይም ምልስ የህወኃት ወታደሮችን በመመልመል ከሃምሌ 2006 እስከ መስከረም 2007 ለሶስት ወር የዘለቀ በሁመራ ከተማ ለ120 ሰወች ልዩ የስለላና የአፈና ስልጠና የተሰጣቸው ሲሆን በፀለምት ዲቪዥን ከተማና በዳንሻ ከተማ በያንዳንዳቸው 1500 የሰው ሃይል ለፀጥታ ስራ በሚሊሻነት አሰልጥኗል። በተጨማሪም በማይካድራና ንጉስ ከተሞች በያንዳንዳቸው 1000 የሰው ሃይል ለተመሳሳይ አላማ አሰልጥኗል። በአጠቃላይ ተከዜን ተሻግረው ከሚኖሩት ትግሬወች 5120 ተመልምለው ለሶስት ወር የዘለቀ ስልጠና ወስደው መደበኛ ደመወዝም ተመድቦላቸው ለተጨማሪ የመስፋፋት አላማቸው አዝጋጅተው አሰማርተው እንደነበር በወቅቱም ታውቆ ነበር። እነዚህ ለአፈናና ለግድያ የሰለጠኑ ሃይሎች አሁንም ተደራጅተው ለህወኃት እየሰሩ ያሉ ናቸው።

ይህንኑ ዝግጅታቸውን እንዳጠናቀቁ ከባለፈው ታህሳስ 17 ጀምረው በርካታ የፀጥታ ሃይል ከሌሎች አካባቢወም በመጨመር ህወኃት በሰሜናዊ ምዕራብ ጎንደር ላይ ሰፊ የመስፋፋት ዘመቻ ከፍቶ እንደነበረና በአካባቢው ህዝብ የተደራጀ ትግል ያሰበውን ሳያሳካ መቅረቱ ይታወሳል። ድርጅታችን የአማራ ዴሞራሲያዊ ሃይል ንቅናቄም ከህዝቡ ጎን በመሰልፍ ተስፋፊውን የህወኃት ቅጥረኛን ከመፋለምም በተጨማሪ ወቅታዊ መረጃወችንም ለህዝብ በማድረስ ወሳን ሚናውን ተወትቷል ፣ አሁንም እየተወጣ ይገኛል።

ህወኃት ያሰበውን የቅዠት ህልሙን ለማሳካት የጀመረው መንገድ ከአካባቢው ህዝብ ባጋጠመው ተቀዋውሞና ትግል ትልቅ ፈተና እንደገጠመው ስላወቀ አላማውን ለማሳካት በአሁኑ ሰዓት ሁለት አይነት ዘዴወችን ቀይሷል።

1ኛ. የፌደራል መንግስቱ ጣልቃ ገብቶ እንዲወስን በማድረግ አካባቢውን መቆጣጠር ነው፣ ለዚህም ጥር 04/05/07 ፀገዴ ወረዳ ማክሰኞ ገበያ ከተማ ላይ ከፀገዴና አካባቢው ህዝብ ጋር ትልቅ ስብሰባ ተካሂዷል። በስብሰባው የተገኙ 1, ዶ/ር ሽፈራው ተክለማሪያም 2. አባይ ወልዱ 3. ተወድሮስ ሃጎስ 4. ገዱ አንዳርጋቸው 5. ሌ/ጅ ብርሃኑ ጁላ /የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ/ 6. ሜ/ጅ ገብረግዛብሄር መብራቱ /የመከላከያ ዘመቻ ሃላፊ/ እና ሌሎችም ነበሩ። በዚህ ስብሰባ ህዝቡ በአንድ ቃል እኛ አማራ ነን እንጅ ትግሬ አይደለንም የትግሬና የጎንደር ደንበር ተከዜ ነው ትግሬ ተከዜን ተሻግሮ ግዛት ሊኖረው አይገባም በሚል ቁጣ ባዘለ መልኩ ነግሯቸዋል። ህወኃቶቹ እነ አባይ ወልዱም በሁኔታው መበሳጨታቸው የታወቀ ሲሆን የደላንታው ተወላጅ ገዱ አንዳርጋቸው ህዝቡ ያነሳውን እና ያራመደውን ሃሳብ ደግፏል፡ የህዝቡን ውሳኔ ማክበር አለብን በማለት ከህወኃቶች ጋር ትልቅ ልዩነት መፍጠሩ ሲታወቅ፣ መግባባት ባለመቻላቸው ጉዳዩን ፌደራል ጣልቃ ገብቶ ይይልን ሲሉ ህወኃቶች ባቀረቡት ሃሳብ ተግባብተው ስብሰባው ተጠናቁአል። አሁን አካባቢው ብዙ የፌደራል የፀጥታ ሃይል የተከማቸበት ሲሆን ከፌደራል መንግስቱም የሚጠበቅ ነገር ስለለለ ህዝቡ ለነፃነቱ ለሚያደርገው ትግል በተለየ መንገድ እየተዘጋጀ ሲሆን ድርጅታችንም ይህንኑ በማጠናከር ትኩረት አድርጉኣል።

2ኛ. በጎንደር ክ/ሃገር የሚኖሩ የቅማንት ማህበረሰብን የማይገባ የፈጠራና ልብወለድ ታሪክ በመንገርና አንዳንዶቹንም በጥቅም በማታለልና በማሳሳት በፀረ-አማራነት እንዲሰለፉ እያደረገ ነው። ይህ ተንኮል ቀደም ብሎ ጀምሮ በደንብ ታስቦበት ሲሰራበት እንደቆየ ሁኔታውን በቅርብ የሚከታተሉ ሃይሎች ያውቁታል። ህወኃት አሁን ላይ የገንዘብና የስልጣን አቅሙን በመጠቀም የቅማንት ማህበረሰብን ዘራችሁ ከትግሬ እንጅ ከአማራ አይደለም መጀመሪያ የራሳችሁን አስተዳደር መስርቱና የራስን ኣድል በራስ የመወሰን መብታችሁን ተጠቅማችሁ ወደ ዘራችሁ ወደ ትግራይ ትካለላላችሁ በማለት የመስፋፋት ህልሙን እውን ለማድረግ በሌላ መንገድ ተግቶ እየሰራ ነው።

ሁኔታው የሚመለከታችሁ ወገኖቻችን ሁሉ ይህ በጎንደር ነዋሪ ህዝብ ላይ እየተካሄደ ያለው ግፍና በደል የጎንደር ብቻ ሳይሆን የአማራው የጋራ ጥቃትና የኢትዮጵያዊያንም በደል ነው። ስለሆነም በጉዳዩ ላይ መነጋገርና በመፍትሄው ላይም መተባበር የሁላችንም ግዴታ እንዲሆን ያስፈልጋል።
- See more at: http://satenaw.com/amharic/?p=4115#sthash.kGuppVZ0.dpuf

የደደቢት ጉዞ መዘዝ፤ ከሰራዊት ፍቅሬ እስከ ታገል ሰይፉ

ክንፉ አሰፋ (ጋዜጠኛ)
በመጀመርያ ዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) ደጋፊና ተደጋፊ የኪነጥበብ ባለሙያዎችን በሙሉ ጠሯቸው። ሰበሰቧቸው። እንዲህም አሏቸው። “ወደ ደደቢት አብራችሁን ትሄዳላችሁ፤ እዛ እንደደረሳችሁም አመጣጣችንንና አካሄዳችንን በደንብ አድርጋችሁ ታጤናላችሁ። ከዚያ ስትመለሱ ሁሉንም ነገር ለህዝቡ ትናገራላችሁ።…”       
በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የሃገር መሪ ሆነው የሚሰሩት እኝህ ሰው መልዕክታቸውን በዚህ አላበቁም። አይናቸውን ፈጠጥ፤ ጉሮሯቸውንም ጠረግ-ጠረግ አደረጉና ንግግራቸውን ቀጠሉ “ስለረጅሙና መራራው ትግላችን፤ ከጅምራችን እስከ አያያዛችን የታዘባችሁትን ሁሉ ንገሩን። ጥሩውንም ይሁን መጥፎውን ነገር ሳትደብቁ ተናገሩ።…”
serawit fikre
ድምጻዊው በዝማሬ፣ ጸሃፊው በድርሰት፣ ተዋንያኑ በተውኔት ስለ ህወሃት የአርባ አመት ጉዞ እንዲመሰክሩ የተሰጠች ትእዛዝ መሆንዋ ነው። አጭር፣ ግልጽ እና ቀጭን መልዕክት ነበረች።
       የስርዓቱ ደጋፊ ሳይሆን ይልቁንም ተደጋፊ የሆኑት ሁሉ የዘመቻውን ጥሪ በደስታ ተቀበሉ። ወደ ደደቢትም አመሩ። የታዘቡትንም ነገር ሲናገሩ ሰማን።
ልብ እንበል! እነዚህ የጥበብ ሰዎች ናቸው። ጥበብ ደግሞ የሕዝብ አገልጋይ ናት። ጥበብ ለእውነት የምትቆም ዘብ ናት። ጥበብ አንድን ህብረተሰብ የመቅረጽ እና የመለወጥ ሃይል አላት።
በአለማችን የጥበብ ሰዎች ሚና ጎልቶ የሚታየው ተፈጥሮ ባደላቸው የጥበብ ስራ ብቻ ሳይሆን፤ እነዚህ ሰዎች በጥበብ ስራቸው ውስጥ ለህዝብ በሚያስተላልፉት እውነተኛ መልእክትም ጭምር ነው። 
አርቲስቶች አክቲቪስቶች መሆን አለባቸው ብሎ መከራከር አይቻልም። ይህ የራሳቸው ምርጫ ነው። መሆን ካለባቸው ግን የህዝብን እንባ ማበስ ነው የሚገባቸው። ወቅቱን ጠብቆ እንደሚቀየር ድሪቶ መንግስት ሳይሆን ከህዝብ ጎን መቆም ያስከብራቸዋል።
ጥበብ ቆራጥነትን ትጠይቃለች። መስዋዕትነትን ልታስከፍልም ትችላለች። ፍሬዋ ግን ሁል ጊዜ ጣፋጭ ነው። እውቁ ቻይናዊ አርቲስት አይ ዌዊ እዚህ ላይ ይጠቀሳል። አሜሪካዊቷ ጁዲ ችካጎም እንዲሁ። ጃማይካዊው ቦብ ማርሌይ እና የናይጄርው ፌላ ኩቲ በአለማችን ላይ ለውጥ ያመጡ የጥበብ ጀግኖች ናቸው። የኛዋ አርቲስት አስቴር በዳኔም ለዚህ ዋቢ ነች። ማህበራዊ ድረ-ገጾች ይህንን አስረግጠውልናል።
  “ህዝቡ አጎብዳጆች ይለናል።” አለች አርቲስት አስቴር በዳኔ ከዚያ ሁሉ መንጋ ተነጥላ። ‘እውነት ነጻ ያወጣችኋል!’  የሚለው ክርስቶሳዊ አባባል የተዋሃዳት ወጣት። እውነትን ተናግራ ራስዋን ነጻ አወጣች። እርግጥም የህሊና ነጻነትዋን ለማወጅ መድፈር ነበረባት። ማማጥም ነበረባት። አርቲስትዋ እንደጦር የፈራችው ከፊትዋ ተደርድረው የነበሩ ጉምቱ ባለግዜዎች አልነበሩም። ምክንያቱም ጉዳዩን ለነሱ አስቀድማ ተናግራ ነበርና። ይልቁንም ከአጠገብዋ የነበሩ የስራ ባልደረቦችዋ እና የሙያ አጋሮችዋ እንደጦር ያስፈራሉ። እንደ ይሁዳ አሳልፈው ሊሰጧትም ይችላሉ። ደደቢት ላይ ሲደርሱ ሁሉም በአንድ ማሰብ ጀመሩ። ደደቡ… አንድ ግዜ ተኑሮ ለሚሞትበት አለም ሁሉም ከራሱ ተጣላ። ሁሉም ከህሊናው ሸሸ። ሁሉም ለማደር አጎብዳጅ ሆነ። በመጨረሻም ሁሉም አስቴርን በአርባ ክንድ ራቁዋት። ግና እስዋ ጣርያ ስትነካ እነሱ ደግሞ ሲዘቅጡ አየን።
የኪነ-ትበብ ሰዎቻችንን መፈተኛ ግዜ ብቅ አለ። ግን ይህ ሁሉ ወጪ እና ሽርጉድ ለምን አስፈለገ?
ጉዞውን ከመጪው ምርጫ ጋር የሚያያይዙ ወገኖች አሉ። ጉዞውን እንደምርጫ ዘመቻነት ለመጠቀም…። ይህ የዋህነት ይመስላል። ምክንያቱም ህወሃት አንድም ግዜ በምርጫ ዘመቻና ግልጽ በሆነ ውድድር ምርጫ አሸንፎ አያውቅም። ነብሳቸውን ይማርና አቶ መለስ ከነ ስዬ ቡድን ጋር በተለያዩ ግዜ ተናግረውታል። “ህወሃት በስብሷል!” ነበር ያሉት። ላለፉት ፪፫ አመታት ይህ የበሰበሰ ስርዓት ነው ሃገሪቱን እየገዛ ያለው። ይህ የበሰበሰ ስርዓት በምርጫ ሳይሆን የህዝብን ድምጽ በመስረቅ ነው እስካሁን ያለው።
ከምናከብራቸውና ከየምናደንቃቸው የኪነጥበብ ስዎች ውዳሴዎች ሰማን። ነዋይ ደበበም እጅግ አድርጎ ሲረግመው በነበረው ደደቢት ላይ ዘፈነ። እንዲያውም በስሜት ዘፈነ። “የሃገር ነቀርሳዎች” ሲላቸው የነበሩትን እነ ሳሞራን፣ እነ አባዱላን፣ … እያቀፈ … አልረሳም እያለ አቀነቀነ።
tagel
በዚያ የቀውጢ ወቅት ከሰለሞን ተካልኝ ከተቃዋሚ ወገን ወጥቶ ህወሃትን ሲቀላቀል ድምጻዊው ነዋይ ደበበ እንደ እብድ ነበር ያደረገው። ያዙኝ፤ ልቀቁኝ አለ። የንዴት ቃላትን ሁሉ በዘፋኙ ላይ አዥጎደጎደው። “ማሰብ የማይችል ደደብ ሰው!” አለ ነዋይ። ቀጠለናም “ሰለሞን ተካልኝ ስጋ የሚበላ በሬ ነው።” ሲል ድምጻዊውን ከሰብአዊ ፍጡርነት ወደ እንስሣነት ጎራ መድቦት ነበር።
ዛሬ በዚያው መድረክ ላይ አዲስ ትእይንት እያየን ነው። የግዜ ሃዲድ ላይ ሆኖ የሚመለከተው ሁሉ በትዝብት የሚያስቆዝም አሳዛኝ ድራማ፤ አርቲስት ብለን የምንጠራቸው ወገኖቻችን የሚፈጽሙት የፖለቲካ ዝሙት። ነዋይ ደበበ በግዙፉ የሰለሞን ተካልኝን ትከሻው ላይ ለመጠምጠም እጆቹ በጣም ሲረዝሙ በመገናኛ ብዙሃን ተመለከትን። … አጃኢብ አለ ያገሬ ሰው!
አዕምሮ ማሰብ ሲያቆም፣ አንገታቸው አዙሮ ማየት ሲሳነው፣ ልቦናችን የቅርቡን ክስተት ሲዘነጋ፣ የስነ-ልቦና ችግር ነው ከማለት ውጭ ምን ይባላል?
የሰራዊት ፍቅሬ ማጎብደድ ደግሞ ተወዳዳሪ አልተገኘለትም። ይህ ሰው በ ፩፱፹ዎቹ በነበረው የርስ በርስ ውግያ ወታደር ሆኖ ከደርግ ወገን ነበር የተሰለፈው። ዛሬ በሽሬ ሽንፈቱ ላይ ጥሎት የሸሸው የጦር ታንክ ላይ ቆሞ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እጆቹን እያወጣ ደግም ቀለደ። ለካስ ደርግ እንደዚህም አይነት ወታደር ይዞ ነበር ህወሃትን ይፋለም የነበረ? ሰራዊት ፍቅሬ ዛሬ ዝናው ሳይሆን ሃብቱ ጣርያ ነክቷል። አሰልቺ ድምጹና ምስሉ እጅ-እጅ እስኪል በቴለቭዥን እንዲቀርብ በገዢው ፓርቲ ተፈቅዶለታል። ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ የሚውሉ የስርዓቱ በዓላት ቁጥር እጅግ በዝተዋል። የብሄር ብሄረሰቦች ቀን፣ የከተሞች ቀን፣ የአርሶ አደሮች ቀን፣ የአርብቶ አደሮች ቀን፣… ባዛር ለልማት ወዘተ። የማስታወቂያ ወጪው ከዝግጅቱ ወጪ አይተናነስም። ሁሉንም የማስታወቂያ ስራ ለሰራዊት ፍቅሬ ሰጥተውታል። ታዲያ እሱም ገሚሱን ለባለስልጣናቱ ማካፈሉ የግድ ነው። የዚህ ሰው መንቀልቀል ምስጢር ይህ ብቻ ነው። ሰራዊት ፍቅሬ በዚህ ሁኔታ የማስታወቂያ ስራውን በሙስና መስመር ውስጥ አዝልቆታል።
  አንደኛው ተደጋፊም ተነስቶ  “ይህ ነገር በአፍሪካ አንድነት ድርጅት ፊት ለፊት ሃውልት ሊሰራለት ይገባል።” ሲል ተደመጠ። ሰውዬው ይህንን አምኖበት እንዳልተናገረ ሰዎቹም ይገምታሉ። መቼም ለእለት ጉርስ ሲባል እንደዚህ አይነት ለህሊና የሚጎረብጥ ነገር እያደረጉ ከመኖር፤ በልመና መተዳደር ክብር ነው።  
        ከጅምሩ የስርዓቱን አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ሂደት ለመገምገም ወደ ደደቢት በረሃ መሄድም አያስፈልግም። ኢትዮጵያ ዛሬ ከገባችበት መከራ ለማውጣት የህወሃት አነሳስን ማጥናት ምንም ፋይዳ የለውም። መነሻው ጥሩም ይሁን መጥፎ፣ መድረሻው ግን አላማረም። ይህ ስርዓት ሃገሪቱን ባህር አልባ አገር አድርጓታል። የባህር በር የአንድ ሃገር ምስጢርም ነው። ኢትዮጵያ እንደ ማንኛውም ሉአላዊ ሃገር ምስጢር እንኳን የላትም።
ህዝቧም ከአፈናው ሰንሰለት ገና አልወጣም።
       በአመለካከት ልዩነታቸው ብቻ ወገኖቻችን እንደ ጥጃ ሲታሰሩ የደደቢት ተጓዦቹ ይመለከታሉ። ሃሳባቸውን በነጻ የገለጹ ዜጎች የሽብርተኛነት ታርጋ ተለጥፎላቸው በግፍ ሲፈረድባቸው ይሰማሉ።  ኢትዮጵያውያን እንደ ምጽዓት ሲሰደዱ በአይናቸው ይመለከታሉ።  ለነጻነትና ለእኩልነት ታግለን መጣን የሚሉን ደግሞ በአንዲት ጀንበር ሚሊየነር ሲሆኑ ይታዘባሉ። ይህ ሁሉ ሲሆን ታዲያ እንደሙያቸው አንዲት ቃል እንኳን ተንፍሰው አያውቁም። ወደ በረሃው መጓዙ እንደ ሲሲሊው የማፍያ ቡድን ከደደቢት ምሽግ ውስጥ ቃል-ኪዳን ለመግባባት ካልሆነ በቀር ፋይዳው አይታይም።
        “ህዝቧ አጎብዳጆች ይለናል።” አለች አስቴር በዳኔ። ህዝብ ምን እንደሚላቸው የምትሰማው እስዋ ብቻ አይደለችም። ጆሮ ያለው ሁሉ ይሰማዋል።  ይህን እያወቁ ግን አጎብዳጅ ምሆናቸውን ጭራሽ በብሄራዊ ቴሌቭዥን ወጥተው አሳዩን።  
ህዝቡ ብቻ አይደለም። በእርግጠኝነት ለመናገር እነዚያ ባለ-ስልጣናትም አድርባዮቹን ይንቋቸዋል። በባህር ዳሩ የኢህአዴግ ጉባኤ “የኢህአዴግ አባል ለመሆን አንዱና ዋናው መስፈርት አድርባይነት ነው” በማለት አድርባይነትን የፈጠረውና ያስፋፋው ራሱ ህወሃት እንደሆነ ተናግረው ነበር። “አድርባይነት” ስርዓቱን በሚፈታተን ደረጃ መስፋፋቱን ከመግለጻቸውም በላይ አድርባዮቹን እንዴት እንደሚበቀሏቸውም ባህርዳር ላይ መክረዋል።
        ደብረጽዮን ትእዛዙን ሲሰጡ ትንሽም ቢሆን ዲፕሎማት ነበሩ። ከትእዛዞቻቸው መሃል እንዲት እንዲህ የምትል መልእክት ነበረች። “…ችግሮቻችንንም ንገሩን።”
ይህች ሃረግ የኪነ-ጥበብ ሰዎቹ የህዝብን ብሶት በአደባባይ እንዲናገሩ በር ከፋች ነበረች። እነ አበበ ባልቻ ይህችን እድል ተጠቅመው ስለ-ኪነጥበብ መውደቅ እንኳን ትንሽ መልእክት ከማስተላለፍ ይልቅ ልወደድ ባይነትን መረጡ።   ይህን ጥሬ ሃቅ የመናገር ድፍረት ያለው አንድ ሰው ጠፋ። ሁሉም ምስጋናና ውዳሴውን አበዛ። ለማደር የሚደረግ ካንገት በላይ ውዳሴ… መቼም ያሳዝናል።
  በጭምጭምታም እንደሰማነው፤ በደደቢት አንዳች የተለወጠ ነገር የለም። ደደቢት ድሮም በረሃ – አሁንም በረሃ ነው። የአካባቢው ህዝብ ላይም ምንም የሚታይ ለውጥ የለም። ይህ ህዝብ ከሃያ አመታት በፊት የመናገር በብት አልነበረውም።  ይህ መብት አሁን ብሶበት ሕዝቡ የመናገር ብቻ ሳይሆን የውጭ ራዲዮ እንኳን የመስማት መብቱን ተነፍጓል።  
ይህችን ሃቅ የጎበኘ አንድ የኪነ-ጥበብ ባለሞያ እንዴት አስችሎት ዝም ይላል? ይህ የብዙዎች ጥያቄ ነበር። “ስለ እውነት የቆመ አንድ ሰው ይጥፋ?” የሚለው ጥያቄ በህዝብ ዘንድ እየተብላላ እያለ ነበር አስቴር በዳኔ ብቅ ያለችው። ይህች አርቲስት የህዝቡን ጥያቄ ይዛ በድፍረት ወረወረችው። መገናኛ ብዙሃንና ማህበራዊ ገጾችም በዚሁ ጉዳይ ተጨናንቀው ከረሙ።
ለድቅድቅ ጨለማ ትንሽ የብርሃን ፍንጣቂ ትበቃለች እንዲሉ የዚያን ሁሉ የውሸት ክምር አንድ እውነት አፈራረሰው። ህዝብ ያከብራቸው የነበሩ የኪነጥበብ ባለሞያዎች ሁሉ ወረዱ። የማያልፈውን የህዝብ ፍቅር በሚያልፍ ነገር ቀየሩት።
ጥሪ የተደረገላቸው አርቲስቶች ሁለት አማረጮች ነበራቸው። ጥሪውን ተቀብሎ ሄዶ እውነትን መመስከር አሊያም እንደ ገጠሚ ታገል ሰይፉ ጥሪውን አለመቀበል። ገጣሚ ታገል ሰይፉ በኤፍ ኤም ፱፯ ራዲዮ ሲናገር እንዲህ ነበር ያለው።
“ባለፈው የመቀሌ ጉዞ ላይ እኔ አልሄድኩም። አርቲስቶች ሲሄዱ ጥሪ ተደርጎልኛል። ነገር ግን የደደቢቱን ጉዞ ስላላመንኩበት ቀርቻለሁ። ስለማልፈልገው ማለት ነው። …ለነሱም የምለው ነው። በተለይ ባለፉት 15 አመታት ብዙ ነገር አልተሰራም። ለስነ ጽሁፍ የሚመች ግዜ አይደለም። ስነጽሁፍን ትኩረት አልሰጡትም። እያየን ነው።”
ታገል ሰይፉ ቀደም ሲልም በመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሃሳቡን ተቆርጦ እንዳስቀረበት ተናግሯል። ደደቢት ድረስ ሄዶ ሃሳቡን የማያስተላልፉለት ከሆነ መቅረቱ አይነተኛ አማራጭ ነው። አበበ ባልቻን፤ ሙሉ አለምን፣ ነዋይ ደበበን፣ … አርቲስቶች እና የኪነጥበብ ሰዎች ብለን ጠርተን፤ አስቴርንና ታገል ሰይፉን ምን ልንላቸው ይሆን?… ማህበራዊ ፍርዱን ከህዝቡ ያገኙታል።
ህወሃት ግን አንድ መልዕክት ለማስተላለፍ ነበር አርቲስቶቹን ወደ ደደቢት የወሰዳቸው። አዚህ ተነስተን፣ አፈር ለብሰን፣ አፈር በልተን፣ የፈረስ ሽንት ጠጥተን የያዝናት ስልጣን ናት። ይህችን ስልጣን በምርጫ እንደማናስረክብ እናንተም አረጋግጡልን… እንዲሁ ተቃጥላችሁ ታልቃላችሁ እንጂ በሰላማዊ መንገድ ለውጥ አታስቡ… የሚል መልዕክት።
እኔም በዚህች ቀልድ ጽሁፌን ልቋጭ። አንድ የህንድ ኢንቨስተር አዲስ አበባ ዬሴፍ ቤተ ክርስቲያንን የቀብር ስፍራ አይቶ በሊዝ ሊገዛ ፈለገ። የአዲስ አበባ ባለስልጣናትን ጠርቶ እንዲሸጡለት ጠየቀ። ባለስልጣናቱም መልሰው ሌሎች ቦታዎች ሳያልቁ የቀብር ስፍራ ለግዜው እንደማይሸጡለት ነገሩት። ህንዱ መለሰና መከራቸው። “እኛ አገር ሰው ሲሞት እናቃጥላለን እንጂ አንቀብርም። ለምን ይህን ለም ቦታ ታባክናላችሁ?”
ባለስልጣናቱ መለሱ፣ “እኛ አገር ደግሞ ሰውን በቁሙ ነው እንጂ ሲሞት አናቃጥልም!“