Netsanet: አንድነት በአባላቱ ላይ እስርና ወከባ እየተፈጸመበት መሆኑን አሳወቀ

Freitag, 7. November 2014

አንድነት በአባላቱ ላይ እስርና ወከባ እየተፈጸመበት መሆኑን አሳወቀ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በሚገኙ አባላቱ ላይ መጠነ ሰፊ እስርና ወከባ እየተፈጸመበት መሆኑን አሳወቀ፡፡

ፓርቲው ዛሬ ጥቅምት 28/2007 ዓ.ም በጽ/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳስረዳው ገዥው አካል አንድነትን በሚያዳክም መልኩ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ የፓርቲው አባላትን በማሰር ላይ እንደሚገኝ ገልጹዋል፡፡ 

አንድነት ፓርቲ በወላይታ ያሉ አባላቱ ላይ ከፍተኛ የሆነ ድብደባና ማዋከብ እንደሚፈጸምባቸው ያስታወቀ ሲሆን፣ ከቀናት በፊት በጎንደር፣ በጎጃምና በመቀሌ በሚገኙ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ላይም እስር እየተፈጸመባቸው መሆኑን በመግለጫው አስታውቋል፡፡ መግለጫው አክሎም በእስር ላይ የሚገኙት አባላቱ የት እንዳሉ እስካሁን ማወቅ አለመቻሉን አመልክቷል፡፡ 

‹‹በሀገሪቱ ላሉት ዘርፈ ብዙ ፖለቲካዊ ችግሮች እስርና ወከባ መፍትሔ አይሆንም›› ያለው የአንድነት መግለጫ አሁን ያሉት ችግሮች በዚሁ ከቀጠሉ የህዝቡ ብሶት ወደሌላ አቅጣጫ ሊሄድ እንደሚችልና ያልታሰበ ጥፋት ሊመጣ እንደሚችል ስጋቱን ገልጹዋል፡፡ አንድነት በቀጣይ ለሚያደርገው ትግልም ህዝቡ ከጎኑ እንዲቆም ጥሪውን አቅርቧል፡፡

Photo: አንድነት በአባላቱ ላይ እስርና ወከባ እየተፈጸመበት መሆኑን አሳወቀ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በሚገኙ አባላቱ ላይ መጠነ ሰፊ እስርና ወከባ እየተፈጸመበት መሆኑን አሳወቀ፡፡

ፓርቲው ዛሬ ጥቅምት 28/2007 ዓ.ም በጽ/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳስረዳው ገዥው አካል አንድነትን በሚያዳክም መልኩ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ የፓርቲው አባላትን በማሰር ላይ እንደሚገኝ ገልጹዋል፡፡ 

አንድነት ፓርቲ በወላይታ ያሉ አባላቱ ላይ ከፍተኛ የሆነ ድብደባና ማዋከብ እንደሚፈጸምባቸው ያስታወቀ ሲሆን፣ ከቀናት በፊት በጎንደር፣ በጎጃምና በመቀሌ በሚገኙ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ላይም እስር እየተፈጸመባቸው መሆኑን በመግለጫው አስታውቋል፡፡ መግለጫው አክሎም በእስር ላይ የሚገኙት አባላቱ የት እንዳሉ እስካሁን ማወቅ አለመቻሉን አመልክቷል፡፡ 

‹‹በሀገሪቱ ላሉት ዘርፈ ብዙ ፖለቲካዊ ችግሮች እስርና ወከባ መፍትሔ አይሆንም›› ያለው የአንድነት መግለጫ አሁን ያሉት ችግሮች በዚሁ ከቀጠሉ የህዝቡ ብሶት ወደሌላ አቅጣጫ ሊሄድ እንደሚችልና ያልታሰበ ጥፋት ሊመጣ እንደሚችል ስጋቱን ገልጹዋል፡፡ አንድነት በቀጣይ ለሚያደርገው ትግልም ህዝቡ ከጎኑ እንዲቆም ጥሪውን አቅርቧል፡፡

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen