Netsanet: November 2014

Sonntag, 30. November 2014

እናታችን ፋናዬና ተመስገን በዝዋይ…. (የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ወንድም እንደፃፈው)

ከታሪኩ ደሳለኝ 
(የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ወንድም)
ያቺ የስምጥ ሽለቆ ከተማ ይበልጥ መንደድ ከጀማመራት አንድ ወር አልፏታል:: በፍትህ መዛባት ስሜቱ የተጎዳ፣ በወገኖቹ ስቃይ መንፈሱ የታመመ፣ ሀገራቸውን ከስቃይ መታደግ በሚችሉበት እድሜያቸው በታሰሩ፣ በተሰደዱና በተገደሉ ወገኖቹ ልቡ ያዘነ፣ ለሀገሩና ለባንዲራው ያለው ፍቅር ጥልቅ የሆነ አንድ ወጣት ጋዜጠኛ በውስጧ ይዛለች፡፡ ዝዋይ፡፡
ከዚህች ከተማ ሦስት ኪሎ ሜትር ገደማ ወደሚርቀው የዝዋይ እስር ቤት ለመሄድ የአስፓልት ዱካ እንዳረፈበት በሚያሳብቀው ኮሮኮንቻማ መንገድ ማለፍ የግድ ይላል፡፡ ከረጅም ዓመታት በፊት ተሰርቶ ዛሬ አስታዋሽ ያጣው ይህ ጎዳና እስረኞችን የመጠየቁን ጉዞ አስቸጋሪ አድርጎታል፡፡ ከፀሐዩ ግለት ትይዩ ያለው የመሬቱ አቧራ በእግሩ ቆሞ ይሄዳል ብል አይበዛበበትም፡፡ ይህን አልፈን ግዞት ቤቱን እናገኛለን፡፡ የእስር ቤቱን መግቢያ ያለበሰው አቧራ ደግሞ ቅጥሩን በቁፋሮ የተገኘ ጥንታዊ ከተማ አስመስሎታል፡፡ የግቢው ገፅታ ለዕይታ በማይስቡ ነገሮች ቢከበብም፣ ተናፋቂውን ብዕረኛ ግን ደጋግሜ እንድጠይቀው ከወንድምነት የሚዘለው ጥንካሬው ይስበኛል፡፡
በአቧራውና በንዳዱ መካከል ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከቀድሞ ይልቅ በጠነከረ ፅናቱ ስለመኖሩ ሳስብ ደስተኛ እሆናለሁ፡፡ እናታችንስ ምን ታስብ ይሆን? የማይበርድ፣ የማይዳፈንና የማይጠፋ የሀገር ፍቅር ስሜቱ ከአቧራውና ከንዳዱ በላይ መሆኑ ለእርሷ ምን ስሜት ያጋባባታል?
yetemesgen enat
እናታችንና ተሜን ሲገናኙ…
ዛሬ ቅዳሜ ህዳር 20/07 ዓ.ም ነው፡፡ እናቴ አብረዋት ከኖሩ ጎረቤቶቿ ጋር በመሆን፣ ዝዋይ እስር ቤት ከከተመ አንድ ወር ያለፈውን ተመስገንን ልታየው ተሰናድታለች፡፡ ዝዋይ ከሄደ ወዲህ አይታው አታውቅም፡፡ እንደናፈቃት ግን የፊቷ ገፅታ ይመሰክራል፡፡ እንደ ልጅነቱ ፀጉሩን ባትደባብሰውም፤ እጁን ልትነካውና በዕርጅና አንደበቷ ‹እንዴት ነህ?› ልትለው ወደዚያው እያቀናች ነው፡፡ ጠዋት ወጥተው ማታ እንደሚገቡት፣ ክፍለ-ሀገር ሰንብተው እንደሚመለሱት እንደ ጓደኞቿ ልጆች ተመስገን እንደማይመለስ የተረዳችው እናታችን ልጇ ጋር እየሄደሰች ነው፡፡
ለሊት 11፡30 ከጀሞ ኮንዶሚኒየም የተነሳችው መኪና ዝዋይ የደረሰችው ከጠዋቱ 2፡20 ላይ ነበር፡፡ አስፋልት መሰል ፍርስራሽ መንገዱን ስለለመድኩት ነው መሰለኝ ዛሬ አልሰጠኝም፡፡ ፍተሻውን አልፈን እስረኛና ጠያቂ የሚገናኘበት ቦታ ላይ ደረስን፡፡ ከነበርነው ሰዎች ይልቅ እናታችን ጉጉት እንዳደረባት ለመናገር ሁኔታዋን ማየት ብቻ በቂ ነው፡፡
እናታችን ተመስገን በልጅነቱ ከዕኩዮቹ ጋር ተጫውቶ ሲመጣ ጠብቃዋለች፣ ትምህርት ቤት ውሎ ሲመጣ ጠብቃዋለች፣ ስራ ውሎ ሲመጣ ጠብቃዋለች፤ አንዳንዴም ሲያመሽ ደውላ ‹‹አልመሸም፤ የቀረው ለነገ ይቆይህ›› ትለዋለች፤ እርሱም ሁሌ እንደሰማት ነበር፡፡ ዛሬ ግን ልጇን የምትጠብቀው ከትምህርት ቤት አልያም ከጨዋታ ወይም ከስራ አይደለም፡፡ ከእስር ቤት ውስጥ እንጂ!
እናታችን እስረኞች ከሚወጡበት በር ላይ ከተቀመጠችበት ደቂቃ ጀምሮ አይኗን አላነሳችም፡፡ በሩ ሲከፈት የወታደር ልብስ የለበሰ ወጣት ወጣ፡፡ ከወታደሩ በኋላ ተሜ እስካርፉን እንዳደረገ ተከተለ፡፡ እናቴ ከመቀመጫዋ ተነሳች፤ ዐይኗቿ እንባ አዘሉ፡፡ በዕስረኛና በጠያቂ መሀል ያለውን አጥር ተደገፈች፡፡ ሌላ ጊዜ አጥሩን መደገፍ የሚከለክሉት ወታደሮች እናታችንን ግን ጥቂት ታገሷት፡፡ ምን ያድርጉ? እነሱም እኮ እናት አላቸው፡፡ ከተመስገን ኋላ ሌላ ወታደር አለ፡፡ በሁለት ወታደሮች መካከል ሆኖ ተሜ እናቱን አያት፤ ፈገግ አለ፡፡ እየቀረበ ሲመጣ ግን ፈገግታው ከፊቱ ላይ ጠፍቶ በሀሳብ ተተካ፡፡ እናቴን በዚህ እድሜዋ አንከራተትኳት ብሎ እንዳላሰበ እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ ከዚህ ይልቅ ስንትና ስንት እናቶች በየቦታው እየተንከራተቱና እየተሰቃዩ ስለመሆናቸው እያሰበ የተጨነቀ ይመስላል፡፡ እናትና ልጅ አንገት ለአንገት ተቃቅፈው ቆዩ፡፡ ምን አለ ባይለያዩ? እንዲሁ እንዳሉ ወደ ቤት ቢሄዱስ ምን ነበረበት?
ይሄ ግን አይሆንም፤ ይሄ ቦታ ተሜ ለሀገሩ የከፈለውን፣ እየከፈለ ያለውንና የሚከፍለውን መስዋዕትነት ማቅረቢያው ቦታ ነው፡፡ ተሜ ወደ ቤት አይሄድም፡፡
ተሜና እናቴ የተጫወቱት ብዙ ነው ፡፡ ሲገናኙ የነበረው ድባብ ጠፍቶ ሁለቱም ደስ ብሏቸዋል፡፡ ተሜ ትንሽ አይቷት ‹‹ከስተሻል›› ሲላት ፈገግ እንዳለች ‹‹አረ አልከሳሁም፤ አንተ ግን ጤናህ እንዴት ነው?››፤ ‹‹ደህና ነኝ››… እናቴ በየመሀሉ ጨዋታቸውን ገታ እያደረገች በስስት ታየዋለች፡፡ እናትና ልጅ የሆድ የሆዳቸውን እንዲያወሩ የፈቀዱት ወታደሮችም ሁለቱን በስስት የሚያዩ ይመስላሉ፡፡
ሳይታወቀን 6፡00 ሆነ፡፡ የመሰነባበቻ ጊዜ ደረሰ፡፡ እናቴ እየሳቀች አቀፈችው፤ ተሜም እየሳቀ ተሰናበታት፡፡ እንደ አመጣጡ በሁለቱ ወታደሮች መካከል ሲሄድ ከጀርባው ትክ ብላ አየችው፡፡ የሆነ ነገር ልትል የፈለገች ትመስላላች፡፡ ‹‹ተመስገን›› አለች፤ አልሰማትም፡፡ በሩን አልፎ ገባ፡፡ እሱ ፊት የደበቀችውን እንባ ማቆም አልቻለችም፡፡ በዝዋይ እስር ቤት ውስጥ ከፈገግታዋ ጋር አለቀሰች፡፡
እሁድ ህዳር 21/07 ከንጋቱ 12፡00 ሰዓት፡፡ እናቴ ልጇ እስኪፈታ አልጋ ላይ አልተኛም ብላ መሬት መተኛት ከጀመረች 1 ወር ከ17 ቀኗ ነው፡፡ የዛሬውን ለሌት እንዳለፉት ጊዜ አንዴም ተነስታ ‹አይ ልጄ› ወይም ‹እህህ….እህህ….› ሳትል በሰላም ተኝታ በማደሯ ሳልተኛ እያየኋት አደርኩ፡፡ ልክ 12፡10 ሲል ነቃች፡፡ ስታየኝ እያየኋት ነው፡፡ ‹‹ስንት ሰዓት ሆነ?›› ነገርኳት፡፡ አላመነችም፡፡ ተሜ ከታሰረ ጀምሮ እንደ ዛሬ ተኝታ አታውቅም፡፡ ተነሳች፡፡ ‹‹እስከዚህ ሰዓት ስተኛ ዝም ትላለህ?›› አለችኝ፡፡ ‹‹እንዴት ዝም አልልም?›› አልኳት፡፡ ‹ዛሬ የዓመቷ ማሪያም ነች› አለችኝ፡፡ ፊቷ ላይ ድካም አይታይባትም፡፡ … ከደቂቃዎች በኋላ የሀገር ባህል ጥበብ ቀሚስ ለብሳ አየኋት፤ አምሮባታል፡፡ የደስታ ሲቃ ይዞኝ ‹ትላንት እንዴት ነበር?› አልኳት፡፡ በፈገግታ እያየችኝ ‹‹ልጄ ጀግና ነው፤ ጀግና›› ስትል መለሰችልኝ፡፡ እኔም በመስማማት ራሴን ነቀነኩ፡፡ እናቴ በንጋት ፀሐይ ታጅባ የሀገር ባህል ልብሷን እንደለበሰች ስትሄድ በዐይኔ ተከተልኳት፡፡ ይሄ ብርታቷ እስከመቼ እንደሚቆይ እያሰብኩ ነበር፡፡
ተሜ ለሀገሩ ሲልና ሀገሩ እንድትሆን የሚመኝላትን በመፃፉ በግዞት እስር ቤት በአቧራና በንዳድ መሀል እንዲሰነብት ተፈርዶበታል፡፡ ፍትህ የነገሰባት፣ ልጆቿ የማይገደሉባትና የማይሰደዱባት ኢትዮጵያ እንደምትመጣ በተቃጠለ ስሜት እያሰበ፣ በማለዳ የወጣችውን የንጋት ፀሐይ በፈገግታ እያያት እንደሆነ ሳስብ እኔም በደስታ ተሞላው፡፡

WAZA ENA KUMNEGER Special on 4th Year Anniversary of ESAT London – 30 Nov, 2014 | ESATTUBE

WAZA ENA KUMNEGER Special on 4th Year Anniversary of ESAT London – 30 Nov, 2014 | ESATTUBE

የብሄር ነጻነት እስከ መጨፈር — ክንፉ አሰፋ (ጋዜጠኛ) —


ማስታወሻ፡ ይህች ጽሁፍ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከተከሰሰባቸው ሁለት መጣጥፎች አንደኛዋ ናት። በመጭው ወር በአሶሳ የሚደረገውን የብሄር ቀን ድራማ እሳቤ በማድረግ – በርካታ አንባብያን በጠየቁት መሰረት እነሆ በድጋሚ ለንባብ አቅርበናል።
— ክንፉ አሰፋ –

Bahir dar
“እኛ ጭቁን ብሄረሰቦች ከዚህ ቀደም በየሰው ቤት ተቀጥረን የምንሰራ፣ አሽከሮች እየተባልን ነበር የኖርነው። አሁን ግን ይኸውና ህገ-መንግስታችን መብታችንን ሰጥቶናል… ኑሯችንም ተሻሽሎ ዛሬ ዘመናዊ ኑሮ እየኖርን ነው።”
እያለ የሚናገርን አንድ ጎልማሳ የቴሌቪዥኑ መስኮት ያሳያል። የደቡብ ቅላጼና ዘዬ ባለው አማርኛ ከደቡብ የመጣ ጎልማሳ ነው በቴሌቪዥን ቀርቦ መግለጫ እየሰጠ ያለው። ከአነጋገሩ በቀን ሶስቴ የሚበላ፣ የባቡር ሃዲድ እና የኤሌክትሪክ መስመር ገብቶለት፣ የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚም… ይመስላል።
  የዚህ ምስኪን ሰው ገጽታ እና አለባበሱ የሚነግረን ግን ሌላ ነው። በኢህአዴግ ዘመን መብቱ እንደተከበረና ኑሮው እንደተሻሻለ የሚነግረን ይህ ሰው፣ መሰረታዊ የሆነውን የሰው ልጆችን የኑሮ ፍላጎት እንኳን አላሟላም። ለእግሩ ጫማ የለውም።  በባዶ እግሩ ነው የቆመው። ሃፍረተ ስጋውን ከሸፈነለት ብጣቂ ጨርቅ በስተቀር ሰውነቱም እርቃኑን ነበር።
ለመገናኛ ብዙሃን ፍጆታ አነጋገሩ እንዲያሳምር ተነግሮት ሊሆን ይችላል – ንግግሩ ልክ መካከለኛ ገቢ ካላቸው የምዕራብ አውሮፓ ሃገሮች ተርታ የተሰለፈ ይመስላል። ይህ ደግሞ ገና የ’ትራንስፎርሜሽኑ’ ተስፋ እንጂ፤ ለውጡ በብሄር ብሄረሰቦቹ ላይ እንደማይታይ የቪድዮ ምስሎቹ ፍንትው አድርገው ነው የሚያሳዩት። ኢትዮጵያ በአምስት አመት ጊዜ ውስጥ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሃገሮች ተርታ ላይ እንደምትደርስ ኢህአዴግ ቃል ገብቷል። በአሁኑ ግዜ ሰባት በመቶ ብቻ የሆነው የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ብሄር ብሄረሰብ እና ሕዝብ በአምስት አመቱ እቅድ 80 በመቶ ይደርሳል ብለውናል። በእስር ያለው ጠንቋይ ታምራት ገለቴ ነግሯቸው ካልሆነ በስተቀር መቼም ይህንን ተረት ተረት በማህበራዊውም ሆነ በተፈጥሮ ሳይንስ ሊያረጋግጡልን እንደማይችሉ እርግጥ ነው። ከፈረሱ ጋሪው… እንዲሉ ከተግባሩ ወሬው፣ ከ’ህዳሴው ግድብ’ ስራም ሽልማቱ ቀድሞ መያዣ – መጨበጫው የጠፋ ነው የሚመስለው።
ከገጠር እየታፈሱ ለሚመጡት ለነዚህ ምስኪን ወገኖች የ ‘ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች’ መብት ማለት በአመት አንዴ በጎዳና ላይ እየወጡ መጨፈር እና ያለፈውን ስርዓት ማውገዝ ብቻ ነው የሚመስለው። ጭፈራውና ውግዘቱ እንደ ጥምቀት በዓል ስለተለመደ የግድ መደረግ እንዳለበት ያመኑበትም ይመስላል።
የደርግ ስርዓት ሰዎች በባህላቸውና በቋንቋቸው እንዳይዘፍኑ ከልክሎ እንደነበር የሚጠቁም መረጃ የለም። ደርግ አስራ ሰባት አመት ገዛ፣ 20 አመት ሙሉ በብሄር ጭቆናው ሲወገዝ ኖረ። በባንዲራ ቀን ውግዘት፣ በከተሞች ቀን ውግዘት፣ በብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ውግዘት፣ በግንቦት ሃያ ቀን ውግዘት…. በየሽልማቱ ስነ ስርዓት እና በየበዓላቱ ቀን ውግዘት….። የደርግ ሃጢያት መብዛት የነሱን ግፍ ይሸፍን ይመስል የኢህአዴግ በዓላት እና ውግዘቱ ከለት-ተለት ሲጨምር ብቻ ነው የምናየው – እንደ 11 በመቶው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚያ እድገት።
የዚህ ሳምንት ወሬ ደግሞ በመቀሌ ስለተካሄደው ስድስተኛው የ ‘ብሄር – ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ቀን’ ነው። የመከር ወቅት ስራቸውን እንዲያቆሙት ተደርገው፣ ከየክልሉ እየተጫኑ ለጭፈራ መቀሌ የገቡ አርሶአደሮች ቁጥር ቀላል አይደለም። በዲያጎን እየተፈለጉ የተለቀሙ ልማታዊ አርቲስቶች እና የመድረክ አስተዋዋቂዎችም በስፍራው ተገኝተዋል።
የእውቁ ኪነጥበብ ሰው – የኪሮስ አለማየሁ ልጅ ዛፉ ኪሮስ ‘አንበሳ ገዳይ’ በሚለው የትግርኛ ዘፈንዋ መድረኩን ይዛዋለች። በርከት ያለ ሰው መድረኩን ከቦት ይጨፍራል። አዳራሹም በ ‘ብሄር – ብሄረሰቦች እና ህዝቦች’ ተሞልቷል። መቀሌ፣ ኅዳር 27 ቀን 2004 ዓ.ም.።
የእለቱ የመድረክ አስተዋዋቂ ‘አንበሳ ገዳይ’ የሚለው የዛፉ ኪሮስ ዘፈን የተስማማው አይመስልም፤ አልተዋጠለትም። አልያም ዘፈኑን እዚያው መድረክ ላይ እንዲያስተባብል ተነግሮታል። ተራውን ጠብቆ ማይክራፎኑን ያዘ።
“ህገ መንግስታችን ለብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ብቻ ሳይሆን ለዱር እንስሶችም…”
ብሎ እየተናገረ እያለ እንደተለመደው መብራት ተቋረጠ።
  በዚህ ‘ታላቅ’ ቀን መብራት መቆራረጡ ቢያበሳጭም፣ በእንግድነት ወደ መቀሌ የተጓዙት ‘ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች’ ኤሌክትሪክ ምን እንደሆነ ስለማያውቁ አልደነቃቸውም – የሚያውቁት ደግሞ የለመዱት ስለሆነ – ለእነሱ እንግዳ ነገር አይደለም።  ከቆይታ በኋላ ግን መብራት መጣ። ልማታዊው አርቲስትም ንግግሩን ቀጠለ።
“…ህገ መንግስታችን ለብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ብቻ ሳይሆን የዱር አራዊቶችንም መብት ስላስከበረ አንበሶች አሁን አይገደሉም።…”
በማለት የዘፈኑን መልእክት ለማስተባበል እና ጭብጡን ለብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ለማስረዳት ሞከረ። እዚህ ላይ የመድረክ አስተዋዋቂው እና ዘፋኝዋ እንዳልተግባቡ መገመት ይቻላል። ዛፉ ኪሮስ ዘፈንዋን በዚህ መድረክ ታቅርበው እንጂ መልእክቱ ላሁኑ ትውልድ ሳይሆን ምናልባት ‘ተራራ ላንቀጠቀጠው’ ለዚያኛው ሊሆን ይችላል ብሎ ማሰብ የተሳነው ይመስላል። ያ ቡድን የትኛውን ተራራ እንዳንቀጠቀጠ ባይገለጽልንም አሁን ያጠለለበት የለውጥ ደመና ግን በተራው እያንቀጠቀጠው ለመሆኑ ከሚያደርጋቸው ግራ ገብ ድርጊቶቹ መረዳት ይቻላል።
የሆነው ሆኖ በአሉ ለመቀሌ ህዝብ ልዩ ስሜት እንደሰጠው ይታያል። ይህ ህዝብ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወገኑ ተለይቶ፣ በእነ መለስ እና በረከት ካድሬዎች ታጥሮና ታፍኖ የሚገኝ ህዝብ ስለመሆኑ በርካታ መረጃዎች ይመሰክራሉ። ከስፍራው የሚደርሱን መረጃዎች እንደሚተቁሙት ከመንግስት ራዲዮ እና ቴሌቪዥን ውጭ ያሉ የመገናኛ ብዙሃንን በዚያ ክልል መጠቀም ራሱ እስከ ስድስት ወር የሚያሳስር ወንጀል ነው። ለ20 አመታት የታፈነ ህዝብ ከሌላው ወገኑ ጋር ተቀላቅሎ ፣ አብሮ ሲጨፍር የሚፈጥርበትን ስሜት መገመት አያደግትም። የደርግ ስርዓት የአሜሪካ እና የጀርመን ድምጽ ራዲዮን የትግራይ ህዝብ እንዳይሰማ አልከለከለም ነበር። ወያኔ ግን የትግራይ ህዝብን የመናገር ብቻ ሳይሆን የመስማት መብቱንም ጭምር ነው የነፈገው።
የሳተላይት ዲሽ ቴሌቪዥን ክልክል በሆነበት በዚያ ክልል የኢቲቪ አኬልዳማ ድራማ ይደገምልን ብሎ የትግራይ ህዝብ ቢጠይቅ ሊደንቀን አይገባም። ጆሮ ካሰለቸው የ’ህዳሴው ግድብ’ ወሬ እና እጅ እጅ ካሉት ከነ ሰራዊት ፍቅሬ አኬልዳማ ትንሽም ቢሆን ዘና ሳያደርጋቸው አልቀረም። የቴሌቪዥኑ መግቢያ ላይ ታዲያ ‘እንደምን አመሻችሁ ዲሽ የሌላችሁ” ብሎ ነው የሚጀምረው እየተባለም ይቀለዳል። ይህ ህዝብ በስሙ ሲነገድበት እና ከሌላው ወገኑ ጋር እንዲቃቃር ሲደረግ የትግራይ ኢሊቶች ዝም ማለታቸው እጅግ የሚያሳዝን ጉዳይ ነው።
ስለ ዱር አራዊት መብት እና ስለ አንበሳ መግደል ሲነሳ ትዝ ያለኝ የ1983ቱ የአምባሳደር ተስፋዬ ሃቢሶ ንግግር ነበር። ቻርተሩ ሲጸድቅ በነበረበት ጊዜ የከምባታና ሃድያን ጎሳ እወክላለሁ ብለው ወንበር ይዘው የነበሩት አቶ ተስፋዬ ሃቢሶ በወቅቱ ሲናገሩ።
  “እኛ አናሳ ብሄር ብሄረሰቦች ዲሞክራሲ ብቻ ሳይሆን የሚያስፈልገን፣ እንደብርቅዬ እንስሣ እንክብካቤም ይገባናል።” ብለው ነበር።
ኢህዴግም በወቅቱ ለእነኚህ ‘አናሳ ጎሳዎች’ ልዩ እንክብካቤ እንደሚያደርግ ነበር ቃል የገባው።
አቶ ተስፋዬ ይህንን በተናገሩ ከአመታት በኋላ ታዲያ በሃዲያ እና ወላይታ ወገኖቻችን ላይ ጥይት እና ቦምብ እንደዝናብ ወረደባቸው። የ1993ቱ ብሄራዊ ምርጫ ተጭበርብሯል፣ ‘ድምጻችን ይከበር’ ብሎ የጮኸው የደቡብ ወገናችን በመለስ ወታደሮች ያለ ርህራሄ ነበር የተጨፈጨፈው። ልዩ እንክብካቤው እና ዴሞክራሲው ቀርቶ ይልቁንም የቆሙለት፣ በስሙም ስልጣን ያገኙበት፣ የራሳቸው ጎሳ በጥይት ሲቆላ አቶ ተስፋዬ ሃቢሶ ሹመታቸውን ላለማጣት ሲሉ ትንፍሽ አላሉም። እንዲያውም ዛሬም ስለ ‘ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች’ መብት መከበር ከሚነግሩን እና የሌሎችን ጽሁፎች እየሰረቁ ከሚጽፉት ሰዎች አንዱ ናቸው።
  ማሌሊቶቹ የሃገሪቱ የዘመናት ችግር የብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች መብት መነፈግ ነው ሲሉ ሰበኩ። የዚህ ችግር መፍቻ ቁልፍም በእጃቸው እንዳለ ነገሩን። በለስ ቀንቷቸው ምኒሊክ ቤተ መንግስት ሲገቡም ጫካ ውስጥ የጻፉትን ያንን የስታሊን ፍልስፍና ወደ ህገ-መንግስትነት ቀየሩት። መፍትሄ ያሉት የጎሳ ፖለቲካም በጥላቻና በበቀል ተተካ።
የማሌሊት ፍልስፍና ሲተገበር ታዲያ የመጀመርያ ሰለባ የሆነው አማራው ወገናችን ነበር። ለፖለቲካ ትርፍ ሲሉ እነ አቶ መለስ ዜናዊ ይዘውት የመጡት የጥላቻና የብቀላ ፖለቲካ እንደስካር ቶሎ በረደ እንጂ አካሄዱ እጅግ ዘግናኝ ነበር። በምስራቅ እና በምእራብ ኢትዮጵያ የአማራ ዘር ጨርሶ እንዲጠፋ ተዘምቶበት ነበር። የአማራን ዘር ጭካኔ በተሞላበት መንገድ ከተበቀሉት በኋላም ጽዋው ወደ አኙዋክ – ጋምቤላ ሄደ ፣ ከአኙዋክ ጭፍጨፋ በኋላ ደግሞ ዘመቻው በኦሮሞ ወገናችን ላይ ቀጠለ። በወላይታ ተከተለ፣ በኦጋዴን… ተዛመተ። የብሄር መብት እስከመገንጠልን ያስከበረው ህገ-መንግስት ጸድቆ በወረቀት ላይ ተቀምጧል። ይህንን መብት እየጠየቁ ያሉ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችንን ግን በዘራቸው ብቻ እየተመረጡ ማጥፋቱ ዛሬም በሚያሳዝን ሁኔታ እንደቀጠለ ነው።
እነ መለስ እነ በረከት ለዘመናት ተዋልዶና አብሮ ሲኖር የነበረን ህዝብ እንደ እንግሊዝ ከፋፍለህ ግዛው ቅኝ ስርዓት ለአገዛዝ እንዲያመቻቸው ህዝቡን እርስበርስ እያጋጩት ላለፉት 20 አመታት ለመቆየት ችለዋል። የዘር ፖለቲካው ምስጢር ይኸው ነው። ይህንን ባያደርጉ ኖሮ እስካሁን እንደ ጉም ተበትነው በጠፉ ነበር።
  ወደመቀሌው በዓል እንመለስ።
ብሄር ብሄረሰቦቹ በመቀሌ ከተማ በቡድን በቡድን እየዘፈኑና እየጨፈሩ ይጓዛሉ። በተለይ ከደቡብ የመጡት ብሄር ብሄረሰቦች መብታቸው ተከብሮላቸው ወደ እድገት ጎዳና ከተጓዙ ከሃያ አመት በኋላም – ጥንታዊው የጋርዮሽ ስርዓት ከሚመስለው አለባበሳቸው እንኳን አልተቀየሩም።
መር ከሃያ አመት በፊት ቅጠል ለብሶ ይጨፍራል፣ ዛሬም ቅጠሉን አልቀየረም። ዳውሮ ድሮ ለእግሩ ጫማ አያደርግም ነበር አሁንም ጫማ የለውም። ከፊቾ ከ20 አመታት በፊት ከቀንድ የተሰራ የሙዚቃ መሳርያ ነበር የሚጠቀመው፣ አሁንም እሱኑ ይዞ ነው መቀሌ የመጣው…። ሁሉም አንዳች ለውጥ አይታይባቸውም። ታድያ የዚህ ሕዝብ ነጻነቱ፣ ለውጡ እና እድገቱ የቱ ላይ እንደሆነ ማን ይሆን የሚያስረዳን?
ህገ መንግስታዊ መብቴ ይከበርልኝ ባለ ብቻ ምላሹ የጥይት እና ቦንብ የሆነ ሕዝብ ቅጠል ለብሶ መጨፈሩ ምን ትርጉም ይሰጠናል? ይህ ነጻነቱን ያሳየናል እንዴ? ወይንስ ዛሬም የእግር ጫማ እንኳን አለማድረጉ እንደ ባህል ተቆጠረለት?
  ጎንደሬው ሁመራ ላይ ለማረስ ፈቃድ ከመቀሌ መጠየቁ ነው የመብቱ መከበር? ወይንስ መቀሌ ላይ ሄዶ እስክስታ መምታት? አፋርና ኢሳ – ጉርጉራ ላይ ካላረሰ – አማራው ኦሮሞ ምድር ላይ እንዳይሰራ ከታገደ መብቱ ምኑ ላይ ነው?
ተረስቶ ይሆን ይሆናል እንጂ “የአክሱም ሃውልት ለወላይታው ምኑ ነው?…” ብለው ነበር አቶ መለስ። ታዲያ ዛሬ ምን አዲስ ነገር ተገኘ? በመቀሌ እየተደረገ ያለው የወላይታ ጭፈራስ ለአድዋው ምኑ ሊሆን ነው?
‘የኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ አንተን አይመለከትህም’ ተብሎ የነበረ የወላይታ ህዝብ ዛሬ የመለስን ፎቶ እና ‘ለልማት የተጋ ብቸኛው መሪ’ የሚል መፈክር ይዞ በመቀሌ እንዲሰለፍ ተደርጓል።
ደቡቡ የየራሱን የአፍ መፍቻ ቋንቋ እርግፍ አድርጎ ትቶ ኢህአዴግ በፈጠረለት ‘ወጋ ጎዳ’ እንዲናገር አቶ መለስ፡ ሲያስገድዱት እነሱ ግን ልጆቻቸውን በአለም አቀፍ ቋንቋ ብቻ እንዲማሩ ነው ያደረጉዋቸው። ዛሬ አቶ መለስ የነዚህን ጎሳዎች መብት መከበር ነው በመቀሌ እያበሰሩ ያሉት።
ይህ ህዝብ እንዲሁ ‘ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች እየተባለ ሲቀለድበት እንደዋዛ ሃያ አመታት አለፉ።
በኢህአዴግ ዘመን ተወልዳ፣ ተምራ ዩኒቨርሲቲ የተመረቀች ወጣት አንድ አፍሪካ ሃገር አግኝቼ አወራኋት። ሜሮን ትባላለች። ስለ ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች መብት እና ነጻነት ልትነግረኝ ሞከረች። ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባ ውጤት ሳይኖራት ይልቁንም ኢህአዴግ በሰጣት እድል ዩኒቨርሲቲ ገብታ እንደተማረች ስለተነገራት የመለስ ዜናዊ አድናቂ ናት።
በወሬያችን መሃል በድንገት ‘ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ማለት ምን ማለት ነው?’ ብዬ ጠየቅኳት። ጥያቄዬ ዱብዳ ነገር ሆነባት። ለሚለኒየም ግብ ሲባል ከተከፈቱት ዩኒቨርሲቲዎች ለስታስቲክስ ማሟያ የተመረቀች ስለመሆንዋ አመለካከትዋ፣ አስተሳሰብዋ እና ንግግርዋ ይገልጸዋል።
ጥያቄዬን ለመመለስ እንደከበዳት ተረዳሁ። ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች የሚለውን ቃል የሜሮን ትውልድ ለሃያ አመታት ያለማቋረጥ ሲሰማው የነበረው ጉዳይ ነው። ለዚህ ትውልድ የብሄር መብት ማለት ግን በየአመቱ በጎዳና ላይ ከሚደረግ ጭፈራ ውጭ የሚሰጠው ሌላ ትርጉም ያለ አይመስለኝም።
ማን ነው ብሄር? ብሄረሰሰቦችስ የትኞቹ ናቸው? ህዝቦች የሚባሉትስ? ለዚህ ጥያቄ እንኳንና ሜሮን – ወያኔም መልሱ እንደሚቸግረው ይገባኛል።
ሜሮን ግን ኮስተር ብላ “ህገ መንግስቱ ነዋ!” አለችኝ።
ከዩኒቨርሲቲ ከተመረቀች ወጣት ቀርቶ ከአንደኛ ደረጃ ተማሪ እንኳን የማልጠብቀውን መልስ በማግኘቴ ባዝንም – በመልስዋ ግን ትንሽ ፈገግ ማለቴ አልቀረም።
ከአፍታ ቆይታ በኋላ – ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ማለት ራሱ መለስ ዜናዊ ይመስለኛል ስትል ቀለደች ሜሮን።
እዚህ ላይ ልብ በሉ! ‘የህዳሴው ግድብ’ ሽልማት ስነ ስርዓት እየተደረገ በነበረበት ግዜ የግድቡ “ወደር የሌለው ተሸላሚ”ን ሰራዊት ፍቅሬ በቴሌቭዥን ሲያስተዋውቅ የሆነው ነገር ታወስውኝ። ነገሩ ጤነኛ አእምሮ ላለው ሰው እንግዳ ነበር።
ሰራዊት እና ሙሉአለም እየተቀባበሉ – እየደጋገሙም ‘የህዳሴው ግድብ ወደር የሌለው ተሸላሚ’ ይላሉ። ከብዙ ደቀቃ በኋላም የህዳሴው ግድብ ወደር የሌለው ተሸላሚ ይፋ ሆነ።
“ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች!” ሲል ሰራዊት ፍቅሬ በሚለኒየም አዳራሽ ለተሰበሰበው ህዝብ አበሰረ።
ሸልማቱን የሚሰጠው አቶ መለስ ዜናዊ ፣ ሽልማቱን የሚቀበለው የኢህዴግ ተወካይ ሲሆን ፣ ይህም በተዘዋዋሪ አቶ መለስ ዜናዊ መሆኑ ነው።
ሜሮን ይህንን ማለትዋ ከሆነ – ጥያቄዬን በትክክል እንደመለሰችልኝ ተረዳሁ።
ሽልማቱ መጣም አልመጣ ለብሄር ብሄረሰቦቹ የሚፈይደው ነገር አይኖርም። በየአመቱ የሚደረገው የጎዳና ላይ ጭፈራ ግን የብሄረሰቦች መብት ብቻ ሳይሆን ግዴታቸውም ሆኗል ብለን እንደምድም።
የብሄር ነጻነት እስከ መጨፈር! ከዛ ካለፈ ግን የህይወት ዋጋም ያስከፍላል። ኦጋዴንን ያስተውሏል?
***

የሶስት ወር ህጻን ልጇን አንቃ የገደለችው በ16 ዓመት እስራት ተቀጣች

ህጻን ልጇን በሻሽ አንቃ በመግደል የጣለችው ተከሳሽ ላይ የእስራት ቅጣት የተወሰነባት መሆኑን የኢትዮጵያ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
crimeበአርሲ ዞን የሒጦሳ ወረዳ ፖሊስ እንደገለፀው በተከሳሽ መስታወት ደረጄ ላይ የእስራት ቅጣት ሊወስንባት የቻለው ከወለደችው የሶስት ወር እድሜ ያለውን ልጇን ሐምሌ 14 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም ከቀኑ 11 ሰዓት በሚሆንበት ጊዜ ጎንዴ ፊንጨማ ልዩ ስሙ ሾሪማ ተብሎ ከሚታወቅበት አካባቢ በመውሰድና ከበቆሎ ማሳ ውስጥ በመግባት በያዘችው ሻሽ አንቃ በመግደሏ ነው፡፡ እንደ ሒጦሳ ወረዳ ፖሊስ ገለጻ የተገደለውን ህጻን የተመለከቱ የአካባቢው ነዋሪዎች ለፖሊስ በሰጡት ጥቆማ መሰረት አስከሬኑ ተነስቶ በዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል በተደረገለት የአስከሬን ምርመራ መሠረት ህጻኑ ታንቆ መገደሉ ተረጋግጧል ተብሏል፡፡
ተከሳሿ በቁጥጥር ስር ውላ በሰጠችው የእምነት ቃልም በቡና ቤት አስተናጋጅነት እየሰራች ሳለ ከተዋወቀችው አሽከርካሪ ጋር ፍቅር በመመስረቷና ከወለደችለት በኋላ ሊረዳት ፍቃደኛ ባለመሆኑ ድርጊቱን ልትፈጽም መነሳሳቷን ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የአርሲ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽ መስታወት ደረጄን በአስራ ስድስት ዓመት ጽኑ እስራት እንድትቀጣ ወስኖባታል፡፡

የነዳጅ ዋጋ በዓለም አቀፍ ደረጃ ቢቀንስም የኢትዮጵያ መንግስት እስካሁን የችርቻሮ ዋጋን አልቀነሰም

ለአመት ያህል በበርሜር ወደ 110 ዶላር ንሮ የቆየው የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ፤ ካለፈው ሐምሌ ወዲህ እየወረደ በያዝነው ሳምንት ከ75 ዶላር በታች የደረሰ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ የነዳጅ ዋጋ ላይ መንግስት እስካሁን ቅናሽ አላደረገም።
በአመት በአማካይ ከሰባት በመቶ በላይ እየጨመረ የመጣው የኢትዮጵያ የነዳጅ ፍጆታ፣ ባለፈው አመት 3.4 ቢሊዮን ዶላር (ከ65 ቢሊዮን ብር በላይ) ወጪ እንዳስከተለ ታውቋል። ሸቀጦች ወደ ተለያዩ አገራት በመላክ የሚገኘው የውጭ ምንዛሬ ባለፉት አራት አመታት እድገት ባለማሳየቱ አመታዊው ገቢ ከሶስት ቢሊዮን ዶላር ገደማ ብዙም ፈቅ ባለማለቱ፣ የነዳጅ ግዢን እንኳ ለመሸፈን የማይበቃ ሆኗል።
news
በአለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ ባለፈው አመት በነበረበት ቢቀጥል ኖሮ፣ በቀጣዩ አመት ኢትዮጵያ ሩብ ቢሊዮን ዶላር (5 ቢሊዮን ብር) ተጨማሪ ገንዘብ ለነዳጅ ግዢ ለማውጣት መገደዷ አይቀርም ነበር። ይሁን እንጂ፣ ያለማቋረጥ እየወረደ የመጣው የነዳጅ አለማቀፍ ዋጋ በስድስት ወራት ውስጥ ሲሶ ያህል ስለቀነሰ፣ ኢትዮጵያ ለነዳጅ ግዢ የምታውለው የውጭ ምንዛሬ ዘንድሮ እንደማያሻቅብ ተገምቷል።
እንዲያውም የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በበርሜል ከ80 ዶላር በታች ሆኖ ከቀጠለ፣ የአንድ ቢሊዮን ዶላር (የ20 ቢሊዮን ብር ወጪ ቅናሽ ያስገኛል፡፡) በርካታ ነዳጅ አምራች አገራትን የሚቆጣጠሩ መንግስታት በአባልነት የተካተቱበት ኦፔክ የተሰኘው ማህበር፣ ሰሞኑን በነዳጅ ዋጋ ዙሪያ የተወያየ ቢሆንም፣ ውይይታቸው በአለም የነዳጅ ዋጋ ላይ ለውጥ እንደማያስከትል ትናንት ቢቢሲ ዘግቧል። እየወረደ የመጣው የነዳጅ ዋጋ፣ የበርካታዎቹን መንግስታት ገቢ እንደሸረሸረ የገለፀው ቢቢሲ፣ ከፍተኛ የበጀት ጉድለት ያጋጥማቸዋል ብሏል። “ዋጋ እንዲያንሰራራ የነዳጅ ምርት መቀነስ አለብን” የሚል ጥያቄ ከሁለት መንግስታት በኩል እንደቀረበ ዘገባው ጠቅሶ፣ ጥያቄው በአብዛኞቹ መንግስታት ተቀባይነት ሳያገኝ መቅረቱን አመልክቷል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የነዳጅ ዋጋ መውረድ የጀመረው፣ በከፊል ከአለም ኢኮኖሚ መቀዛቀዝ ጋር በተያያዘ ምክንያት ቢሆንም፣ ዋናው ምክንያት ግን የአሜሪካ ኩባንያዎች ከፍተኛ የነዳጅ ምርትን የሚያስገኝ አዲስ ዘዴ በመፍጠራቸውና ተጨማሪ ነዳጅ ማምረት በመጀመራቸው እንደሆነ ፎርብስ መፅሔት ዘግቧል።
ከአለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ ውጣ ውረድ ጋር፣ የኢትዮጵያ መንግስት በንግድ ሚኒስቴር በኩል በየወሩ የነዳጅ ዋጋ ተመን የሚያወጣ ሲሆን፣ ከጥቂት ጊዜያት በስተቀር አብዛኛውን ጊዜ የዋጋ ተመኑ በነበረበት እንዲቀጥል አልያም የአለም ገበያን ተከትሎ እንዲጨምር ሲወስን መቆየቱ ይታወሳል።
ባለፉት ስድስት ወራትም እንዲሁ፣ በአለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ በፍጥነት እየወረደ ቢመጣም፣ በኢትዮጵያ ግን የችርቻሮ ዋጋ በነበረበት ደረጃ እንዲቀጥል አልያም እንዲጨምር የተደረገ ሲሆን፣ በያዝነው ወር መጨረሻ የዋጋ ተመኑ ላይ ምን አይነት ለውጥ እንደሚደረግበት ገና አልታወቀም። በተለመደው የመንግስት አሰራር፣ የዋጋ ተመን ውሳኔው በይፋ እስከሚገለፅበት እለትና ሰዓት ድረስ በሚስጥር ተጠብቆ ነው የሚቆየው።

ምንጭ አዲስ አድማስ ጋዜጣ ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣ

ኩማ ደመቅሳ በዋሽንግተን ዲሲ ሆስፒታል ተኝተዋል

(ኢየሩሳሌም አርአያ)
አቶ ኩማ ደመቅሳ በዋሽንግተን ዲሲ ሆስፒታል ተኝተው እንደሚገኙ ታማኝ ምንጮ አስታወቁ።
kuma demekesa
ኩማ በጭንቅላት እጢ (ቲዩመር) በሽታ ምክንያት ለከፍተኛ ህክምና ዲሲ መምጣታቸውን የጠቆሙት ምንጮቹ የመዳን ተሳፋቸው 90 በመቶ የተመናመነ መሆኑን ከሃኪሞች እንደተገለፀላቸው አስታውቀዋል።
ከባለቤታቸው ጋር የመጡት ኩማ ሆስፒታል ከመግባታቸው በፊት ባለፈው ሳምንት ማርዮት ሆቴል አርፈው እንደነበረ ሲታወቅ ሁለት ኢትዮጵያውያንን በሆቴሉ መተላለፊያ ላይ ሲያገኙ ክፉኛ ደንግጠው እንደነበረ ማወቅ ተችሏል። አሜሪካ -ዲሲ መምጣታቸው እንዳይታወቅባቸው የሚጠነቀቁትና ፍርሃት የሚታይባቸው ኩማ የስጋታቸው ምንጭ እንደሌሎች ባለስልጣናት ተቃውሞ ይገጥመኛል በሚል እንደሆነ ሲታወቅ የማያውቁትን ስልክ እንደማያነሱ ማረጋገጥ ተችሏል።
በተለይ የመዳን ተስፋ እንደሌላቸው ከተነገራቸው በኋላ ከኢትዮጵያ የሚደወልላቸውን ስልክ እንደማያነሱ ታውቋል። ኩማ ደመቅሳ ከ1993ዓ.ም በፊት ሙስና ውስጥ እንዳልገቡና ነገር ግን የአዲስ አበባ ከንቲባ ከሆኑ በኋላ በከፍተኛ ሙስና ከተዘፈቁት ባለስልጣናት ተርታ እንደተመደቡ ይታወቃል።

Samstag, 29. November 2014

እስረኞችን ለመጠየቅ ቃሊቲ የሄዱ ሰዎች በቁጥጥር ሥር ከዋሉ በኋላ ተለቀቁ

በአንድነት ፓርቲ በቃሊቲ እና ቂሊንጦ የሚገኙ የህሊና እስረኞችን ለመየጠቅ ወደስፍራው ያመሩ ወደ 30 የሚገመቱ ሰዎች ቀትር ላይ በቃሊቲ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ መለቀቃቸው ታወቀ፡፡
የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት አቶ አስራት አብርሃ ከ30 ደቂቃዎች በፊት በስልክ እንደነገሩኝ ከሆነ ‹‹እነእስክንድርንና አንዷለምን መጠየቅ አትችሉም፡፡ ተባልን ከዚያም ‹‹ለምን?›› ብለን ስንጠይቅ በዋናው በር በኩል ኃላፊውን አነጋግሩ የሚል መልስ ተሠጠን፡፡ እኛም ይህንን አምነን ሄድን፡፡ ስንደርስ በቁጥጥር ሥር ውላችኋል ብለውን ወደ 30 የምንገመት ሰዎችን መታወቂያችንን ከመዘገቡ በኋላ በአንድ ክፍል ውስጥ ለጊዜው እንገኛለን›› ብለውኝ ነበር፡፡ አሁን ባገኘሁት መረጃ መሰረት ደግሞ በኮንቴይነር ውስጥ ታግተው የነበሩት እስረኛ ጠያቂዎች ከበድ ያለ ፍተሻ ተደርጎላቸው ከቃሊቲ ግቢ እንዲወጡ ተደርጓል
a3a1a2

Freitag, 28. November 2014

የእስክንድር ነጋ ያገባኛል ባይነት!

በላይ ማናዬ
‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል!››
ይህን ያለው ትንታጉ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ እስክንድር ነጋ ነው፡፡ እስክንድር ነጋን ካወኩት ወዲህ እንደዛሬ በኃይለ ቃል ሲናገር ሰምቼው አላውቅም፤ ወይም ትዝ አይለኝም፡፡ ዛሬ (ህዳር 19/2007 ዓ.ም) እኩለ ቀን ላይ እስክንድርን ልጠይቀው ቃሊቲ ተገኝቼ ነበር፡፡ ሆኖም ሁኔታው ሁሉ እንደማንኛውም ቀን አልነበረም፡፡ በር ላይ ስደርስ በርከት ያሉ የአንድነት ፓርቲ አባላት ሰሞኑን እያካሄዱት ያለውን የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ በማስመልከት እስክንድር ነጋን፣ አንዱዓለም አራጌን እና ሌሎችንም ሊጠይቁ በቦታው ተገኝተው ነበር፡፡
በጠዋት ቂሊንጦ የሚገኙ ወዳጆቼን ጠይቄ አብረውኝ ከነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ጋር ነበር ወደ ቃሊቲ ያመራሁት፡፡ ቃሊቲ የተገኘው ሰው ሁሉ መጠየቅ የሚፈልገውን ሰው እና ሙሉ አድራሻውን እያስመዘገበ ሳለ በመሐል እኔም እስክንድርን መጠየቅ እንደምፈልግ ነግሬ ተመዘገብኩ፡፡ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ግን ስማችሁ ከዚህ ቀደም ያልተመዘገባችሁ አሁን መግባት አትችሉም መባሉን መዝጋቢ ፖሊሱ አረዳን፡፡ እኔ እና ትንሽ ሰዎች መግባት ስንችል አብዛኛው ሰው ግን መግባት እንደማይችል ተነገረን፡፡
በዚህ ሁኔታ እስክንድር ጋር ደርሰን ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ አንድ የአንድነት ፓርቲ አባል ሰሞኑን ፓርቲያቸው እስረኞችን በተመለከተ በማህበራዊ ድረ ገጽ ላይ እየተሰራ ያለውን ስራ ለእስክንድር ያብራራለት ጀመር፡፡ እስክንድር በተለመደ ጥሞናው ሲያዳምጠው ቆይቶ፣ በግሉ የተሰማውን እና መሆን ቢችል ያለውን ነጥብ ተናገረ፡፡ በመሐል ወጣቱ የአንድነት አባል ወደ እስክንድር ጠጋ ብሎ ሌሎች ተጨማሪ ጉዳዮችን ሲነግረው ድንገት አንድ የፖሊስ አዛዥ ጨዋታቸውን እንዲያቆሙና እስክንድር ወደ እስር ቤቱ እንዲገባ፣ ወጣቱ የአንድነት አባል ደግሞ ወደ ውጪ እንዲወጣ በትዕዛዝ ማጣደፍ ያዘ፡፡
ይህኔ እስክንድር ለስለስ ባለ አነጋገር ምንም እንዳላጠፋን በመግለጽ ፖሊሱ መረጋጋት እንዳለበት አስረዳ፡፡ የፖሊስ አዛዡ ግን ጭራሽ ብሶበት ወጣቱ በቶሎ እንዲወጣ አደረገ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ‹ፖለቲካ ማውራት አቁሙ› የሚል ሆነ፡፡ ይህን ተከትሎ እስክንድር ድንገት በኃይለ ቃል ተናገረ፡፡ ‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል! የማወራው ስለ ሰላማዊ ትግል፣ ስለህጋዊ ትግል ነው!›› አለ እስክንድር በስሜት ውስጥ ሆኖ፡፡
በግሌ እስክንድር እንዲረጋጋ፣ ሁኔታው ግን ያልተገባ እንደሆነ ገለጽኩ፡፡ ፖሊሱ ግን ሊረጋጋ አልቻለም፡፡ እስክንድርን ይዞት ሄደ፡፡ ‹‹በርቱ! እንቅስቃሴያችሁ ህጋዊና ሰላማዊ ይሁን እንጂ ትግላችሁን ቀጥሉ!›› ሲል እስክንድር ወደ እስር ቤቱ እየገባ ተናገረ፡፡ የፖሊስ አዛዡም ከእስክንድር ጋር የነበረንን ቆይታ ሰዓቱ ሳይደርስ ገታው፡፡ የእስክንድር ያገባኛል ባይነት አስደመመኝ፡፡ እስር ቤት ሆኖም፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖም እስክንድር ስለ ሀገሩ እንደሚያገባው በስሜት ተናገረ፡፡ መብቱን መቼም ቢሆን አሳልፎ እንደማይሰጥ አስረገጠ፡፡
ስለ ያገባኛል ባይነት ሳስብ በጠዋት ቂሊንጦ ያገኘኋቸውን የዞን 9 ጦማሪዎች አስታወስኩ፡፡ ‹ስለሚያገባን እንጦምራለን!› ይላሉ ወጣቶቹ ጦማሪያን፡፡ ከአብርሃ ደስታ ጋር አብረው ያገኘኋቸው እነ በፍቃዱ ኃይሉ እና አጥናፍ ብርሃኔ ብዙ ጉዳዮችን እያነሱ አወጉኝ፡፡ ‹‹ህወሓት አንድ ወይም ሁለት ነባር የህወሓት ባለስልጣናትን በሽብር ከከሰሰ ስርዓቱ እንዳበቃለት እቆጥራለሁ፡፡ ምክንያቱም ሽብር ማታለያ መሆኑ ይቀራል›› አለኝ በፍቃዱ ኃይሉ፡፡ አብርሃ ደስታ ቀበል አድርጎ ‹‹እናት አልጋነሽ በሽብር ስትከሰስ በጣም ብዙ ሰው ተቃውሞ ነበር›› አለ፡፡ አጥናፍ በበኩሉ ‹‹ቄስና ሸህ ሽብርተኛ እየተባለ አይደለም እንዴ›› በማለት ጠየቀ፡፡
አብርሃ ደስታ አንድ ነገር በኃይል እንደሚቆጨው ተናገረ፡፡ ምን እንደሆነ ጠየቅሁት፡፡ ‹‹ብዙ የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ሳላደርግ መታሰሬ ይቆጨኛል!›› አለ፡፡ በፍቃዱ በበኩሉ፣ ‹‹እኔም የገባኝ ነገር ያለውን የሰላማዊና ህጋዊ የመስሪያ ልክ አለመስራታችን ነው፡፡ አሁን ላይ ሆኜ ሳስበው እንዲህ ለሚያስሩን ስንት ህጋዊና ሰላማዊ እንቅስቃሴዎችን እንኳ ሳናደርግ በትንሽ ነገር በርግገው እዚህ ሲያስገቡን ይቆጨኛል›› በማለት ሀሳቡን ቀጠለ፡፡ ‹‹በእርግጥ አንድ ሰው አሁን መጠንቀቅ ያለበት የሚሰራው ስራ ህጋዊ መሆን አለመሆኑን እንጂ፣ ይህን ካደረኩማ ያስሩኛል የሚለውን መሆን የለበትም፡፡ እነሱ ከፈለጉ ያስሩሃል፤ ስለዚህ መብትህን ተጠቅመህ መታሰሩ ይሻላል እንዲሁ ምንም ሳይሰሩ ከመግባት›› ሲል አብርሃ ሀሳቡን አካፈለ፡፡
ቂሊንጦ ከእነ በፍቃዱ ጋር ስንጨዋወት ስለእስክንድር ነጋ ትሁትነት፣ አስተዋይነት፣ ሰላማዊነት እያነሱ ሰላምታ እንዳደርስላቸው ጠየቁኝ፡፡ እኔም እስክንድር ነጋን ሳውቀው በትሁትነቱ፣ በአስተዋይነቱና በሰላማዊነቱ ነው፡፡ ዛሬ በነበረው ሁኔታ ግን ክፉኛ ተበሳጭቶ ነበር የተመለከትኩት፡፡ ያ ፈገግታው ከፊቱ ብን ብሎ ጠፍቶ ‹‹ያገባኛል!›› ሲልበት የነበረውን ስሜት ግር አለኝ፡፡ ካልነኩት የማይነካ ሰው ሲነኩት ትንታግ ነው፡፡ እስክንድር እዛ ስሜት ውስጥ የገባው ተገድዶ ነበር፡፡ ሊጠይቁት የመጡትን ሰዎች አብዛኞቹን አላስገባም ማለታቸው ሳያንስ ከገቡትም መካከል የምታወራውን እኔ ልምረጥልህ በሚል ግብዝነት አባርረዋል፡፡ እስክንድር ይህን አይቶ ዝም ማለት አልቻለም፡፡ ስለሆነም እንዲህ አለ፤
‹‹…እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል! የማወራው ስለ ሰላማዊ ትግል፣ ስለህጋዊ ትግል ነው! ስለሀገሬ ያገባኛል!››

Donnerstag, 27. November 2014

አንድነትና መድረክ ተለያዩ

ሪፖርተር
ላለፉት ስድስት ዓመታት ገደማ ያህል በጋራ ለመሥራት ተስማምተው የተቃውሞ ጐራው ላይ በጋራ ሲሠሩ የነበሩት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) እና አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የነበራቸውን አብሮ የመሥራት ስምምነት አቋርጠው ተለያዩ፡፡
UDJAEUPሁለቱ ፓርቲዎች የቀድሞው የአንድነት ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው ሰጥተውታል በተባለው አስተያየት የተነሳ እሰጥ አገባ ውስጥ መግባታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ አስተያየቱን አንድነት ያስተባብል በሚል ከመድረክ የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ለፓርቲዎቹ መለያየት ከፍተኛውን ድርሻ መውሰዱን የሁለቱ ፓርቲዎች ባለድርሻ አካላት መግለጻቸውን መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡
ከሁለት ሳምንታት በፊት ዳግም የመድረክ ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ለአንድነት እስከ ኅዳር 15 ቀን 2007 ዓ.ም. ድረስ ገደብ መስጠታቸውን መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡
በዚህም መሠረት አንድነት ለመድረክ ኅዳር 11 ቀን 2007 ዓ.ም. በጻፈው የመልስ ደብዳቤ፣ ከመድረክ አባልነት መውጣቱን ገልጾ መጻፉን የመድረክ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጥላሁን እንደሻው ለሪፖርተር አረጋግጠዋል፡፡
የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ አበበ አካሉ በበኩላቸው፣ ‹‹ከመድረክ ጋር በይፋ ተለያይተናል፤ ፊርማችንን ቀደናል፤›› በማለት ከመድረክ ጋር የነበራቸውን ግንኙነት ማቋረጣቸውን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
ለሁለቱም የፓርቲ አመራሮች ምርጫ በተቃረበበት ወቅት እንዲህ ዓይነት ውሳኔ መውሰድ አጠቃላይ ሰላማዊ ትግሉን አይጐዳውም ወይ የሚል ጥያቄ ሪፖርተር አቅርቦ ነበር፡፡ የሁለቱም ፓርቲ አመራሮች ጉዳት ማስከተሉን ተቀብለው ነገር ግን ከአቅም በላይ በመሆኑ መለያየት መፍትሔ እንደሆነ አስረግጠው ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
በዚህ ረገድም ‹‹ይሄ እኮ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ የተቃውሞ ፓርቲዎች የጋራ ትብብር አለመኖር፤ ውህደት አለመኖር የኢትዮጵያን ሕዝብ ትግል ይጐዳዋል፡፡ ይህንን እናውቀዋለን፡፡ ነገር ግን ትግሉን እየጐዳው ቢሆንም አብሮ የማይሄድና የማይሆን ነገር ሲታይ አብረህ መቀጠል አትችልም፡፡ መለያየት አለብህ፤›› በማለት ልዩነቱ በመስፋቱ መለያየቱ የግድ እንደሆነ አቶ አበበ ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡
‹‹እንዲህ ዓይነት ውሳኔዎች ትግሉን እንደሚጐዳ ይታወቃል፤›› በማለት የገለጹት አቶ ጥላሁን በበኩላቸው፣ ‹‹የተቃውሞ ጐራውን ለመጉዳት የተነሱና የተመኙ ሰዎች የሠሩት ሥራ ጠቅላላ አንድነትና መድረክን ወደ መለያየት ወስዷል፤›› በማለት ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም የሁለቱም ፓርቲ አመራሮች ወደፊት ስለሚያደርጉት የትግል አቅጣጫ የየራሳቸውን ዕቅድ ማዘጋጀታቸውን የገለጹ ሲሆን፣ ‹‹እኛ ቀድሞውኑ በአፍራሽ መልኩ የመጣውን እንዴት እንደምንቋቋምና እንዴት ትግላችንን በዚህ ጉዳት ምክንያት ሳይዳከም ሊቀጥል እንደሚችል የራሳችንን ሥራ ስንሠራ ስለቆየን ይህን ጉዳይ አሁን እንደ አዲስ አናየውም፡፡ በእኛ በኩል የራሳችንን ትግል በተጠናከረ ሁኔታ እንቀጥልበታለን፤›› በማለት አቶ ጥላሁን ቀጣይ ሥራቸውን ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ አቶ አበበ በበኩላቸው፣ ‹‹መድረክ አንካሳ ነው ያደረገን፡፡ ነገር ግን አንካሳ ሆነን ከምንቀጥል ባለን ነገር ሮጠን ምርጫውን እኛ ባለን መዋቅር ብንጋፈጠው የተሻለ ውጤት እናገኛለን፤›› በማለት ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

በቀለ ገርባ

የሚሊዮኖች ድምፅ ቀጣይ መርሀ ግብሮች

አቶ በቀለ ገርባ
10734019_734141523337451_8980381146422839409_n
አቶ በቀለ ገርባ
ነሐሴ 21/2003 ዓ/ም ከምሠራበት ቦታ በስልክ ተጠርቼ በተለምዶ ማዕከላዊ ተብሎ ከሚጠራው የፌዴራል ወንጀል ምርመራ ዘርፍ ተወስጄ ከአንዲት ትንሽ ጨለማ ክፍል ውስጥ ከተወረወርኩ በኋላ በማግስቱ አራዳ ወረዳ ፍ/ቤት ቀርቤ የሃያ ስምንት ቀን የምርመራ የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆብኝ ተፈቅዶላቸው ያም ሲያልቅ እንደገና ሌላ ቀጠሮ ተጠይቆ ተፈቅዶላቸው፣ የማይመለከቱኝን ጥያቄዎች ስጠየቅና ስመልስ ቆይቼ ጥቅምት 3/2004 በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍ/ ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት ቀርቤ የክስ ወረቀት ደርሶኝ ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ተልኬ እነሆ እስከዛሬ ድረስ ዞን አንድ ቅጣት ቤት ተብላ በምትጠራው ቤት እገኛለሁ፡፡

የቀረበብኝ ክስ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 241 የተመለከተውን በመተላለፍ የአገሪቱን የፖለቲካና የግዛት አንድነት በመንካት ወንጀል ሲሆን ዝርዝሩ፡- “የኦሮሞ ነፃነት ግንባር /ኦ.ነ.ግ/ አባል በመሆን ሶሎሎ ጐልቦ ሥልጠና ወስደሃል፤ በጥር ወር 2002 ዓ/ም በአምቦ ከተማ ኦ.ነ.ግ በቅርብ ወደ አገር ውስጥ አሸንፎ ይገባል፤ ከጐኑ ቆመን በሥልጣን ላይ ያለውን መንግስት መጣል አለብን ብለህ መመሪያ ሰጥተሀል፤ በሐምሌ 2003 ዓ/ም ተማሪዎችንና ህዝቡን ለአመጽና ለብጥብጥ እንዲነሳሱ ቅስቃሳ አካሂደሀል፤ እንዲሁም በ2004 ዓ/ም በመላው ኦሮሚያ አመጽና ብጥብጥ በማስነሳት በሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት መጣል አለብን በማለት ትዕዛዝ አስተላልፈሀል፤ በዚሁ ወር የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህርነትህን ሽፋን በማድረግ ቢሮህ ተገኝተው የመመረቂያ ጽሁፍ ሊሰጡህ የመጡትን ተማሪዎች በሥልጣን ላይ ያለውን መንግስት በሃይል ከሥልጣን እናውርድ በማለት መመሪያ ሰጥተሀል” የሚል ነው፡፡

እነዚህ የቀረቡብኝ ክሶች ፈጽሞ የሀሰት ውንጀላዎች መሆናቸውን ለማስረዳት በመጀመሪያ ደረጃ ትጥቅ ትግልና ሰላማዊ ትግልን አስመልክቶ ያለኝን አቋምና እምነት ባጭሩ ከገለጽኩ በኋላ በቀረቡብኝ ምስክሮችና የሠነድ ማስረጃ ላይ ያሉትን እውነታዎች አቅርቤ በአጭሩ የማጠቃለያ ሀሳብ እደመድማለሁ፡፡

1.የትጥቅ ትግል በአንድ ወገን ድል አድራጊነት የሚጠናቀቅ እንደመሆኑ አሸናፊውን ወገን ክብርና የበላይነትን ሲያጐናጽፍ ተሸናፊውን ወገን ደግሞ የውርደትና የበታችነት ስሜት ይፈጥርበታል፡፡ በዚሁ የተነሳ ተሸናፊው ወገን ቂም አርግዞ ጊዜውን ጠብቆ አድፍጦ የሚያደባበት ስለሆነ እውነተኛ ያልሆነ አሉታዊ ሠላም የሰፈነበት ነው፡ ፡ ፖለቲካውም የምሬት፣ የጥላቻ የበቀልና የጠላትነት ስለሚሆን እስራት፣ ስደት፣ ከሥራ መፈናቀልና ሌሎች ምስቅልቅሎችን ያስከትላል፡፡ ይህን የትግል ዘዴ በታሪካችን ደጋግመን ሞክረነዋል፡፡ መዘዙንም ቀምሰነዋል፤ ለኋላ ቀርነታችን አንደኛው ምክንያት ሆኗልና፡፡ በአንፃሩ ግን ሠላማዊ ትግል አሸናፊና ተሸናፊ ስለሌለው መቋጫው እርቅ ወንድማማችነትና ዘላቂ ሰላም ነው፡፡ አውንታዊ ሠላም ፖለቲካውም ልዩነትና ብዙሀንነት ስለሚያስተናግድ የሚማረር ወገን አይኖርም፡፡ ስለዚህ ተመራጭ ብቻ ሳይሆን ብቸኛ የትግል ዘዴ መሆን አለበት የሚል እምነት ስላለኝ ህጋዊ በሆነ የፖለቲካ ድርጅት ውስጥ በመሳተፍ የድርሻዬን በማበርከት ላይ እገኛለሁ፡፡

2.የትጥቅ ትግል አሸናፊው ቡድን የአልበገር ባይነት ስሜት እንዲሰማውና እብሪተኛና ጨካኝ እንዲሆን ከማድረጉም በላይ ድሉን ለማግኘት ለከፈለው መስዋዕትነት ካሳ ፈላጊ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ በዚህ ምክንያት ሥልጣንንና የሀብት ምንጮችን ጨምድዶ በመያዝ በትግሉ ያልተሳተፉትን በማግለል ፍትሀዊ ክፍፍልን አዛብቶ የዜጐችን የእኩልነት መብት ወደ መርገጥ ያመራል፡፡ ውሎ ሲያድርም ይህን ስህተቱን ማረም ስለሚሳነው የሃሳብ ልዩነትን የማይቀበል አምባገነን ይሆናል፡፡ በዚህ ምክንያት መብታቸውን የሚጠይቁ ዜጐችን በጠላትነት ፈርጆ ሊያጠፋቸው ሕጋዊ የሚመስል ህገወጥ ድርጊቶችን በስውርና በግልጽ በመፈጸም ለሌላ ትጥቅ ትግል በር ይከፍታል፡፡ ይህን የትጥቅ ትግል ዑደት አንድ ቦታ ላይ ሰብሮ በማቆም አገሪቱን ከትርምስና የመገዳደል ባህል መታደግ የሚቻለው ራሳቸውን ለአደጋ አጋልጠው ሳይገድሉ እየሞቱ እየታሠሩና ከሥራ እየተፈናቀሉ በሠላማዊ መንገድ ብቻ በሚታገሉ ኃይሎች አማካኝነት ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ መርጬ እየተጓዝኩበት ያለሁትም ይህን ነው፡፡

3.የትጥቅ ትግል ሰብዓዊና ቁሳዊ ሀብትን ከማውደሙም በላይ ጊዜያዊም ቢሆን ሥርዓተ አልበኝነትን ያስከትላል፡ ፡ በጣም ውስን በሆነች የሀገር ሀብት አንዱ የገነባውን ሌላው እያፈረሰ የሚሄድ ከሆነ መጨረሻችን የት ሊሆን እንደሚችል መገመት አያስቸግርም፡፡ የትጥቅ ትግል ለዜጎች ስንዴና ዘይት እንኳን ማቅረብ የማይቻል እንደኛ ያለ አገር ቀርቶ የሚዋጉበት በጦር መሳሪያ ለሚያመርቱ አገሮች እንኳን አዋጭ ስላልሆነ ዘለው አይገቡበትም፡፡ ብጥብጥና ሁከት በሚነሳባቸው አገሮች ዋነኞቹ ተጐጂዎች ተራ ዜጎች እንጂ እንደከሳሾቼ ያሉ ባለሥልጣናት ወይም የመንግሥት መሪዎች አይደሉም፡፡
በኛ አገርም ይህ ሁኔታ ቢከሰት ግንባር ቀደም ሰለባ መሆን ከሚችሉት ውስጥ እኔና ቤተሰቤ እንገኛለን፡፡ ምክንያቱም የምጓዘው በተራ ትራንስፖርት፤ የምኖረው በተራ መንደር በተራ ቤት፣ ልጆቼ የሚማሩት በተራ ትምህርት ቤት ሲሆን ከሳሾቼ ግን ይህ ሁሉ የማይመለከታቸውና የማያስጋቸው በመሆኑ ከነሱ የበለጠ ሠላም ለኔ ትልቅ ዋጋ አለው፡፡ ስለዚህ ነው ምንም ዓይነት ዜግነት፣ ቀለም ወይም ዘር ይኑርው ስብአዊና ቁሳዊ ውድመትን የሚያስከትል ጦርነትም ሆነ ብጥብጥ ከሚራምድ አካል ጋር የማልተባበረው

4.በትጥቅ ትግል ወደ ሥልጣን የሚመጡ መንግስታት ከውይይትና ድርድር ይልቅ በኃይል መፍትሔ ስለሚያምኑ ዴሞክራሲያዊ አካሄድን ከማቀጨጭ አልፎ እስከነአካቴው ይፃረራሉ፡፡ ለይስሙላ በሚገኙባቸው የድርድር መድረኮችም ሌላም ወገን እንዲቀበል የሚፈልጉትን ለመንገር እንጂ ሰጥቶ ለመቀበል ስላልሆነ በድርድሩ ማግስት ወደ ቀድሞ የኃይል ተግባራቸው ይመለሳሉ፡፡ ህዝቡ የጦር ሜዳ ገድሎቻቸውን አይቶና ሰምቶ አይበገሬነታቸውን ተረድቶ በፍርሃት እንዲገዛላቸው ሚዲያውን በጦርነት ወሬ ያደምቃሉ፡፡

በሰላማዊ ትግል አግባብ ስልጣን የሚይዙት ግን የስልጣናቸው ምንጭ የሆነው ሕዝብ ጥቅሙና መብቱ ካልተጠበቀለት ነገ ደግሞ ለሌላ መስጠት እንደሚችል ስለሚገነዘቡ ዜጐቻቸውን ያከብራሉ፤ ከመፍራት ይልቅ መከበርን ይሻሉ ከመናገር ይልቅ ማዳመጥን ያስቀድማሉ፡ ፡ እውነተኛ ዴሞክራሲን በማስፈን ሕዝባቸውን ወደ ዘላቂ ሰላምና እድገት ይመራሉ፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰላማዊ ትግል ነው እንዲካሂድ የምሻውና ዋጋ እየከፈልኩበት ያለው፡፡

5.በእምነት ዝንባሌዬ ነፍስ የፈጣሪዋ ብቻ ስለሆነች የሰውን ልጅ ነፍስ ማጥፋት ከወንጀል አልፎ ኃጢአት መሆኑንና ይህን ክቡር ነገር በኃይል ከሰው የሚነጥቁ ሁሉ በተመሳሳይ መንገድ እንደሚነጠቁ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ “ሠይፍ የሚመዙ በሠይፍ ይጠፋሉ” የሚለውን መለኮታዊ ቃል አምናለሁ፡፡ ስለዚህ የኃይል ተግባርን እንደአማራጭ ወስጄ አላውቅም፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ፈጣሪ እውነት ነው፤ በፈጣሪ የሚያምን ሁሉ እውነትን ያመነ ማለት ይገባዋል፡፡ “እውነትን ሲሻና ለፍትህ ሲከራከር በፍቅር ብቻ ማድረግ አለበት” የሚለውን የጋንዲ “ሳትያግራሀ” ፍልስፍና እቀበላለሁ፡፡ “ሳትያግራሀ” “የእውነት ኃይል፤ የፍቅር ኃይል” ማለት ሲሆን ጥቃት ለሚሰነዘር ሰው አፀፋ ሳይመልሱ በፍቅር ቀርቦ በውስጥ ያለውን መልካም ነገር በማንቀሳቀስ በህሊና ወቀስ ከክፉ ሥራው እንዲመለስ ማድረግ ይቻላል፡ ፡ የሚል ፍልስፍና ነው፡፡ ይህ የሰላማዊ ትግል የመጨረሻ ተሞክሮ በሰላማዊ ታጋዩ ወይም ሳትያግራሂው ላይ ከፍ ያለ ሥቃይን የማያስከትል እንደመሆነ በአስተሳሰቦች በሞራላዊነታቸውና በትዕግሥታቸው የላቀ ደረጃ ላይ የደረሱ ሰዎች ብቻ የሚተገብሩት ነው፡፡ ከሳትያግራሀ የሰላማዊ ትግል ስልቶች አንዱና ዋነኛው ከክፉ ሥራ ጋር ያለመተባበር ነው፡፡ እኔም አንድን ዓላማ ለማሳካት ኃይልን ከመጠቀም የበለጠ ክፉ ነገር አለ ብዬ ስለማሰብ ከእንዲህ አይነት ተግባር ጋር ተባብሬ አላውቅም፡፡ እንግዲህ ትጥቅ ትግል ውስጥ ያልተሳተፍኩት እላይ በጠቀስኳቸው ምክንያቶች እንጂ በማንምና በምንም ፍራቻ አሊያም አጋጣሚ አጥቼ አልነበረም፡፡ ከሳሾቼ እንደሚሉት ልጆች ሳላፈራና በትምህርት ሳልገፋ በአፍላ የወጣትነት ጊዜዬ ያላሰብኩትን ድንገት በሃምሳኛ ዓመት እድሜዬ ላይ በተራ የኦ.ነ.ግ ተዋጊነትና ካድሬነት ለመሠልጠን ኬንያና ሰሎሎ አልሄድኩም፡፡

ነፍስ ካወቅሁ ጊዜ ጀምሮ የሰው ልጆች መብት እንዲከበር ጽኑ ፍላጎና አቋም የነበረኝ ቢሆንም ሁሉም ሰው ፓለቲከኛ መሆን አለበት የሚል እምነት ስላለነበረኝ እስከ 2002 ዓ/ም ድረስ የማንኛውም ፖለቲካ ፓርቲ አባል ሆኜ አላውቅም፡፡ ተሰጥኦውና ዝናባሌው ያላቸው ጥቂቶች የፖለቲካ ማህበር መስርተው ለስልጣን ተወዳድረው ህዝባቸው በፍትሀዊነት ማስተዳደር ከቻሉ ሌሎች ዜጐች በተለያየ ሙያ ተሰማርተው አገራቸውን ማገልገል አለባቸው ብዬ ስለማምን እኔም በመምህርነት ሙያ ብቻ ተሰማርቼ ተግባሬን በትክክል ስወጣ ኖሬያለሁ፡፡

ይሁን እንጂ የፖለቲካ ድርጅቶች የሰዎች ስብሰብ እንደመሆናቸው መጠን ሁሉን ነገር ያለእንከን ይፈጽማሉ ብሎ ማመን ስለማይቻል ጊዜ ሊሰጣቸው እንደሚገባ በመረዳት ኢትዮጵያን እያስተዳደረ ያለው ፓርቲ የሚሰብከውን መተግበር እየተሳነው ሲሄድ ወይም በተፃራሪው ሲተገብር ሆን ብሎ አለመሆኑን ለራሴ ለማሳመን ሃያ አመታት ያህል ጥረት አድርጌያለሁ፡፡ በመጨረሻም በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ በተለይ ደግሞ በኦሮሞ ሕዝብ ላይ የሚደርሰውን በደል ዝም ብሎ መመልከትን ህሊናዬ አልቀበል አለኝ፡፡

– ሦስት መቶ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ጥያቄ እንኳን ሳይቀርብላቸው በአንድ ቀን ሲባረሩ
– በየዩኒቨርስቲው ያሉ ሌሎች ደግሞ በየዓመቱ ሲደበደቡና ሲንገላቱ
– የፋብሪካ ዝቃጭ አተላዎች በማንአለብኝነት ህዝብ ወደሚጠጣቸው ወንዞች ሲለቀቁና አደጋ ሲያስከትሉ
– ለፌዴራሉ መንግስት ከፍተኛውን ገቢ የሚያስገባ ህዝብ በአንፃሩ ግን በነፍስ ወከፍ እጅግ ዝቅተኛው የፌዴራል በጀት ድጐማ ሲመደብለት
– መሬቱ በስበብ አስባቡ በግፍ እየተወሰደ ተቸብችቦ ሌሎችን ባለፀጋ ሲያደርግ፤ የሱ ቤተሰቦች ግን የትም ሲበተኑ
– ቋንቋው ቀድሞ ሲነገር ከነበረበት ቦታ እየጠፋ ሲሄድ
– ከኤኮኖሚው ዘርፍ ወጥቶ የበይ ተመልካች ሲሆን
– የዛሬ 120 ዓመት የኦሮሞ መንደር በነበረቸው ፊንፊኔ በቋንቋው የሚማርበት አንድ ት/ቤት ወይም አንድ የእምነት ሥፍራ እንኳ ሲነፈገው
– የፌዴራል ሠራተኞች ቅጥርና የመከላከያ ሠራዊቱ አመራር ብሔራዊ ተዋጽኦ አግባብ ባልሆነ መልኩ ሲከናወን
– ከሁሉም በላይ ደግሞ ገዥው ፓርቲ ሥልጣን ሲይዝ በእስር ቤት ከነበሩ ኦሮሞ፣ ዛሬ በብዙ እጥፍ የሚሆኑት በፌዴራል ወህኒ ቤቶች ሲማቅቁና ቤተሰቦቻቸው በረሃብ አለንጋ ሲገረፉ እያየሁ ዝም ማለት እንዴት ይቻለኛል?
እነዚህ ነገሮች እንዲሰተካከሉ ህገ መንግስቱ በሚፈቅደው መሰረት በሠላማዊ መንገድ አስተዋፅኦ ለማድረግ የአንድ ፓርቲ አባል መሆንን ሳውጠነጥን የኦሮሞ ፌዴራሊስት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ኦ.ፌ.ዴ.ን/ ጥሪ አድርጐልኝ በ2002 ዓ/ም ለመጀመሪ ጊዜ አባል ሆንኩ፡፡ ከዚያም የድርጅቱ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ሆንኩ፡፡ በ2002 ዓ/ም ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ ሆኜ መላው ሕዝባችን በሚያውቀው ሁኔታ ተሸነፍኩ፡፡ በምርጫ ዘመቻ ወቅትም በግልና በቡድን የተካሄዱብኝን ትንኮሳዎች ተቋቁሜ መንግሥት ባሰማራቸው ሁከት ፈጣሪዎች መካከል ቆሜ ለሠላማዊ ትግልና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን መሆን ያለኝን ቁርጠኝነት አስመስክሬያለሁ፡፡ ምርጫውን እንደማላሸንፍና መጨረሻዬም አሁን ያለሁበት እስር ቤት እንደሆነ እየተነገረኝ አንድ ሰላማዊ ታጋይ ማድረግ ያለበትን አድርጊያለሁ፡፡

በፖርቲዬ ውስጥ በተሰጠኝ የሕዝብ ግንኙነት የሥራ ድርሻ ምክንያት በእስር ላይ ስላሉ ኦሮሞዎች ሁለት ጊዜ ያህል ለውጪ ሚዲያዎች ቃለ መጠይቅ በመሰብሰብ ከሳሾቼን እንዳላስደስታቸው ከራሳቸው ተነግሮኝ ነበር፡፡ ነገር ግን የሰጠሁት መረጃ ሀሰትም፣ ምሥጢርም እንዳልሆነ ነግሬያቸው በተያየን በሃያ ቀናት ከቢሮዬ ተጠርቼ ታሰርኩ፡ ፡ ከመታሰሬ ጥቂት ቀናት በፊት ከአምነስቲ ኢንተርናሽናል የመጡ ሰዎች አነጋግረውኝ ነበር፡፡ የእነዚህ ነገሮች ድምር ነው “የአገርና የሕዝብን አንድነት በማፍረስ” ወንጀል አስከስሶ ለእስራት የዳረገኝ፡፡

በሕዝቦች መካከል ግልጽ ልዩነት እየፈጠረ አንዱ ሌላውን እንዲጠራጠር ኅብረቱ እንዲላላና አንድነቱ እንዲፈርስ እያደረገ ያለ ሥርዓቱ ነው ወይስ ይህ ሁኔታ እንዲሰተካከል በሰላማዊ መንገድ እያሳሰበ በመታገል ላይ ያለ ሰው ነው የአገሪቱን የግዛትና የፖለቲካ አንድነት በማፍረስ ወንጀል የሚጠረጠረው? ህገ መንግሥቱን በተግባር እየጣሰ ያለውስ መብቴ ይከበር የሚለው ነው ወይንስ መብቱን የገፈፈው ነው?
ድርጅታችን በኢ.ፌ.ዴ.ን ህዝቦች መብታቸው እስከተከበረላቸው ድረስ የመገንጠል ጥያቄ አያነሱም መለየትንም አይፈልጉም የሚል እምነት ስላለውና የአገር አንድና ቁልፍ እውነተኛ እኩልነት የሰፈነበት ሥርዓት ማስፈን መሆኑን ያምናል፡፡

ስለዚህ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግሥት አንቀጽ 39 ንዑስ አንቀጽ 1 ላይ ያለው እስከመገንጠል የሚለው ሀረግ ጠቃሚ አይደለም በሚል እምነት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክረሲያዊ አንድነት መድረክ መለስተኛ የፖለቲካ ፕሮራም ውስጥ እንዲካተት ከፈረሙት አባል ድርጅቶች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ እኔም የድርጅቱ አባልና አመራር ይህን ለማሳመን ጉንበስ ቀና በምልበት ሰዓት የአገር አንድነትን ለማፍረስ በመሞከር እንዴት ልከሰስ እችላለሁ?
ማንኛውም ኦሮሞ መብቱን የመጠየቅ አዝማሚያ ወይም ከሥርዓቱ ጋር ያለመተባበር ዝናበሌ ያሳየ እንደሆነ በኦነግነት ፈረጆ ማናቸውንም የግፍ ተግባር መፈፀም ከተጀመረ ሃያ አመታት ተቆጠሩ፡፡ ይህ አድራጎት በአፍሪካ ደረጃ እንኳን ሲታይ ወደር የለሽ ነው፡፡ ናይጄሪያ በየጊዜው ፍንዳታ እያደረሰ ኃላፊነት በሚወስደው የቦኮሃራሞ ድርጅት አግባብ ተመሳሳይ ቋንቋ የሚናገሩና ተመሳሳይ እምነት የሚከተሉ ዜጐቿን ቁም ስቅል አላሳየችም፡፡ የወደቀው የግብጽ መንግስት እንኳን ህገወጥ ነው ብሎ በፈረጀው የሙስሊም ወንድማማቼች ፓርቲ አመካኝቶ ተቀናቃኞችን ለማጥፋት ዘመቻ አልከፈተም፡ ፡ ከአንድ የዘር የተገኘ ሁሉ አንድ አይነት የፖለቲካ አመለካከት አለው ብሎ የሚገምት ቢኖር በሥልጣን ላይ
ያለው የኢትዮጵያ መንግስት ብቻ ይመስለኛል፡፡ አገር የሚያፈርሰው እንዲህ አይነት አመለካከት ነው፡፡ እኔ ግን ይህን በመርህም ተቀብዬ በተግባርም ሞክሬ አላውቅም፡፡
ነገር ግን ለሥርዓቱ ካለመመቸት ውጪ በሀገሬና በሕዝቤ ላይ አንዳች ጥፋት እንዳልፈፀምኩ ጠንቅቀው የሚያውቁት ከሳሾቼ በወህኒ ቤቶች አካባቢ “አዳፍኔ” በመባል የሚታወቁ የሀሰት ምስክሮችን አቅርበው አስመስክረውብኛል፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ 1ኛ ነገሥት ምዕራፍ 21 ላይ አጽመርስቴን አልለቅም ስላለ “ንጉሡንና እግዚአብሔርን ሰድቧል” ብለው የሀሰት ምስክሮችን አስመስክረው ናቡቴን በድንጋይ አስወግረው እንዳስገደሉት የአክአብ ባለሥልጣኖች የሰው ልጆች መብት ይከበር ባልኩ ኢትዮጵያዊው ናቡቴ ሆኜ ቀርቤያለሁ፡፡ ይህ ድርጊት ከዚህ መዘምር ከሳሾች እራሳቸው ሲኒማ ቤት ውስጥ የእጅ ቦምብ ወርውረው ብዙ ሰዎችን ካቆሰሉ በኋላ ይህን ያደረገው ማሞ ነው በማለት በሀሰት አስመስክረው ሞት ተፈርዶበት አለም በቃኝ እስር ቤት ውስጥ በስቃላት ተቀጥቷል፡፡
በኔ ላይ የቀረቡት የአቃቤ ህግ ምስክሮች በቁጥር አራት ሲሆኑ ሁለቱ ቤቴ ሲፈተሸ ታዛቢ የነበሩ ናቸው፡፡ ሁለቱም ያዩትን በመመስክራቸው በምስክርነት ቃላቸው ውስጥ ወንጀለኛ የሚያሰኘኝ ነገር ባለመኖሩ ሌሎች ሁለት ምስክሮች በሰጡት የሀሰት ምስክርነት ቃል ላይ አተኩራለሁ፡፡ የአቃቤ ሕግ ምስክር ሆኖ የቀረበብኝ አንደኛው ሰው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዬ ሆኖ የተመደበ የክረምት ተማሪ ኢዮስያስ አበራ ማሞ ከሌሎች ተማሪዎች ተነጥሎ ቢሮዬ መጥቶ የገዥው ፓርቲ አባል እንደሆነ ይህን ያደረገውም የደህንነት አባል የሆነውን አባቱን በመፍራት እንደሆነ አሁን ግን በፓርቲው ውስጥ የሰፈነውን ኢፍትሐዊነት በመፀየፍ የአንድ ተቃዋሚ ፓርቲ አባል መሆን እንደሚፈልግ በተለይም ደግሞ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክን እንደሚያደንቅ ነግሮኝ እንድመለምለው ጠይቆኝ ነበረ፡፡ እኔም እኔ ያለሁበት ፓርቲ የኦሮሞ ድርጅት እንደሆነና የመድረክ አባላት ከሆኑ ህብረብሔር ፓርቲዎች ውስጥ ወስኖ አንዱን መጠየቅ እንዲሚችል ነግሬው የአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አመራር አባል የሆነውን የአቶ አንዱአለም አራጌን ስልክ ቁጥር ሰጠሁት፡፡

ግለሰቡ ክቡር ፍ/ቤቱ ፊት ቀርቦ ቃሉን ሲሰጥ ተማሪዬ እንደሆነ ኮርስ ሰጥቼው እንደማላውቅ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገናኘነው ሐምሌ ወር 2003 ዓ/ም የመመረቂያ ጽሁፉን ሊያስረክብ ቢሮዬ በተገኘበት ዕለት መሆኑን በዚሁ የመጀመሪያ ግኑኝነታችን “መንግሥት የኦሮሞንና የደቡብን ህዝብ ስለሚጠላ ይጨቁናቸዋል፣ ስለዚህ ተነሳስተን በአመጽ እናስወግደው” እንዳልኩት ተናግሯል፡፡ ሌሎችንም ተማሪዎች ጨምሮ እንደተወያየን አስመስሎ መስክሯል፡፡

ይህ ግን ፈጽሞ ሀሰት ነው፡ ፡ ግለሰቡ አግኝቶኝ የማያውቅ ከሆነ በሐምሌ 2003 ዓ/ም ሊያስረክበኝ የመጣው የመመረቂያ ጽሁፍ ማን ያማከረውን ነበር? ከአማካሪው ጋር አንዳች ግንኙነት ሳያደረግ ምንነቱ ያልታወቀ የመመረቂያ ጽሁፉን ይዞ ከመጣ ተማሪ ጋር ያውም በመጀመሪያው ግንኙነት ከአካዳሚ ነክ ጉዳዮች ወጥቶ ስለ መንግስት ግልበጣ ማውራት ይታሰባል ወይ? ለአንድ የዩኒቨርስቲ መምህር ተመካሪ ተማሪዎች የሚመደቡት በሚመለከተው ትምህርት ክፍል እንደመሆኑ የተለያየ ፖለቲካ ዝናባሌ እንዳላቸው እየታወቀ አንድን ወገን ብቻ በሚመለከት ፖለቲካ ውይይት መክፈት እንዴት ይታሰባል? የተከሰሰኩት በአሽባሪነት ከተፈረጀ የኦሮሞ ድርጅት ሆኖ ሳለ ግለሰቡ ደግሞ የዚህ ማህበረሰብ አባል አለመሆኑን በግልጽ እየተናገረ፤ ኦሮሞዎች ተበድለዋልና በመንግስት ግልበጣ ተባብረን ልል እንዴ እችላለሁ? ይህ ሰው ኦሮሞዎችን ከጭቆና ለመታደግ ከሰማየ ሰማያት የተላከ አዳኝ ነው ብዬ ልገምት አልችልም፡፡ ይልቅ እሱስ ፍትህን ሲገድል የተመደበ የአክአብ ምስክር ኖሯል፡፡
ሌላኛው ስሜን እንኳን በትክክል ያላስጠኑት የአቃቤ ሕግ ምስክር አመና አርኮ በክቡር ፍ/ቤቱ ፊት ቀርቦ ቃሉን ሲሰጥ “በጥር ወር 2002 ዓ/ም አቶ ጉቱ ሙሲሳ ቤት ተገናኝተን ለአመጽ አነሳስቶኛል” ሲል ተናግሯል፡፡

እኔ ይህን ግለሰብ ለመጀመሪያ ጊዜ ያየሁት ከዚሁ ፍ/ቤት ውስጥ ነው፡፡ ነገሩ የማይታመንና ዱብዕዳ ስለነበረ በዕለቱ ጥያቄም አላቀረብኩለትም፤ ስለማንነቱ ለማወቅ ባደረግሁት ጥረት በቂና ተጨባጭ መረጃዎችን ለማግኘት ችያለሁ፡፡ ግለሰቡ እውነተኛ ማንነቱ ኢመና ኢርኮ ሳይሆን ሺፈራው ኤቢዳ ሲሆን የትውልድ ሥፍራው በምዕራብ ሸዋ ዞን ሸነን ወረዳ ሆኖ አድራሻዬና የሥራ ቦታዬ ነው ያለውን ነቀምቴ ከተማ 01 ቀበሌን ረግጦ እንኳን አያውቅም፡፡

ይህ ግለሰብ የኦሮሞ ህዝብ ኮንግረስ /ኦ.ህ.ኮ /አባል የነበረ ሲሆን በ1997 ዓ/ም የምርጫ ታዛቢ ስነበር በ1998 ዓ.ም ታስሮ የተሠቃየ በ1999 ዓ.ም አጣሪ ኮሚሽን ፊት ቀርቦ ቃሉን የሠጠ በ2000 ዓ/ም ኦህኮን ወክሎ ለወረዳና ለቀበሌ ምርጫ የተወዳደረ፡ ፡ በ2003 ዓ/ም እንደገና ታስሮ የነበረ ሲሆን ይህን ሁሉ ያደረገው በእውነተኛ ስሙ ነበር፡ ፡ በመጨረሻም ከደረሰበት ስቃይ የተነሳ እንዲሁም የሚሉትን እሺ ካላለ መኖር እንደማይችል ስለተገለጸለት ያሉትን ሁሉ ለማድረግ ቃል ግብቶ በመፈታት በኔ ላይ በምስክርነት የቀረበ ነው፡፡ ይህንን የመከላከያ ምስክሮች ያስረዱልኛል፡፡
ከላይ እንደገለጽኩት ከግለሰቡ ጋር በአካልም ሆነ በማንኛውም የመገናኛ ዘዴ ተገናኝተን የማናውቅ ከመሆን አልፎ ቤቱ ተገናኘን ያለውን አቶ ጉታ ሙሊሳን እንኳን ለመጀመሪያ ጊዜ ያየሁት ማረሚያ ቤት ሁለታችንም እስረኞች ሆነን ነው፡፡ ይህንንም ምስክሮቼ ያረጋገጡልኛል ለመሆኑ በ2002 ዓ.ም ህገ መንግሥቱን አምኜና አክብሬ በምርጫ ለመሳተፍ ዝግጅት ላይ የነበርኩ ሰው እንዴት ሆኖ ለአመጽ ቅስቀሳ ማካሄድ የምችለው?
ከዚህ መረዳት እንደሚቻለው ግለሰቡ በኔ ላይ ስለመሰከረው ነገር ብቻ ሳይሆን ማንነቱንና አድራሻውን ጭምር እንዲዋሽ የተገደደ እንደመሆኑ መጠን ክቡር ፍ/ቤቱ ይህን ተመልክቶ የሰጠውን የምስክርነት ቃል ውድቅ እንዲያደርገልኝ እጠይቃለሁ፡፡
አቃቤ ህግ ወንጀለኛ ለመሆኔ እንደአስረጂነት ያቀረበው ሌላው የሠነድ ማስረጃ በ1989 ዓ/ም መጀመሪያ ላይ የተነሳሁት የኦነግ አርማ ተሰቅሎ የሚታይበት ፎቶ ግራፍ ነው፡፡ በ1983 ዓ.ም መጨረሻ ደረግ እሠራበት የነበረችውን ዓለም ተፈሪ ከተማ ለቆ ሲሄድ ብዙ ሰዎች አካባቢውን ለቀው ሲሰደዱ ሠላምና መረጋጋትን ለመፍጠር የተቋቋመውን ኮሚቴ እንድመራ በህዝብ ተመርጬ እስከ 1984 ዓ/ም መጨረሻ ድረስ ሰርቻለሁ፡፡ በዚህ ወቅት በከተማው ፍ/ቤት ከፍተው በይፋ ይንቀሳቀሱ ለነበሩ ሁለት የኦሮሞ ድርጅቶች ኦህዴድና ኦነግ ስብሰባዎችን እየጠራሁና እየመራሁ በገለልተኝነት ሥሰራ ቆይቻለሁ፡ ፡ በነዚህ ጊዜያት ውስጥ ለኦህዴድ በርካታ ስብሰባዎችን ለኦነግም ጥቂት ሰብሰባዎችን ከተማው መሃል በሚገኝ የወረዳው አስተዳደር ግቢ ሜዳ ላይ መጥራቴን አስታውሳለሁ፡ ፡ ከነዚህ ስብሰባዎች በአንዱ የተወሰደ ነው የተጠቀሰው ፎትግራፍ ያ ወቅት ሁለት ድርጅቶች እንኳን በመሰብሰቢያ ቦታዎች ቀርቶ በየምሶሶዎቹና ዛፎቹ አርማቻቸውን ይሰቅሉ የነበረ የትኩሳት ጊዜ ነበር፡፡
ኢፍትሐዊነትንና አድሎን …
ከ ገፅ 15 የዞረ….
በፎቶግራፍ ላይ እንደሚታየው ቁጥሩ ብዙ የሆነ ህዝብ ሜዳ ላይ ተሰብስቦ ይታያል፡፡ እንደሚታወቀው ኦነግ በ1984 ዓ/ም በመጨረሻ ሽግግር መንግሥቱን ለቆ ከወጣ በኋላ እንዲህ ዓይነት ስብሰባ በመሀል ከተማ አደባባይ ሊደረግ ይችላል ተብሎ አይታሰብም፡፡ በፎቶ ግራፉ ላይ የሚታዩ ሰዎች ብዙዎች በህይወት የሉም፡፡ በፎቶግራፉ ላይ የሚታየው የራሴ ገጽታም ከዛሬ ጋር ሲስተያይ የፎቶውን ዕድሜ ይናገራል፡፡ በፎቶግራፉ ላይ የሚታየው ቦታም ዓለምተፈሪ መሆኑ ተለይቶ ይታወቃል፡፡ እኔ ደግሞ በ1985 ዓ/ም ከዚያ ተዛውሬ ስለሄድኩ እና ወደዚያ ለመመለስ እድሉ ስላልነበረኝ፣ ቢኖረኝ ኖሮም ያንን ሰብሰባ ማካሄድ እንደማልችል ይታወቃል፡፡
በአጠቃላይ ከዛሬ ሃያ ዓመት በፊት በወቅቱ ህጋዊ የነበረና በሚኒስትሮች ም/ቤት አራት የካቢኔ ሚኒስተሮች የነበሩትና መዲናዋን (አዲስ አበባን) ጭምሮ በአርማዎቹ አጥለቅልቆት በነበረ ድርጅት አርማ ጋር የተነሳኸው ፎቶ ግራፍ የአገር ግዛትና ፖለቲካዊ አንድነት ለመንካትህ ማስረጃ ነው ተብሎ ሊቀርብብኝ ስለማይገባ ክቡር ፍ/ቤቱ ውድቅ እንዲደረግልኝ እጠይቃለሁ፡፡
ማጠቃለያ
ያለመተደል ሆኖ በአገራችን መልካም አስተዳደር አፈአዊ እንጂ ተግባራዊ ሆኖ ስለማያወቅ አንዱ የሠራውን ሌላው እያፈረሰ በዓለም ፊት በኩራት አንገታችንን ቀና የምናደርግበት ሳይሆን በሀፍረት የምንሸማቀቅበት፤ ለልጆቻችንም ተስፋን ሳሆን የስጋት ቅርስ እየተውንላቸው አበሳን እንደ ዱላ እየተቀባበልን ዛሬ ላይ ደርሰናል፡፡ ይህ እንዳይቀጥል የሳተው በጊዜ እንዲመለስ የተጣመመው እንዲቃና የተበላሸው እንዲስተካከል ጎረቤት ሳይሰማ፣ ፈረንጅ ገመናችንን ሳያውቀው አድብተን ሰንጠፋፋ ችግራችን ገለጥለጥ አድርገን ተወያይተን ተከራክረን ተወቃቅሰን መፍትሔ እናበጅለት፡፡ ይህንንም አንዱ ባንዱ ላይ ዱላ ሳይሰነዝር ቃታ ሳይስብ፣ ወደ እስር ቤት ሳይጎትተው በሠላማዊ መንገድና በፍቅር እናድርገው የሚል ጽኑ አቋም ነው፡፡ እኔና ድርጅቴ የምናራምደው፤ ይህ በኛ በጎ ጥረትና ፍላጎት ብቻ የሚሳካ ባይሆንም እኛ ግን በዚሁ መንገድ እንጓዛለን፤ ኢፍትሃዊነትንና አድልኦን አሜን ብሎ ውርደት ከመቀበል መከራና ስቃይን በክብር ማስተናገዳችንን እንቀጥላለን፡፡ በመጨረሻም ፍትህ ከጎናችን
ትቆማለች፡፡

የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ከአውሮፓ ህብረት ልዑካን ጋር ተወያዩ

የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ትላንት ህዳር 16 ቀን ከአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያ ልዑክ ኃላፊ ሻንታል ሄበርረሼት እና ከልዑኩ ተቀዳሚ ቆንስል እንዲሁም የፖለቲካ፣ የፕሬስና የኢንፎረሜሽን ኃላፊ ከሆኑት ሳነዲ ዋዴ ኦቤ ጋር በ2007 ምርጫ ዙሪያ መወያየታቸውን ከፓርቲው ህዝብ ግንኙነት ለፍኖተ ነፃነት የደረሰው መረጃ አመላከተ፡፡
ህብረቱ ባደረገላቸው ጥሪ መሰረት ውይይቱን ያደረጉት የአንድነት አመራሮች “እኛ በሀገራችን ለውጥ ለማምጣት የምንታገለው ሙሉ ለሙሉ ዕምነታችንን የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ጥለን ነው፡፡” ካሉ በኋላ የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ጉዳይ አሳስቦት ያቀረበውን ጥሪ አክብረው መምጣታቸውን ለህብረቱ ልዑካን አስረድተዋል፡፡ ምርጫ 2007ን በሚመለከት “አንድነት በምርጫ ለመሳተፍ ወስኗል፤ የምርጫውም ነፃ፣ ፍትሀዊና ተአማኒ እንዲሆን ይታገላል፡፡” በማለት የአንድነትን አቋም አስረድተዋል፡፡ አክለውም “ከምርጫ መውጣት ቀዳሚ ምርጫችን ባይሆንም፤ ምርጫው ለውጥ የማያመጣ ሆኖ በተገኘበት በየትኛውም ጊዜ ከምርጫው እንወጣለን” በማለት ተናግረዋል፡፡
አመራሮቹ አበክረው ለልዑካኑ ያስረዱት በየትኛውም ሁኔታ ኢህአዴግ አይን ያወጣ የምርጫ ዝርፊያ ቢያደርግ አንድነት በዝምታ እንደማይመለከት ማስረዳታቸውን የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ለፍኖተ ነፃነት አስታውቋል፡፡
Millions of voices for freedom – UDJ
UDJ


የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ለአዳሩ ሰልፍ የእውቅና ደብዳቤ አስገባ • ቦታው መስቀል አደባባይ እንዲሆን ወስኗል



በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ከህዳር 27/2007 ዓ.ም እስከ ህዳር 28/2007 ዓ.ም ለሚደረገው የአዳር ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬ ህዳር 18/2007 ዓ.ም ለአዲስ አበባ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል የእውቅና ደብዳቤ አስገባ፡፡
ለሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል የገባው ደብዳቤ በሰማያዊ፣ መኢዴፓ እና ኢብአፓ ተፈርሞ የገባ ሲሆን የእውቅና ደብዳቤውንም ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲና የትብብሩ ሊቀመንበር፣ የከንባታ ህዝቦች ሊቀመንበርና የትብብብሩ ም/ሊቀመንበር አቶ ኤርጫፎ ኤርጌሎ፣ አቶ ግርማ በቀለ ከኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅትና የትብብሩ ፀኃፊ እና የመኢዴፓ ሊቀመንበርና የትብብሩ ገንዘብ ያዥ አቶ ኑሪ ሙደሲር አስገብተዋል፡፡
የትብብሩ አመራሮች ወደ ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍሉ በሄዱበት ወቅት የአቶ ማርቆስ ተወካይ ለሆኑት አቶ ፈለቀ አበበ ደብዳቤውን ለመስጠት ጥረት ቢያደርጉም ተወካዩ ‹‹የከንቲባ ጉዳዮች ጽ/ቤ ኃላፊ አቶ አሰግድ ጌታቸው የለም፡፡ እሱ ካልመራበት መቀበል አንችልም›› በሚል ደብዳቤውን አልቀበልም እንዳሏቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ አመራሮቹ ወደ አቶ አሰግድ ቢሮ ቢያቀኑም እንዳላገኙዋቸው ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ሆኖም የትብብሩ አመራሮች ደብዳቤ መስጠት እንጂ ደብዳቤ ማስመራት የሰራተኞቹ እንጂ የእነሱ ስራ እንዳልሆነ በመግለጽ ደብዳቤውን ዛሬ ህዳር 18/2007 ዓ.ም ታመዋል የተባሉት የአቶ ማርቆስ ተወካይ የሆኑት አቶ ፈለቀ ቢሮ በአራት ምስክሮች ፊት አስቀምጠው መምጣታቸውን አስረድተዋል፡፡ አመራሮቹ የእውቅና ደብዳቤውን አቶ ፈለቀ ቢሮ አስቀምጠው ከመውጣታቸውም ባሻገር በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት በፈጣን መልዕክት (ኢ ኤም ኤስ) በሪኮመንዴ ቁጥር eg157416502et መላካቸውን ገልጸዋል፡፡
የአዳር ሰላማዊ ሰልፉ ህዳር 27 ከጠዋቱ 3 ሰዓት ተጀምሮ ህዳር 28 ከቀኑ 6 ሰዓት ላይ እንደሚጠናቀቅ የሚጠበቅ ሲሆን ቦታውም መስቀል አደባባይ ላይ እንደሚሆን መወሰኑ ታውቋል፡፡
የትብብሩ አመራሮች የእውቅና ደብዳቤውን ለማስገባት በሄዱበት ወቅት በቦታው የትብብሩ አመራሮች የሚያውቋቸው ደህንነቶች ባለ ጉዳይ በመምሰል ይመላለሱ እንደነበርና ፖሊሶችም ይከታተሉ እንደነበር ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

Mittwoch, 26. November 2014

በ21ኛው ክ/ዘመን መንግሥት አላባዋ ሀገር ፣መንግሥት አልባው ሕዝብ ።

ትላንት ውባለም የተባለች አንዲት ኢትዮጵያዊት እለት ቤይሩት ኢጀኑብ (ኢዘሪሂ) በሚባለው ከከተማው ወጣ ባለ አካባቢ ራሷን ከሶስተኛ ፎቅ ላይ ወረወረche
የኢትዮጵያውያን ደም እንደውሻና እንደ ድመት በአረብ ሀገር አውራ ጎዳና ላይ መፍሰሱ የተለመደ በመሆኑ ዛሬ ዛሬ እንደዜና ለወሬም አልተመቸም አሰልች ሁኗል ።
ትላንት ውባለም የተባለች አንዲት ኢትዮጵያዊት  ቤይሩት ኢጀኑብ (ኢዘሪሂ) በሚባለው ከከተማው ወጣ ባለ አካባቢ ራሷን
ከሶስተኛ ፎቅ ላይ በመጣል ህይወታ ሊያልፍ ችልዋል።
በትላንትናው እለት የ20 አመት እድሜ ያላት ውባለም የተባለች አንዲት ኢትዮጵያዊት የቤት ሰራተኛ በደቡብባዊ ሊባኖን ከአሰሪዎቿ ቤት 2ኛ ፎቅ ላይ ወድቃ ህይወቷ ማለፉ ተነገረ፡፡
አንዳንድ አለምአቀፍ ድርጅቶች የቤት ሰራተኞች ሰብዓዊ መብቶች በስፋት በሚጣስባት ሊባኖን ሰራተኞች ጥቃት እዳይደርስባቸው ለመከላከል እንቅስቃሴ መጀመራቸውን ዴይሊ ስታር ሲዘግብ
በአረብ ሀገራት የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ጥቃት የሚደርስባቸው ቢሆንም በየአረብ ሀገራቱ የሚገኙት የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ወይም ቆንፅላ ጽ/ቤቶች ችግሩን ለመቅረፍ የሚያደርጉት ጥረት እንደሌለ አንዳንድ በአረብ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ተናግረዋል፡፡
የዜጎች መብትን ማስጠበቅ ካልተቻለ የኤምባሲዎቹና ቆንፅላ ጽ/ቤቶች እዛ መገኘት ፋይዳው ግልፅ አይደለም ይላሉ ችግሮቹን በቅርበት የሚመለከቱ ኢትዮጵያውያን፡፡

የሽብር ክስ የቀረበባቸው የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ለታህሳስ 9 ቀጠሮ ተሰጠባቸው


በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ በፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ የተመሰረተባቸው አራቱ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች እና በተመሳሳይ መዝገብ የተከሰሱት ሌሎች ስድስት ተከሳሾች የቀረበባቸውን የክስ መቃወሚያ እንዲያቀርቡ ለታህሳስ 9 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡
የአንድነት፣ የሰማያዊና የአረና ፓርቲዎች አመራሮች የሆኑት አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታ እና ዳንኤል ሺበሽ በሚገኙበት የክስ መዝገብ የተከሰሱት አስሩም ተከሳሾች ዛሬ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት፣ የተከሳሽ ጠበቆች በጠየቁት መሰረት የተከሳሾቹን የክስ መቃወሚያ ለመቀበል ፍርድ ቤቱ ለታህሳስ 9/2007 ዓ.ም ጠዋት 3፡00 ቀጠሮ ይዟል፡፡
በሌላ በኩል የተከሳሽ ጠበቆች በተከሳሾች ላይ አቃቤ ህግ አለኝ ያላቸውን የሰነድ ማስረጃዎች ዝርዝር እንዲደርሳቸው መጠየቃቸው የሚታወስ ሲሆን፣ አቃቤ ህግ ግን እስካሁን ድረስ ዝርዝሩን ለተከሳሽ ጠበቆች አለማቅረቡን በመጥቀስ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲደርሳቸው እንደሚያደርግ አስረድቷል፡፡ የማስረጃው አለመሟላት ሁሉንም ተከሳሾች የሚመለከት አለመሆኑን ያወሳው አቃቤ ህግ፣ ለአብነት 10ኛ ተከሳሽ አቶ ተስፋዬ ተፈሪ ከብሄራዊ መረጃ ደህንነት የተገኙ ማስረጃዎች እንደማይመለከቱት አስረድቷል፡፡
ተከሳሾቹ በ1994 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ እና አወዛጋቢውን የፀረ-ሽብር አዋጅ አንቀጾች በመተላለፍ በሽብር ወንጀል ተካፍለዋል፣ ድርጊቱን ለመፈጸም ተንቀሳቅሰዋል፣ ህዝብን ለአመጽ ቀስቅሰዋል በሚል ተጠርጥረው ጥቅምት 21 ቀን 2007 ዓ.ም በይፋ ክስ እንደተመሰረተባቸው የሚታወስ ነው፡፡

ከ9ኙ ፓርዎች ትብብር የተሰጠ መግለጫ ማስፈራራትና አፈና የዲሞክራሲ ጥያቄዎችንና ሠላማዊ ሕዝባዊ የለውጥ ንቅናቄዎችን አይቀለብስም !!

የኢተፖፓ ትብብር አባላት በደረስንበት ስምምነት መሠረት የአጭር ጊዜ የጋራ ዓላማችንን ማስፈጸሚያ ተግባራት የመጀመሪያ ዙር ‹‹ ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል መርህ የአንድ ወር ዕቅድ አውጥተን ወደ ሥራ እንደገባን በገዢው ፓርቲ/መንግሥት ለ07/03/07 በታቀደው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ የዕውቅና ጥያቄ ሂደትና በዕለቱ የተፈጸመውን ሴራ በሚመለከት ‹‹በቢሮክራሲያዊ ሴራ የዜጎችን ህገመንግሥታዊ መብት ማፈን ሠላማዊ ትግሉን አያቆመውም //›› በሚል ርዕስ ሕዳር 08 ቀን 2007 ዓ.ም. ባወጣነው መግለጫ የድርጊቱን ህገወጥነትና ኢህገመንግሥታዊነት አሳይተን ለባለድርሻ አካላት አፍራሽ አካሄዱ እንዲስተካከልና ለዚህ ከምናደርገው ሠላማዊ ትግል ጎን እንዲቆሙ ጥሪያችንን ማስተላለፋችን ይታወሳል፡፡ በመቀጠልም ዕቅዳችንን በመከለስ የቀጣይ ተግባራት ዝግጅታችንን ጀምረናል፡፡ በዚሁ መሰረት ለ21/03/07 ላቀድነው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በ10/03/07 በአባል ድርጅታችን የመላው ኢትዮጵያዊያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ/መኢዴፓ/ አማካኝነት የዕውቅና ጥያቄ ደብዳቤ ይዘን በአካል ብንቀርብም ሁለት ቀን አመላልሰውን በመጨረሻ የአዲስ አበባ መስተዳድር የከንቲባ ጽ/ቤትና የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ አሰግድ ጌታቸው ይመኑ ደብዳቤኣችንን ለመቀበል ፈቃደኛ ያለመሆናቸውን ከመግለጽ አልፈው ‹‹የአብዬን እከክ ወደ እምዬ…››እንዲሉ ቢሮኣቸው ደብዳቤውን አስቀምጠን ስንወጣ ወንጀል ነው በማለት ለማስፈራራት ሞክረዋል፡፡
ባለፈው ሣምንት በተፈጸመብን ሴራ ያለመንበርከካችንን ከቀረበው ደብዳቤ የተረዱ የሚመስሉት እኚሁ ባለሥልጣን በቀጣዩ ቀን(12/03/07 ዓ.ም) የባለፈውን የአደባባይ ስብሰባ እንዲያስተባብር ኃላፊነት በሰጠነው ሰማያዊ ፓርቲ ላይ ‹‹ማስጠንቀቂያ›› በሚል ለተጨማሪ ማስፈራሪያ ደብዳቤ ጽፈዋል፡፡ይህ ዛሬ በወህኒ የሚገኙ በሽብርተኝነትና ህገመንግሥት በመጣስ በሚል የታሰሩ የፓርቲ አመራሮችና አባላት፣የኃይማኖት መሪዎች፣ጋዜጠኞች ፣ብሎጌሮች፣ከገዢው ፓርቲ የተለየ አመለካከት ያላቸውን ዜጎች በመፈረጅ ለማሰር፣ ማሰቃት… የተከደበትን ስልት፣ዛሬም በእኛም ሆነ ሌሎች ላይ እየተሞከረ ያለውን የማስፈራራትና የማሸማቀቅ ሙከራ ከሚያስተውሰን በቀር በህጋዊና ሠላማዊ ትግላችን የሚፈለገውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ስለተዘጋጀን የሚፈራ አልተገኘም፣ ከቁብ አልቆጠርነውም፡፡
በዚያው ዕለት(12/03/07 ዓ.ም) በአካል ተገኝተን አንቀበልም የተባልነውን ደብዳቤ በመንግሥታዊው የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት በፈጣን መልዕክት አገልግሎት/ኢ.ኤም.ኤስ/ በቁጥር eg156846735et ብንልክም የቱም የመስተዳድሩ አካል ደብዳቤውን ለመቀበል ፈቃደኛ ያለመሆኑ በ16/03/07 ከፖስታ አገልግሎቱ ተገልጾልናል፡፡ ይህ በህገ መንግስቱ አንቀጽ 12 የተቀመጠውን ‹‹የመንግስት አሠራር ተጠያቂነት›› የጨፈለቀ ድርጊት በተገለጸልን ተመሳሳይ ጊዜ ደብዳቤውን የጻፈው የመላው ኢትዮጵያዊያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ/መኢዴፓ/ ሊቀመንበርና የትብብሩ ፋይናንስ ኃላፊ (ደብዳቤውን ሲያቀርቡ አንቀበልም የተባሉት) አቶ ኑሪ ሙዴሲር ‹‹ በመኪና ተገጭተው መደባደብ በሚችሉ ጀግና›› እና ግብረ-አበሮቻቸው ተደብድበው በአካላቸው ሦስት ቦታዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ይህ ትናንት በአቡበከር ላይ የተሞከረውን ተመሳሳይ የፈጠራ ውንጀላና ክስ የሚያስታውሰን ሲሆን ክሱ የማያዋጣ መሆኑ ሲታወቅ ‹‹ ተገጭቶ የሚደበድብ›› ወሮበላ ወደማሰማራት መሸጋገሩን ያረጋግጣል፡፡ እነዚህ ድርጊቶች በገዢው ፓርቲ/መንግስት የሚፈጸሙ ከተለመዱ የፈጠራ ውንጀላ፣እሥራት፣ድብደባ … የፍርኃቱ እርከን ወደከፋ ደረጃ መሸጋገሩን ከማረጋገጣቸው በተጨማሪ ቀጣይ ትግላችን የሚጠይቀውን ከፍተኛ መስዋዕትነት ያመለክታሉ እንጂ የህዝቡን የለውጥ ፍላጎትና ለዚያ የሚደረገውን ትግል አፍነው አያቆሙም ፣ለውጡን አያስቀሩትም፡፡ ትብብሩን ከትግሉ እንዲያፈገፍግ አያደርጉም፡፡
በመሆኑም ዛሬም የዕውቅና ጥያቄኣችንን በመስተዳድሩ የፋክስ አድራሻዎች ደግመን አድርሰናቸዋል፡፡
እኛ የጋራ ትግላችንን ‹‹ ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› ብለን ስንጀምር ‹‹ነጻነት በሌለበት ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አይኖርም›› በሚል እምነት በመሆኑ ጥያቄው የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና የሠላማዊ ሥልጣን ሽግግር ነው፡፡ከሌሎች የተቃውሞ ጎራ ፓርቲዎች ጋር ከምርጫ በፊት ‹‹ስለ ፖለቲካ ምህዳሩ›› እና ብሄራዊ መግባባትና ዕርቅ እንነጋገር ስንል ህዝቡ የአገሩና የሥልጣን ባለቤት ይሁን፣በውስጡ ከያዘው መልዕክት አንዱ ስለ ነጻ፣ ፍትሃዊ፣ አሳታፊ፣ ተኣማኒ ምርጫ እንነጋገር የሚል ነው፡፡ ከምርጫ አንጻር እነዚህ ጥያቄዎች በዋነኛነት፡- ፍትሃዊ የሚዲያ አጠቃቀምን፣የፖለቲካ ፓርቲዎችን ነጻ እንቅስቃሴና የፓርቲዎችን እኩልነት፣ የምርጫ ሂደቱን አሳታፊነትና የምርጫ ቦርድን ገለልተኝነትና ግልጽነት፣ የመራጩን ህዝብ በህገ መንግስታዊ መብቱ ተጠቅሞ በነጻነትና በባለቤትነት (ሳይፈራና ሳይሸማቀቅ) በንቃት የመሳተፍ፣የሲቪክና ዲሞክራቲክ ድርጅቶችና ማኅበራት ነጻ ተሳትፎ መረጋገጥ… እነዚህን መብቶች ለመቀማት የተዘጋጁ ህገመንግሥቱን የሚቃረኑ አፋኝ ህጎች መሻር/መታረምና በነዚህ ህጎች የታሰሩ ዜጎች ተፈተው በሙያቸውና አደረጃጀታቸው ሠላማዊ ትግሉን እንዲቀላቀሉ ማለታችን ነው፡፡
ጥያቄዎቻችን ግልጽ፣ ትግላችንም ህጋዊና ሠላማዊ በሆነበት ከላይ የተገለጹት ድርጊቶች የሚያሳዩት በገዢው ፓርቲ/መንግሥት የተመረጠው ኢህገመንግሥታዊና ኢዲሞክራሲያዊ የአፈና አካሄድ መሆኑንና የመንግሥት አስፈጻሚ ተቋማት በገዢው ፓርቲ ሙሉ ቁጥጥር ሥር ወድቀው ለተቋቋሙበት ዓላማ ለስፈጸሚያ በህግ የተሰጣቸውን መብት እንኳ ሊጠቀሙ የማይችሉ መሆኑን፣ ይህም ያነሳናቸው ጥያቄዎችን ትክክለኛነት የሚያረጋግጥ ነው፡፡ በመሆኑም በእኛ በኩል ‹‹ ነጻነታችን በእጃችን›› በመሆኑ በኢህገመንግሥታዊና ኢዲሞክራሲያዊ እርምጃዎች ወደኋላ ሳናፈገፍግ፣ እያንዳንዳችን በተናጠል የተደረጀንበትን፣ በጋራ የተባበርንበትንና የቆምንለትን ዓላማ በአፈና ላለመጣል ለአገራችንንና ህዝቧ የምንቆጥበው የለንምና በሰላማዊ ትግሉ እስከ ህይወት መስዋዕትነት በመክፈል ዕቅዳችንን በህጋዊ መንገድ ለማስቀጠል ያለንን ዝግጁነትና ቁርጠኝነት ዛሬም ደግመን እያረጋገጥን ፡-
1ኛ/ ገዢው ፓርቲ/መንግሥት የሚከተለውን አምባገነናዊ አካሄድ እያወገዝን፣ ከነዚህ ድርጊቶች እንዲገታና ህገመንግስቱን አክብሮ የማስከበር ኃላፊነቱን እንዲወጣ፣ ላቀረብነው ህጋዊ የዕውቅና ጥያቄ በአስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጥ፤
2ኛ/ ጥያቄዎቻችን የአገርና የህዝብ ጉዳይ ፣የመድብለ ፓርቲ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ በመሆኑ ቀዳሚ ባለቤቶቹ በአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጪ የምትገኙ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ለቀጣዩ ሠላማዊ ትግል የምናቀርበውን ጥሪ በንቃት እንድትከታተሉና ከጎናችን እንድትቆሙ፤
3ኛ/በትብብሩ ያልታቀፋችሁ፣ በተለይም በሂደቱ ከጅምሩ እስከ መጨረሻው ተሳትፋችሁ የስምምነቱን ሰነድ ያልፈረማችሁ፣ ዲሞክራቲክ የፖለቲካ ኃይሎች ከትብብሩና ከተያያዝነው ትግል በአስቸኳይ እንድትቀላቀሉ፤
4ኛ/ ለሰብዐዊና ዲሞክራሲያዊ መብት መከበርና ለዘላቂ ሠላም የቆማችሁ የዓለም አቀፉና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላትና መንግስታት በገዢው ፓርቲ/መንግሥት ላይ አዎንታዊ ጫና እንድታሳድሩ፤ጥሪያችንን በድጋሚ እናቀርባለን፡፡
ያለመስዋዕትነት ድል የለም//
ሕዳር 17 ቀን 2007 ዓ.ም.፤ አዲስ አበባ፡፡

Dienstag, 25. November 2014

ቆንጆ መጽሔት ተከሰሰች

ከመጽሔቷ ዋና አዘጋጅ ቴዎድሮስ ካሳ
1507102_562094813935307_9108390875166530007_nከሁለት ሳምንት በፊት ከማዕከላዊ የምርመራ ቢሮ ከወዲያኛው ጫፍ የደወለው ሰው እንደነገረኝ ‹‹ከፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ነው›› ብሎ ደወለልኝ፡፡ ደዋዩ ቆንጆ መጽሔት መሆኑን ካጣራ በኋላ ዋና አዘጋጇ ስልክ ላይ ብደውል ዝግ ነው ፤ ጥር ወር ላይ ባወጣችሁት ዘገባ እኛ ጋ ክስ ተመስርቶባችኋል አለኝ፡፡ ስለሆነም ለዋና አዘጋጇ መልዕክት አድርሱ መጥታ ቃሏን ትስጥ አለኝ፡፡ ለጊዜው በቅርብ እንደሌለች ነገርኩት፡፡ ‹‹እሺ›› ብሎ ስልኩን ዘጋው፡፡ ድጋሚ ባለፈው ሳምንት አንድ ስልክ ተደወለ፡፡ በወቅቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ስለነበርኩ ስልኩን ማንሳት አልቻልኩም፡፡ ስወጣ ግን ደወልኩ፡፡ ስልኩን ያነሳችው ሴት ‹‹የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ዋና (ማዞሪያ ስልክ)›› መሆኑን ነገረችኝ፡፡ እንግዲህ ይህ ስልክ ግቢ ውስጥ ያሉት አብዛኞቹ የሚጠቀሙበት በመሆኑ እንደ እኔ ሞባይሉ ላይ ሚስድ ኮል አይቶ መልሶ ለደወለ ማን እንደደወለለት ገና ተጠያይቆ ነው የሚታወቀው፡፡

ትናንት የደወለችው ግን ቁጣ በተቀላቀለው ንግግር ‹‹ለምንድነው ስልክ የማታነሱት›› አለች፡፡ ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢንተርቪውና ሌሎች ጥሞና የሚፈልጉ (የስልክ ድምጽ የሚረብሹ) ስራዎች ላይ ለሆነ ጋዜጠኛ ስክል ያለማንሳት የተለመደ ጉዳይ መሆኑን ላስረዳት ሞከርኩ፡፡ ስንትን በስንት እንዳባዛችው ባይታወቅም በተደጋጋሚ ጊዜ መደወሏን ተናግራ ‹‹ለረቡዕ ጠዋት ማዕከላዊ መጥተው ቃሎትን እንዲሰጡ›› አለች፡፡

በዚህ ጉዳይ ጥር ላይ ያሳተማችሁት ዕትም ስለተባልኩ ባለፈው ዓመት ጥር ወር ላይ ያሳተምናቸውን ሁለት ዕትሞች ደግሜ ለማየት ሞከርኩ፡፡ የታየኝ ነገር የለም፡፡ እንግዲህ እነሱ የታያቸው ነገር ይኖራል፡፡ በዚያ ላይ ከሳሽ ማን እንደሆነ አልታወቀም፡፡ አቃቤ ህግ? መንግስት? ግለሰብ? ማህበር?. . . የታወቀ ነገር የለም፡፡

ባለፈው ዓመት የዛሬው ኢቢሲ የአምናው ኢቲቪ በሰራው ተከታታይ የዶክመንተሪ ፊልም ምክኒያት በብዙ መጽሔቶችና ጋዜጦች ላይ ክስ ተመስርቶ የቆንጆ መጽሔት አዘጋጆችን ጨምሮ በርካታ ጋዜጠኞች ለስደት ተዳርገዋል፡፡ ተመስገን ደሳለኝንና ብዙ ጋዜጠኞች ለእስር ተዳርገዋል፡፡ ዶክመንተሪው የግል የህትመት ውጤቶችን በሙሉ ሀጢአተኛ አድርጎ ስለፈረጀ ማተሚያ ቤቶች ጋዜጣና መጽሔቶችን ማተም ፈርተዋል፡፡ ዶክመንተሪው የግል ሚዲያውን ብቻ ሳይሆን ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የግንቦት 7 እና የሻዕቢያ ተላላኪ፤ የታሰሩ ሙስሊሞችን ገና ጉዳያቸው በፍ/ቤት እየታየ ባለበት ሁኔታ ላይ አክራሪ፤ ብሎገርና ሌሎችንም ስም እየሰጡና እየፈረጁ በፍ/ቤቶች ላይ ጫና እስከማሳደር የሚደርስ ዘገባዎች ሲሰራጩ ኢቲቪ ነውና ማንም አይጠይቀውም፡፡ የግሉ ሚዲያ ላይ ሲሆን ግን. . .
አዲስ አድማስ ጋዜጣ ባለፈው ቅዳሜ ለንባብ እንዳበቃው የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርት ላይ አሁንም ክስ የሚመሰረትባቸው የህትመት ውጤቶች መኖራቸውን ጠቁሟል፡፡ በዚህ መልኩ ወደ ፊት በኢትዮጵያ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ውጪ የህትመት ውጤቶች ስለመኖራቸው እንድንጠራጠር ያደርገናል፡፡

ጋዜጠኞችን በማሰርና በማሳደድ የቀዳሚነቱን ስፍራ የተቆናጠጠችው ሀገራችን የወደፊት የዴሞክራሲ እጣ ፈንታዋ ምን ይሆን? ይህ ነገር በዚሁ እንዳይቀጥል፤ የጋዜጠኞች እስርና ስደት እንዲቆም ከመንግስት ኃላፊዎች ጋር ቀርቦ ለመነጋገር የተደረገው ጥረት በኃላፊዎቹ ግትርነት መፍትሔ ማግኘት አልቻለም፡፡ ‹‹የተሰደደና የታሰረ ጋዜጠኛ የለም›› እስከማለት ደርሰዋል አይናቸውን በጨው አጥበው፡፡ የጋዜጠኞች እስርና ስደት የሀገርንና የመንግስትን ስም ጥቁር ጥላሸት ከመቀባት ውጪ ለሀገርም ለህዝብም የሚጠቅም ነገር ያለመኖሩን በተደጋጋሚ ቢነገርም ሹማምንቱ ጆሮ ዳባ ልበስ ብለዋል፡፡
የነገው የማዕከላዊ ቀጠሮዬን እያሰብኩ ይህቺን ሰነቅኩላችሁ፡፡

የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል በፖስታ የተላከውን የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ደብዳቤ አልቀበልም አለ



የአዲስ አበባ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል 9ኙ ፓርቲዎች ህዳር 21 ለሚያደርጉት የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በፖስታ ቤት የተላከለትን ደብዳቤ አልቀበልም ማለቱን የስብሰባው አስተባባሪ የሆነው የመኢዴፓ ፀሀፊ አቶ ዘመኑ ሞላ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ህዳር 21/2007 ዓ.ም ለሚያደርጉትና መኢዴፓ ለሚያስተባብረው ስብሰባ ረቡዕ ህዳር 10 የመኢዴፓ አመራሮች ደብዳቤውን ለማስገባት ሄደው የነበር ቢሆንም አቶ ማርቆስ ብዙነህ እና እሳቸውን ተክተው ሲሰሩ የነበሩት አቶ ፈለቀ ታመዋል በሚል የከንቲባ ጉዳይ የካቢኔዎች ኃላፊ አቶ አሰግድ ጌታቸው ማሳወቂያ ደብዳቤውን አንቀበልም ማለታቸው ይታወቃል፡፡

በተመሳሳይ ህዳር 12 ወደ ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍሉ ያቀኑት የትብብሩ አመራሮች ደብዳቤውን የሚቀበላቸው ሲያጡ ጠረጴዛ ላይ ጥለውት የመጡ ሲሆን በፖስታ ቤት በሪኮመንዴ eg156846735et እንደላኩ የትብብሩን ፀኃፊ አቶ ግርማ በቀለን ጠቅሰን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ 

ለአዲስ አበባ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል በፖስታ የተላከውን ደብዳቤ ቢደርስም አመራሮቹና ሰራተኞቹ ደብዳቤውን ለመቀበል ፈቃደኛ እንዳልሆኑ ፖስታ ቤት ድረስ በመሄድ እንዳረጋገጡ አቶ ዘመኑ ሞላ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል ሰራተኞችና አመራሮች ፖስተኛው ደብዳቤው የሚሰጥበትን ቢሮ ሲጠይቅ ለማሳየት ፈቃደና እንዳልሆኑና በስተመጨረሻም ‹‹ተቀባይ የለውም ብለህ መለስ፡፡›› እንደተባሉት አቶ ዘመኑ ሞላ ገልጸዋል፡፡

Montag, 24. November 2014

በፒያሳው ቦንብ ፍንዳታ ዋና አቀናባሪው ተስፋዬ ገ/አብ መሆኑን ያውቃሉ? (ሊያነቡት የሚገባ) (በአለማየሁ መሰለ )

Image
ለዛሬ የማቀርበው መረጃ ተስፋዬ ገብረአብ እንደ ሸፋን ከሚጠቀምበት የደራሲነት እናየጋዜጠኘነት ስራ ባሻገር ለማመን በሚያዳግት ይሰራ የነበረውን የወንጀል ድርጊት ፍንትው አድርጎ ያሳያል።ከዚህ በታች አባሪ ተደርጎ የተያያዘው በእጅ የተጻፈ መረጃ፣በእጄ ላይ ካሉ መረጃዎች መሃከልትኩረቴን የሳበው ነው።እንደምትመለከቱት በራሱ በተስፋዬ ገብረአብእጅየተጻፈነው።ከሌሎችመረጃዎች ለየት የሚያደርገው ደግሞ፣እንደሌሎች መረጃዎች በፎቶኮፒ እጄ ላይ የቀረሳይሆን፣ዋናው(ኦርጅናል)መሆኑ ነው። ምክንያቱም በቀጥታ ወንጀል የተጻፈበት ሆኖ ስለታየኝ ነው።ከእጅጽሁፉ ላይ እንደምትመለከቱት፣መኩሪያ መካሻ ከተባለ ግለሰብ ጋር ድብቅ(ህቡእ) ስራ ለመስራትጀምረው ነበር።እንደኔ ግምት የኤርትራ መንግስትን ጥቅም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያስፈጽማልብለው ያሰቡትን ተልእኮ ለመፈጸም አሲረው ነበር፡፡እንደ መረጃው ከሆነ መኩሪያ መካሻ የተባለውግለሰብ ከፒያሳው ቦንብ ፍንዳታ በኋላ ፈርቶ ይሁን ሌላ ባይታወቅም፣ከተስፋዬ ጋር ያለውን
ግንኙነት አቋርጧል።የፒያሳው የቦንብ ፋንዳታ ብሎ የተገለጸው ደግሞ ሌላ ሳይሆን በ2002 እኤአበትግራይ ሆቴል ላይ የደረሰው ፍንዳታ ነው።የእጅ ጽሁፉን ሙሉ ይዘትና ለአንባቢ ይመች ዘንድ የተየብኩትን ይመሳከር ዘንድ እንደሚከተለው
አቅርቤዋለሁ።አሰሪ መሆንና በቀጥታ ከእሳቱ ጋር መጋፈጥ ልዩነት አላቸው መኩሪያ መካሻ የተባለው ሰው ጥሩ ጀምሮነበረ።ፒያሳ ላይ ቦምብ ሲፈነዳ ከእኔ ጋራ ያለንን ግንኙነት አቁዋረጠ።በጣም ጉዋደኛየ ነበር ለስራውስል ሰዋሁት። ጉዋደኛንመሰዋቴ ትልቅ ነገር አይደለም።ህይወታቸውን የሰዉ፣ክቡር ዜጎች ያሉበት ሃገርሰው ነኘና። እዚህ ላይ በትክክል ማሰብ እችላለሁ።አስቃቂውን ስሜቴን ግን ለመግለጽ ያህል ነው።ያሸማቅቁሃል ሲሳካልኝ በደስታ መጠጣት፣ሲከሽፍብኝ በንዴት መጠጣት፣ልምድ አደረግኩት።ደረጀደስታ እራሱ ከገፋፋኝ በሁዋላ መልሶ በኢትኦጵያ የማምን ኢትዬጵያዊ ነኝ ሲለኝ ምን እንደሚሰማገምቱት።
ሚኒስትር የነበረው ደስታ ወልደማርያም ጋር ለዘላለሙ ተለያይቻለሁ።እነዚህ ሰዎች ለወያኔ ነግረው ምንያስፈጽሙብኝ ይሆን የሚል ስጋት አለብኝ።ያድዋን ወረዳ ያበላሸው ………… የደረሰበትን ታሪክእያሰብኩ መሰቃየቴን አልተውኩም።ከብብቱፈልቅቄ ካስቀረዋቸው መረጃዎች ከዚህ በታች እንደምታዩት በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ላይየኢትዬኤርትራ ጦርነት በሁዋላ እሱም እንዳለቆቹ እንዳቄመ ነው የምናየው።እስከጦርነቱ መጀመሪያ ድረስግን፣የህወሃት አባልነቱን ግዴታ ለመወጣት በአለቆቹ ታዞ ይሁን በራሱ ተነሳሽነት የአማራንና የኦሮሞንህዝብ ለማጋጨት ነበር ስራዬ ብሎ የተያያዘው።አሁን ደግሞ በኤርትራ የመረጃና ደህንነት መስሪያቤትፕሮጀክት ተቀርጾለት የትግራይ ህዝብንም የትኩረታቸው መነሻና መድረሻ አካተው በተቀረው የኢትዬጵያህዝብ ለማስጠላትና ለማሸማቀቅ፣የተስፋዬ ገብረአብን ብእር እንደዋነኛ መሳሪያ እየተጠሙበት እንደሆነበግልጽ ማየት ይቻላል።ከላይ እንደገለጽኩት መስሪያ ቤቱ በሃገራችን ህዝቦች መሃል ያለውን መተማመን እና አንድነት ለማትፋትፕሮጀክት ተቀርጽለት ከፍተኛ በጀት ተመድቦለት በዚህ ግለሰብ ኣማካኝነት እየተፈፀመ የከረመው እና
ሊፈፀም እየቴሰረ ያለው ሤራ እንደሚከተለው ይሆናል፥፥አጠቃላይ የግቡ አላማ የኢትዮጵያን አንድነት ማዳከም ነው፥፥ ስልታዊ አካሄዳቸው ድግሞ አንዱንብሄረሰብ ከሌላኛው ጋር እርስ በእርስ እንዳይማመኑ በማድረግ በመሃላችን አንድ ሃገራዊ አጀንዳና እሴትእንዳይኖረን ማድረግ ነው፥፥
ለዚህ ማጠናከሪያ የሚሆነው፣የአማራ፣የኦሮሞ እና የትግራይ ብሄረሰቦችን ለምሳሌ ያህል ብንወስድአንድ የኦሮሞ የዘር ሃረግ ያለው ግለሰብ፣አማራ ከሆነ ግለሰብ ጋር አብረው በጓደኝነት፣በጋብቻሊኖሩ የሚችሉበት የግኑኝነታችው መሰረት አንድና አንድ ብቻ እንዲሆን ነው የሚፈለገው፡፡ ያምየትግሬ ጥላቻ ነው።በተቀረው ሁለቱ ግለሰቦች የጋራ የሆነ ሃገራዊ አጀንዳ እና እሴት ቀርጸውስለዲሞክራሲ፣ፍትህ፣ልማትና የሰብአዊ መብት መከበር እንዲሁም ሌሎች ሃገራዊ አጀንዳዎች
እንዲያግባቧቸው ፈጽሞ አይፈለግም።የወዳጅነታቸው መሰረት አንድ ብቻ እንዲሆን ነውየሚፈለገው፣እርሱም የትግሬ ጥላቻ ብቻ ነው። በሌላኛውም መአዘን የትግራይና ኦሮሞ ብሄርተወላጆች የወዳጅነታቸውና ያብሮነታቸው መሰረት መሆን ያለበት፣የአማራ ጥላቻ ብቻ እንዲሆንነው እቅድ ወጥቶለት ከፍተኛ ገንዘብ ተመድቦለት በተግባር ላይ እንዲውል እየተደረገ ያለው።ይህንን ለምሳሌ አነሳን እንጂ ሁሉም የሃገራችን ብሄሮች በተገኘው አጋጣሚና እድል በዚህ መልክበጎሪጥ እንዲተያዩ በማድረግ እንደሰው ወይንም እንደ ኢትዬጵያዊ ማሰብ አቁመን ሳንፈልግበመረጥነው የብሄር ማንነታችን ላይ አትኩረን ስንኩላን እንድንሆን የተሸረበ ሴራ አካል ነው።እዚህጋ በኤርትራ የደህንነትና መረጃ መስሪያቤት ሙሉ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ በመታገዝ
የተስፋዬ ስነ-ጽሁፍ የበኩሉን የማናከስ ሚና በመጫወት ሃገራችንን ወደማያባራ ጦርነትና እልቂትለመክተት የራሱን ሚና እየተጫወተ ይገኛል።ሁለት አመት ለሚቆጠር ጊዜ ቤቴ አስጠግቸው ሲኖር ከሚያደርጋቸው የስልክ ልውውጦች
እንደተረዳሁት ከሆነ በተስፋየ ገብረአብ ስም ይወጡ የነበሩ ጽሁፎች በአብዛኛው ማለት ይቻላልከኤርትራ የመረጃና ደህንነት መስሪያቤት የፕሮፓጋንዳ መልእክቶች እንደነበሩ ህያው ምስክር ነኝ።ይህ ማለት ተስፋየ በጋዜጠኝነት ወይንም በደራሲነት ሽፋን የመረጃ መስሪያቤቱ የፕሮፓጋንዳማስተላለፊያ መሳሪያ በመሆን ለኤርትራን ብሄራዊ ጥቅም የሚውል ስራ ይሰራ የነበረ መሆኑን
አስረጂ ነው።ለምሳሌ ከደህንነት መስሪያቤት የላኩለትን ምንም ለውጥ እንዲደረግበት ሃሳብሲያቀርብ፣እነሱም ሃሳቡን ሳይቀበሉት ሲቀሩ በር ዘግቶ በስልክ ሲጨቃጨቅና ሃሳቡ ሲሸነፍበተደጋጋሚ መስማቴን አስታውሳለሁ።እንደ እኔ እምነት ከሆነ ራሱ የኢትዬጵያ መንግስት እያራመደ ያለው የተንሸዋረረና የከረረ የዘርማንነትን ብቻ ማእከል ያደረግ የፖለቲካ ስርአት፣ከውጪ ሊመጣ ለሚችል እንዲህ አይነትየማጋጫት ወይንም ሃገር የማፍረስ ጣልቃገብነት በር እንደሚከፍት ለመተንበይ አዳጋች አይሆንም።ወደ ነጥቤ ልመለስና ከላይ በጠቀስኩት መሰረት፣አማራን ከተለያዩ የሃገሪቱ ብሄሮች ጋር እንዴትሲያላትምእንደነበረ፣ ዳኛ ወልደሚካኤል መሸሻ ጋር በክፍል አንድ ሪፖርታችን ላይ በሰፊውሄደንበታልና አሁን አልመለስበትም። ከዚህ በታች ደግሞ የትግራይ ብሄር አባል በሆኑ ግለሰቦች ላይማህበራዊ ፤ የስነልቦና የአካል ጥቃት መፈጸሙ፤ የሱ መጽሃፍ ስኬት ውጤት እንደሆነ ለኤርትራየመረጃና ደህንነት መስሪያቤት የቅርብ ተጠሪው ለሆኑት አቶ ዓለም እንዲህ በማለት በጽሁፍየፋክስ መልእክት ረቂቅ (ድራፍት ) ያስተላልፍ እንደነበረ መረዳት እንችላለን፡