Netsanet: የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ከአውሮፓ ህብረት ልዑካን ጋር ተወያዩ

Donnerstag, 27. November 2014

የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ከአውሮፓ ህብረት ልዑካን ጋር ተወያዩ

የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ትላንት ህዳር 16 ቀን ከአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያ ልዑክ ኃላፊ ሻንታል ሄበርረሼት እና ከልዑኩ ተቀዳሚ ቆንስል እንዲሁም የፖለቲካ፣ የፕሬስና የኢንፎረሜሽን ኃላፊ ከሆኑት ሳነዲ ዋዴ ኦቤ ጋር በ2007 ምርጫ ዙሪያ መወያየታቸውን ከፓርቲው ህዝብ ግንኙነት ለፍኖተ ነፃነት የደረሰው መረጃ አመላከተ፡፡
ህብረቱ ባደረገላቸው ጥሪ መሰረት ውይይቱን ያደረጉት የአንድነት አመራሮች “እኛ በሀገራችን ለውጥ ለማምጣት የምንታገለው ሙሉ ለሙሉ ዕምነታችንን የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ጥለን ነው፡፡” ካሉ በኋላ የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ጉዳይ አሳስቦት ያቀረበውን ጥሪ አክብረው መምጣታቸውን ለህብረቱ ልዑካን አስረድተዋል፡፡ ምርጫ 2007ን በሚመለከት “አንድነት በምርጫ ለመሳተፍ ወስኗል፤ የምርጫውም ነፃ፣ ፍትሀዊና ተአማኒ እንዲሆን ይታገላል፡፡” በማለት የአንድነትን አቋም አስረድተዋል፡፡ አክለውም “ከምርጫ መውጣት ቀዳሚ ምርጫችን ባይሆንም፤ ምርጫው ለውጥ የማያመጣ ሆኖ በተገኘበት በየትኛውም ጊዜ ከምርጫው እንወጣለን” በማለት ተናግረዋል፡፡
አመራሮቹ አበክረው ለልዑካኑ ያስረዱት በየትኛውም ሁኔታ ኢህአዴግ አይን ያወጣ የምርጫ ዝርፊያ ቢያደርግ አንድነት በዝምታ እንደማይመለከት ማስረዳታቸውን የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ለፍኖተ ነፃነት አስታውቋል፡፡
Millions of voices for freedom – UDJ
UDJ


Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen