Netsanet: ቃለ ምልልስ…. በሊባኖስ ከ4ኛ ፎቅ ከወደቀችው ከእህት ብርቱካን ጋር

Donnerstag, 13. November 2014

ቃለ ምልልስ…. በሊባኖስ ከ4ኛ ፎቅ ከወደቀችው ከእህት ብርቱካን ጋር



ነብዩ ሲራክ ከሳዑዲ አረቢያ
አንዲት እህት ከአራተኛ ፎቅ የመውደቋ መረጃ በሊባኖስ መገናኛ ብዙሃን ሲሰራጭ ከነሰቅጣጭ ተንቀሳቃሽ ምስሉ ነበር ፣ ኢትዮጵያዊቷ እህት ብርቱካን ነበረች ! ለኦማን የአካል ጉዳተኛ ሆና ሃገር ቤት የገባችው በአልማዝ ጉዳት ስንቆሰዝምና ” የረጅ የደጋፊ ያለህ !” በማለት እርዳታ ስናሰባስን ከወደ ሊባኖስ ቤሩት በእህት ብርቱካን ላይ ሆኖ አይተነው የሰቀጠጠን ፣ ሰምተነው ያመመን አደጋ ልባችን ሰበረው: (
birtukan
ብዙም ሳይቆይ በብርቱካን ዙሪያ አወዛጋቢ ሪፖርቶች መቅረብ ጀመሩ ፣ እድሜ ለሥነ ቴክኖሎጅ ወሎ አድሮ ነገሩ እየጠራ መጣ ! በሊባኖስ ከሚገኙ ለሰብዕና ባደሩ ቅን ወዳጆቸ ትብበር የብርቱካንን ጉዳይ በቅረብ በመከታየል ብርቱካን ያለችበት ሁኔታ በአንደበቷ እንድታስረዳን ያደረግነው ጥረት ተሳክቷል ! ከብርቱካን በተጨማሪ ጉዳዩ ሚመለከታቸውን ሃላፊዎችና ሃኪሞች በጉዳቷ ዙሪያ አነጋግሬያቸውም ነበር ። የህክምና ባለሙያዎችና በሊባኖስ የኢትዮጵያ ቆንስል ሃላፊዎች እንዳሉት ከሆነ ብርቱካን የደረሰባት ጉዳት ለከፋ አደጋ ስላልዳረጋት በቀጣይ ቀናት ከሀኪም ቤት በመውጣትና በተዘጋጀላት ማረፊያ ሆና ህክምናና ጉዳይዋን በፍርድ ቤት እንደምትከታተል ያሰባሰብኳቸው መረጃዎች ያስረዳሉ ።
ከዚህ በማስከተል በትናንት ሃሙስ ህዳር 3 ቀን 2007 ከቀትር በኋላና አመበሻሹ ላይ እኔ ከሳወዲ ጅዳ ብርቱካንን ከሊባኖስ ቤሩት ሆስፒታል በመሆን በስልክ ያደረግነውን ቃለ ምልልስ ትከታተሉት ዘንድ ግብዣየ ነው !
ቸር ያሰማን
ነቢዩ ሲራክ
ህዳር 4 ቀን 2007 ዓም

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen