Netsanet: Oktober 2014

Freitag, 31. Oktober 2014

እነ የሽዋስን ጨምሮ 10 ተጠርጣሪዎች በይፋ ክስ ተመሰረተባቸው



• አብርሃ ደስታ የሁለት ድርጅቶች አባል ነው የሚል ክስ ተመስርቶበታል

• ወደ አዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እንዲዘዋወሩ ታዟል

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

በልደታ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ምድብ ወንጀል ችሎት ዛሬ ጥቅምት 21/2007 ዓ.ም ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ በተሰየመው ችሎት 10 ተከሳሾች በፌደራል አቃቢ ህግ በይፋ ክስ ተመሰረተባቸው፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ከ100 ገጽ በላይ የክስ ቻርጅ የተነበበላቸው ሲሆን ከክስ ቻርጁ ጋር ከ300 ገጽ በላይ የምርመራ ሰነድ ቀርቦባቸዋል፡፡ 

የክሱ መዝገብ የተከፈተው ዘላለም ወርቃገኘሁ በተባለውና ‹‹የግንቦት 7 አመራር ነው፡፡›› ተብሎ ክስ በተመሰረተበት ግለሰብ ሲሆን በዚህ የክስ መዝገብ የተካተቱትም፡-

1ኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ
2ኛ ተከሳሽ ሀብታሙ አያሌው
3ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ሺበሺ
4ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታ
5ኛ ተከሳሽ የሽዋስ አሰፋ
6ኛ ተከሳሽ ዮናታን ወልዴ
7ኛ ተከሳሽ አብርሃም ሰለሞን
8ኛ ተከሳሽ ሰለሞን ግርማ
9ኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ደጉ
10ኛ ተከሳሽ ተስፋዬ ተፈሪ ናቸው

ለሁሉም ተከሳሾች ከዛሬ በፊት ክስ እንዳልደረሳቸውና ዛሬ ፍርድ ቤት ውስጥ እንደተሰጣቸው ታውቋል፡፡ በችሎቱ 6ኛ ተከሳሽ ከሆነው ዮናታን ወልዴ በስተቀር ሁሉም ያለ ጠበቃ የቀረቡ ሲሆን ጠበቃዎቹ ያልቀረቡበት ምክንያትም ጠበቆቹ ደምበኞቻቸው የሚቀርቡበት ቦታና ጊዜ ስላልተነገራቸው እንዲሁም ቀደም ብለው እንዳይገናኙ በመደረጋቸው መሆኑን አቶ ኃብታሙ አያሌው ችሎቱ ላይ ተናግሯል፡፡ 

ከሳሹ የፌደራል አቃቢ ህግ በ1996 የወጣው የወንጀል ህግ እና የጸረ ሽብር ህግ ጠቅሶ ክስ ያቀረበ ሲሆን ክሶቹ በሁለት ዋና ዋና ጭብጦች ቀርበዋል፡፡ የመጀመሪያው ጭብጥ ‹‹ከሽብርተኛ ቡድኖች ጋር በጋራ በመስራት›› የሚል ሲሆን ‹‹ህገ መንግስቱንና ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ፣ የመንግስትን መሰረተ ልማት በማፈራረስ፣ ህዝብን ለአመጸ በማነሳሳት መንግስትን መለወጥ አላማው አድርጎ ከሚሰራውና ራሱን ግንቦት 7 ብሎ ከሚጠራው ቡድን ጋር አባል በመሆንና በወንጀል ድርጊቶች በመሳተፍ›› በሚል ቀርቧል፡፡ 

ሁለተኛው የክስ ጭብጥ ‹‹የሽብር ቡድን አመራር በመሆን›› የሚል ሲሆን በተለይም የአንደኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ ‹‹የሽብር ቡድኑ አመራር በመሆንና አባል በመመልመል›› በሚል የክስ ጭብጥ ቀርቦበታልል፡፡

ከ2-5ኛ የክስ መዝገብ የሚገኙት ማለትም ሀብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሽ፣ አብርሃ ደስታና የሸዋስ አሰፋ ‹‹ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲን ከለላ በማድረግ ግንቦት 7 የተባለውን የሽብር ቡድን አላማ ለማሳካት ተንቀሳቅሰዋል፡፡ ፋሲል የኔ ዓለምና ሌሎች የሽብር ቡድኑ አባላት ጋር በስልክ በመነጋገርና በማህበራዊ ድህረ ገጸ የተለያዩ መልዕክቶችን ተለዋውጠዋል›› የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡ አብርሃ ደስታ ከግንቦት 7 በተጨማሪ ‹‹ደምኢት የተባለ ቡድን አባል ነው፡፡›› የሚል ክስ ቀርቦበታል፡፡ 

በስተመጨረሻም ፍርድ ቤቱ ሁለት ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ አንደኛው ረቡዕ ጥቅምት 26/2007 ዓ.ም 3 ሰዓት ተከሳሾቹ ዋስትና ይሰጣቸው አይሰጣቸው በሚለው ጉዳይ ላይ ፍርድ ቤቱ ከተከሳሾቹ ጠበቆች ጋር ተማክሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሏል፡፡ በሁለተኛነት ተጠርጣሪዎቹ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት ቀደም ሲል ለአራት ወራት ወደቆዩበት ማዕከላዊ እስር ቤት እንዳይመለሱ ፍርድ ቤቱን ስለጠየቁ ፍርድ ቤቱ በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት (3ኛ) እንዲቆዩ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡

ተከሳሾቹ ትናንት ጥቅምት 20/2007 ዓ.ም አራዳ ምድብ ችሎት ይቀርባሉ ተብሎ የነበር ቢሆንም ሳይቀርቡ ቀርተዋል፡፡ በተመሳሳይ ዛሬ ጥቅምት 21/2007 ዓ.ም ጠዋት ወደ ልደታ ፍርድ ቤት ተወስደው የነበረ ቢሆንም እንደገና ወደማዕከላዊ ተመልሰው ከሰዓት እንዲቀርቡ ተደርገዋል፡፡

Donnerstag, 30. Oktober 2014

አንድነት በፖለቲካ እስረኞች ላይ እየተፈጸመ ያለውን ኢ-ሰብአዊ ድርጊት አወገዘ



• ‹‹ማዕከላዊ የታሰሩት የፓርቲው አመራሮች መጸዳጃ ቤት ተከልክለዋል››

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ጥቅምት 20/2007 ዓ.ም በጽ/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በፖለቲካ እስረኞች ላይ እየተፈጸመ ያለውን ኢ-ሰአብአዊ ድርጊት አወገዘ፡፡ ‹‹የኢህአዴግ አገዛዝ ከጊዜ ወደ ጊዜ ሰብአዊ መብት በመጣስና ዜጎችን በማሰቃየት ወደር የሌለው ሆኗል›› ያለው መግለጫው፣ ስርዓቱ ለስልጣኑ ያሰጉኛል ያላቸውን የፖለቲካ አመራሮች፣ ጦማሪያንና ጋዜጠኞችን ህገ-ወጥ በሆነ መንገድ ክስ በመመስረት ማሰሩ ሳያንስ እነዚህን ዜጎች ሰብአዊ ክብራቸውን በመድፈር ኢ-ሰብአዊ ድርጊት እየፈጸመ ይገኛል ብሏል፡፡

መግለጫው አክሎም የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት አቶ ሀብታሙ አያሌውና ም/ድርጅት ጉዳይ ኃላፊው አቶ ዳንኤል ሺበሺ በማዕከላዊ እስር ቤት አንድ ሰው ይፈጽመዋል ተብሎ የማይጠበቅ ኢሰብአዊ ድርጊት እየተፈጸመባቸው ነው ሲል ስርዓቱን ወቅሷል፡፡ 

‹‹ሀብታሙ አያሌው ለአንድ ሳምንት የታሰረበት ክፍል ውስጥ እንዲጸዳዳ በማድረግና ለሶስት ቀን ጨለማ ክፍል ውስጥ በማሰር የበቀል በትራቸውን እያሳረፉበት እንደሆነ አውቀናል፡፡ ....አቶ ዳንኤል ሺበሺ ከከፍተኛ ዛቻና ስድብ በተጨማሪ የታፈነ ክፍል ውስጥ እንዲቀመጥ በመደረጉ ለተቅማጥና ለሌሎች በሽታዎች መዳረጉ፣ ወደ መጸዳጃ ቤት እንዳይሄድ›› መከልከሉን በመግለጽ ማዕከላዊ ታስረው የሚገኙ የአንድነት አመራሮች እየደረሰባቸው ያለውን በደል አስረድቷል፡፡ 

አዲሱ የአንድነት ፕሬዝዳንት አቶ በላይ ፍቃዱ ይህ በእስረኞቹ ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ በጥላቻ የሚፈጸምና ትውልዱ ሊወርሰው የማይገባ ነው ብለዋል፡፡ ‹‹ይህን የበደል ዘመን ለማሳጠር እንዲቻል ህዝቡ በቁጭት ለለውጥ እንዲነሳ›› ሲልም ፓርቲው ጥሪ አቅርቧል፡፡

“ተፌ!”

tefera w
ታጋይ፣ ከንቲባ፣ መከላከያ ሚ/ር፣ ምክትል ጠ/ሚ/ር፣ አቅም ገንቢ፣ አቅም ተገንቢ … ከዚህ ሁሉ አልፈው አሁን አቅማቸው ተገንብቶ የስፔስ (ሕዋ) ሳይንስ “አቅም ግንባታ” ለመሆን የበቁት ጡረተኛው ተፈራ ዋልዋ “የኢትዮጵያን የሕዋ (ስፔስ) ሳይንስ ሶሳይቲን” ገንብተው በሪፖርተር በኩል ብቅ ብለዋል፡፡
“አቅም ገንቢ ሚ/ር” በነበሩበት ወቅት “ሂድና ከአባዱላ ተማር የአንተ አቅም ግንባታ እንኳን አቅም ሊገነባ ያለውንም ሊያስቀጥል አልቻለም” ተብለው በአቶ መለስ የተገመገሙት አቶ ተፈራ አቅማቸው ተገንብቶ ለስፔስ መድረሱን “ባለራዕዩ መሪ” ሳያዩና ሪፖርተር ላይ ሳያነቡ መሰዋታቸው አቶ ተፈራን እጀ ሰባራ አድርጓቸዋል፡፡
የአላሙዲን “ወዳጅ” ሪፖርተር የአቶ ተፈራን አንደበት ገድቦት ነው እንጂ ተፈራ “ሼኸ፣ ዶ/ር፣ አቅም አስገንቢ … አላሙዲንን” ባነሱበት አንደበታቸው በግል ጄታቸው ገስግሰን ሁለተኛውን ሙት ዓመት “ነፍስ ይማር” በማለት አክብረን “በባለራዕዩ መሪያችን ስም በዚያውም ዛፍ ተክለን እና ፓርክ አቋቁመን እንዲሁም አንድ ፕላኔት በስማቸው አሰይመን” ተመልሰናል እንዳሉ ይገመታል – የሕዋው “አቅም ገንቢ” ተፌ! (ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®)

Mittwoch, 29. Oktober 2014

ተመስገን የእናቱ፣ የሕዝብ ልጅ!

ከሰማያዊ ፓርቲ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የተሰጠ መግለጫ




ሰማያዊ ፓርቲ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ በሕብረተሰቡ ዘንድ የሚነሱ በርካታ መሰረታዊና ወቅታዊ ጥያቄዎችን ጥያቄዎቹ አድርጎ ሲንቀሳቀስ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ ባለፉት ሁለት አመታት ውስጥም ፓርቲያችን በተለያየ መልኩ የተቻለውን ሁሉ በማድረግ እየታገለ በመንግስት ላይ ጫና ለማሳደርና ችግሮች መፍትሔ የሚያገኙበት አቅጣጫ ሲያመለክት ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ የሀገራችን አስተዳደራዊና ፖለቲካዊ ችግሮች ከግዜ ወደ ግዜ እየተባባሱና እየከፉ የመምጣታቸውን ያህል ገዢው ፓርቲ ቆም ብሎ ከማሰብ ይልቅ ወደ ማይወጣው አዘቅት ውስጥ ሀገሪቷን ጭምር እያንደረደራት ይገኛል፡፡ ይህም አልበቃ ብሎ ከዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ሂደት ፍፁም በማይጣጣም መለኩ ዜጎችን ለአንድ ሀሳብ ብቻ እንዲገዙ አስገዳጅ መንገዶችን ጭምር በመጠቀም አፋኛ መዋቅሩን በማናለብኝነት እያስፋፋ ይገኛል፡፡ ይህም አልበቃ ብሎ ለማናቸውም አስተዳደራዊም ይሁን ፖለቲካዊ ጥያቄዎች ሀይልን በመጠቀም ለመደፍጠጥና ለማጥፋት ቆርጦ በመነሳት ፍፁም አምባገነንነቱን ገፍቶበት የበርካቶች ህይወት ተቀጥፏል፡፡

ለዚሁ እንደማሳያም:-

ካለፈው ዓመት የክረምት ወራት መጨረሻ አንስቶ እስከ አሁን ድረስ ዜጎች በተለያየ ዘርፍ በመከፋፈል የግዳጅ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡ በዚህ አስገዳጅ ስልጠናም የምርጫ ቅስቀሳ በሚመስል መልኩ ከህወሓት/ኢህአዴግ ውጪ አማራጭ እንደሌለ ከመስበክ ባለፈም ማናቸውም የተለየ ሀሳብ የሚያራምዱ የህብረተሰብ ክፍሎችን፣ ድርጅቶችንና ግለሰቦችን ፍፁም ስነ ምግባር በጎደለው መልኩ የጥላቻ ዘመቻ በማካሄድ የሃሳብ ልዩነትን የማስተናገድ ፍላጎቱ ሙሉ ለሙሉ የተዳፈነ መሆኑን አሳይቷል፡፡ ለዚህ ህገወጥ እንቅስቃሴ እና ዓላማም ወደ 1 ቢሊየን የሚጠጋ የህዝብ ሃብት ባክኗል፤ እየባከነም ይገኛል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ እነዚህን ስልጠናዎች እጅግ በቅርበት ሲከታተላቸው የቆየ ሲሆን ከጅማሬውም ተቃውሞውን በይፋ ማሰማቱ ይታወሳል፡፡ 

በሌላ በኩል የሕብረተሰብ የመረጃ ክፍተት ለመሙላት እና ካለበት የፖለቲካ ድብርት ለማውጣትና ለማነቃቃት ሕገ መንግስቱን መሰረት አድርገው ሃሳባቸውን በነፃነት የገለፁ ጋዜጠኞችና የህትመት ውጤቶቻቸው ከገበያ እንዲወጡ በማተሚያ ቤቶች በኩል አስተዳደራዊ ሴራ መስራቱ ሳያንስ ሕገ መንግስቱን በሚፃረር መልኩ በሕትመት ሚዲያዎቹ ባለቤቶች፣ አዘጋጆች፣ በጋዜጠኞቹና ሰራተኞቻቸው ላይ በማስፈራራት ስነ ልቦናዊ ጫና በማሳደር በርካቶች ለስደት ሲዳረጉ ጥቂቶች ደግሞ ለእስር ተዳርገዋል፡፡ ገዢው ፓርቲ ባንድ በኩል ሀሳቡን ለመጫን የግዳጅ ስልጠና እየሰጠ በሌላ በኩል ደግሞ የተለየ ሀሳብን እንዲሁም የህዝብ ብሶትን የሚያሰሙ ጋዜጠኞች ላይ የማሳደድ ዘመቻ መክፈቱ የስርዓቱን መበስበስ እና አፋኝ አምባገነንነትን ብቸኛ አማራጭ አድርጎ መቀጠል መምረጡን ግልጽ አመላካች ነው፡፡

ከላይ ከሰፈሩት ሁነቶች እጅግ የከፋውና እየተባባሰ የመጣው ሌላው ከፍተኛ አደጋ ያዘለ ችግር ደግሞ፤ አስተዳደራዊ እና ፖለቲካዊ ጥያቄ እያነሱ ያሉ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በሀይል ለመገዛት ቆርጦ መነሳቱ ነው፡፡ ባሳለፍናቸው ሁለት ወራት ብቻ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ዜጎች በመንግስት ሀይሎች ተገድለዋል - ቆስለዋል - ተሰደዋል፡፡ በኦጋዴን መንግስትን የተቃወሙ ዜጎች ወደ ግጭት እንዲገቡ በሚገፋፋ መልኩ ጥያቄዎቻቸውን በመግፋት በርካታ ዜጎች በመንግስት ሀይሎች ህይወታቸው መቀጠፉ ሳያንስ ሬሳቸው እንኳን ክብር በሌለው ሁኔታ መሬት ለመሬት እየተጓተተ ባደባባይ ሰብአዊ መብት ሙሉ ለሙሉ ተጥሷል፡፡ በጋምቤላም በተመሰሳይ መልኩ የህወሓት ሰዎች መሬት በሕገ-ወጥ መንገድ መቀራመታቸውን የተቃወሙ ዜጎች ወደ ግጭት የተገፉበት እና በርካታ የሰው ህይወት የተቀጠፈበት ሁነት እጅግ አሳዛኝ እና መንግስት የተያያዘው መንገድ ወደ ከፋ ሁኔታ ሀገሪቷን እየወሰዳት ለመሆኑ ማረጋገጫ ነው፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ ከላይ የተዘረዘሩትንና ከዚህ ያልተጠቀሱትን በተለያየ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚፈፀሙትን በርካታ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እና አስጊ ሁኔታዎች በቅርብ እየተከታተለ ይገኛል፡፡ በተደጋጋሚ እንደተገለፀውም አሁን ካለንበት ሀገራዊ አዘቅት እና አደጋ መውጫው መፍትሔ በቆራጥነት ሀገርን የማዳን ትግል ማካሄድ እንደሆነ ፓርቲያችን በሚገባ ይገነዘባል - ያምናል፡፡ በስልጠናዎቹ ወቅትም ተማሪዎች እና በርካታ የሕብረተሰብ ክፍሎች በብዛት ሲያነሱት የነበረውን ጥያቄና ስሞታም ከግንዛቤ በማሰገባት ጥያቄዎቹ ምላሽ የሚያገኙበትን የትግል አቅጣጫ በተጠናከረና በተጠና መልኩ አሳታፊ አድርጎ ከግብ ለማድረስ በሙሉ ቁርጠኝነት እና አቋም ላይ እንደሚገኝ ያረጋግጣል፡፡

በመሆኑም የሀገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታ ከግምት በማሰስገባት መላው የሀገሪቱ ህዝብ፣ በውጪ የምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ለሀገር ተቆርቋሪ ተቋማት እንዲሁም በገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ስር ሆናችሁ ለውጥን የምትሹ ወገኖች ሀገራችንን ወደ አደጋ እየወሰዳት ያለውን አፋኝ ስርዓት በቻላችሁት ሁሉ በመቃወምና ከስርዓቱ ጋር ባለመተባበር በብሔራዊ ደረጃ የሚደረገው ትግል አካል እንድትሆኑ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ 

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

ጥቅምት 18 2007 ዓ.ም

ሰማያዊ ፓርቲ 

አዲስ አበባ

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የእስር ቅጣቱን በመቃወም ይግባኝ ሊጠየቅ ነው

በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ህዝብን ለአመፅ በማነሳሳትና ሀሰተኛ መረጃን በመስጠት በሚል ዐቃቤ ሕግ ክስ መስርቶበት የ3 ዓመት ፅኑ እስራት የተፈረደበት በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ይግባኝ እንደሚጠይቁ ጠበቃው አቶ አመሀ መኮንን አስታወቁ። ጠበቃው አክለውም፤ ውጤቱ ምንም ይሁን ምን ሕጉ እስከፈቀደው ድረስ ማንኛውንም መድረክ አሟጠን እንጠቀማለን ሲሉ ተናግረዋል። ይግባኝ እንደሚጠይቁ ጠቁመው ያም ሆኖ የተለየ ውጤት ካልተገኘ እስከሰበር ችሎት እንደርሳለን ብለዋል።
በተከሳሹ ላይ ፍርድ ቤቱ የጥፋተኝነት ብይን ከሰጠ በኋላ ስለምን የቅጣት ማቅለያ አላቀረባችሁም ተብሎ ከሰንደቅ ጋዜጣ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱም፤ በመርህ ደረጃ ጥፋተኛ መባል አልነበረበትም፤ አሁን ጉዳዩ ብዙ ዓመት የመታሰርና ትንሽ ዓመት የመታሰር ብቻ ሳይሆን በዋናነት ለቅጣት ቅነሳ መከራከሪያችን ለህግ ጥፋቱን የማመን ምልክት ስላለው አልፈለግንም።
Temesghen Desalegn (CPJ)cropped
አመፅን ለመቀስቀስ በመሰናዳት ወንጀል ተሳትፎ፤ ሕገ-መንግስቱንና ህገመንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ የሚያነሳሱ ፅሁፎችን በቀድሞዋ ፍትህ ጋዜጣ ላይ ሲያሰፍር ነበር በሚል የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ ክስ የመሰረተበት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ጥፋተኛ የተባለበት ግዙፍ ያልሆነ የማሰናዳት ወንጀል ሥር በ3 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ሲል ፍርድ ቤት ባሳለፍነው ሰኞ ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም የቅጣት ውሳኔውን አስተላልፏል።
ዐቃቤ ሕግ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ሶስት ክሶችን በጋዜጠኛው ላይ አቅርቦ በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች አስረድቷል። ተከሳሹም ከተከሰሰባቸው ወንጀሎች ነፃ ያወጡኛል ያላቸውን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች ለፍርድ ቤቱ አቅርቦ የተከራከረ ቢሆንም፤ ችሎቱ የግራ ቀኙን መረጃ መርምሮ ጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም ጥፋተኛ ነህ ብሎት እንደነበር ይታወሳል።
በዐቃቤ ሕግ የክስ ዝርዝር የተጠቀሱት ፍሬ ሀሳቦች መካከል በአንደኛው ክስ ሥር “ሞትን የማይፈሩ ወጣቶች” በሚል ርዕስ ነሐሴ 23 ቀን 2003 ዓ.ም ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በፃፈው ሀተታ ውስጥ ወጣቶች ለአብዮትና ለለውጥ እንዲነሳሱ በማድረግ፤ በአረቡ አለም ወጣቶች የነበራቸውን ሚና በመጥቀስ አሁን ያለውን ስርዓት ለመቀየር ወጣቶች ለአመፅ እንዲነሳሱ አድርጓል የሚል ነው።
በ2ኛ ክስ ስር የተዘረዘረው ሀሳብ ደግሞ “የሁለተኛ ዜግነት ህይወት በኢትዮጵያ እስከመቼ?” በሚል ርዕስ ሐምሌ 22 ቀን 2003 ዓ.ም በፍትህ ጋዜጣ ባወጣው ሀተታ ስር መንግስት በተለያዩ ክልሎች የጅምላ ጭፍጨፋ ፈፅሟል በማለት የአገሪቱን መንግስት ስም በማጥፋትና በሀሰት ወንጅሏል የሚል ክስ ተመስርቶበታል።
ዐቃቤ ሕግ 3ኛ ክስ አድርጎ ያቀረበው ደግሞ በመጋቢት 7 ቀን 2004 ዓ.ም በታተመችው ፍትህ ጋዜጣ ላይ “ሲኖዶሱና መጅሊሱ የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ማጥመቂያ” ሲል ባሰፈረው ፅሁፍ መንግስት የሃይማኖት ተቋማቱን ለፖለቲካዊ ዓላማ እየተጠቀመባቸው ስለመሆኑ በማተት የህዝብን እምነት እንዲሸረሸር አድርጓል ሲል ይከሰዋል።
ተከሳሹ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧቸው በነበሩ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች አማካኝነት በጥቅሉ፤ የጋዜጠኝነት ተግባሩን እየተወጣ በመሆኑንና በዚህም ህገ መንግስቱ የሰጠውን ኀሰብን የመግለፅ ነፃነት ተጠቅሞ ሥራውን ማከናወኑን ባቀረባቸው የመከላከያ ምስክሮች ጭምር አስረድቷል።
ሆኖም የግራ ቀኙን ክርክር ሲመረምር የቆየው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም ጥፋተኛ ማለቱን ተከትሎ ባሳለፍነው ሰኞ የቅጣት ውሳኔውን አስተላልፏል። በዚህም የውሳኔ ንባብ ወቅት ፍርድ ቤቱ እንዳለው፤ ምንም እንኳን ተከሳሹ ጥፋተኛ ቢባልም የቀረቡበት 3 ክሶች በአንድ ሃሳብ ሊጠየቅ የሚገባው ነው በሚል፤ በወንጀል ህጉ የመገፋፋትና ግዙፍ ያልሆነ የማሰናዳት ተግባር ወንጀል ብቻ ይቀጣ ማለቱን ተከትሎ ምንም አይነት የቅጣት ማቅለያ ባላቀረበው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ የ3 ዓመት ፅኑ እስራት ፈርዶበታል።
በተያያዘም አሳታሚው ማስተዋል የህትመትና ማስታወቂያ ኃ/የተ/የግ ማህበር ላይ ዐቃቤ ሕግ አቅርቦት የነበረው የንብረት ይወርስልኝ ጥያቄን ፍርድ ቤቱ ወደጎን በመተው የ10ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ጥሎበታል።
ምንጭ፦ ሰንደቅ ጋዜጣ

ልማት ካለ ነፃነትና ፍትሕ ፋይዳ የለውም – ክፍል ሁለት

ከ ይኩኖ መስፍን
ቦስተን ሰሜን አሜሪካ

መልካም አስተዳደርና የፓለቲካ ምሕዳር

Justiceየሞያ ነፃነት በተገደበባት” ነፃ የፍትሕ” የዳኝነትና የዴሞክራሲ ተቋማት በሌሉበት! የሕግ የበላይነትና ተጠያቂነት በጠፋበት” በጋብቻና በዝምድና የተሳሰረ አንድ ፈላጭ ቆራጭ ፓርቲ የሀገሪትዋን ሁለንትናዊ ሰብኣዊ ማተሪያላዊና አእምራዊ ሀብት ተቆጣጥሮ ራሱ ሕግ አውጪ! ራሱ ሕግ ተርጓሚ! ራሱ ሕግ ፈፃሚና አስፈፃሚ በሆነበት” ባጠቃላይ ፍርሃት! ዱላ! ድሕነትንና ረሃብን እንደ የፓለቲካ መሳሪያ አድርጎ በመጠቀም ለያይቶና አደንቁሮ የሚገዛ አምባ ገነን መንግስት ባለበት ድሃ ሀገር የሚኖር ሕብረተሰብ ምን ያህል ለአፈና! አድልዎ! ጭቆና እና ዝርፊያ የተጋለጠ እንደሆነ መገመቱ አያዳግትም::
አብዛኞቻችን ከደርግ ውድቀት በሗላ በእርስ በርስ ጦርነት የደቀቀውን ሀገርና ህዝብ እፎይታ አግኝቶ በይቅርታ መንፈስ ሁላችንም በአንዲት እናት ሀገር ጥላ ስር ታቅፈን! ተቻችለን! ተፋቅረንና ተከባብረን በጋራ የምንገነባት አንዲት ዲሞክራሲያዊት እናት ሀገር ትኖራለች የሚል ነበር ተስፋችንና ምኞታችን፡፡ የህወሓት/ኢሕአዴግ ስርዓትም ካለፉት መንግስታት ተምሮ በሀገራችን ቢያንስ የዴሞክራሲያዊ ስርዓት መሰረት ይጥል ይሆናል የሚል በጎ እምነትና ግምት ነበረን፡፡ በሂደት የሚታዩ አንዳንድ የልማት እንቅስቃሴዎችም እንደ መልካም ጅምር በመውሰድ” ነገር ግን በመልካም አስተዳድር! በፓለቲካዊ ምሕዳር! በምርጫና በሀገራችን ድሕንነት ዙሪያ የሚታዩ መሰረታዊ ችግሮች ዛሬ ነገ ይታረማሉ በማለት ዜጎች በተደራጀም ሆነ በተናጠል ላለፉት አሰርቱ ዓመታት ብሶታቸውን ሲያሰሙና አቤት ሲሉ ቆይቷል:: ይሁን እንጂ ሰሚ ጆሮ አልተገኘም::
ህወሓት/ኢሕአዴግ በትረ ስልጣኑን ከጨበጠና ካደላደለ በሗላ እሱም በተራው የጥፋት መንገድ በመከተል የህዝቡን የለውጥ ጥማትና የፍትሕ ተስፋ አጨልሞታል:: ትናንት በደርግ ቀይ ሽብር የተቀጣውና የደነገጠው ሕብረተሰብ ለውጥ ይመጣል ብሎ ሲጠብቅ ዛሬም በፀረ ሽብር አዋጅ እንዲገዛ! እንዲሸማቀቅና እንዲሰጋ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ትላንት ለዴሞክራሲና ለሰው ልጅ ነፃነት ሲባል የተከፈለውን ኩቡር የህይወት መስዋእትነት ተረስቶ ዛሬ የህወሓት/ኢሕአዴግ የአንድ ድርጅት አባልና ታማኝ ካልሆንክ በስተቀር የመደራጀት! የመናገር! የመስራት! ባጠቃላይ እንደ አንድ ዜጋ በህይወት የመኖር ነፃነትህን ተነጥቆ ለፍልሰት! ለእስር! አሊያም ለሞት ትዳረጋለህ፡፡ የተከበረና አኩሪ ባህል ያለው ጨዋ ህዝብ ዛሬ ወዳጅ” ማሀል ሰፋሪና ጠላት ብሎው በመፈረጅና በመከፋፈል አንዱ አንዱን የገዛ ወንድሙን በጎሪጥና በጥርጣሬ ዓይን እንዲተያዩ እየተደረገ ይገኛል፡፡ አንድ ዜጋ የተለየ ሃሳብ ወይም የሌላ ድርጅት አባል በመሆኑ ብቻ እንደ ነውርና እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ በህዝብ ፊት የተለያዩ አስነዋሪ የማስፈራሪያ ዘዴዎችን እየተጠቀሙ በተወለባት ምድር ሓፍረት እንዲሰማው” ከሕብረተሰቡ እንዲነጠልና እንዲሰጋ ከማድረግ ባሻገር ይባስ ብለው ሲሞት እንዳንቀበረው” እሳት እንዳናስጭረው” የሚል የወረደ ማሕበራዊ ውግዘትና ተፅእኖ እንዲፈፀምባቸዉ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ሌሎችም በዚሁ ፅሑፍ ለመጥቀሱ የሚከብድና የሚዘገንን ድርጊት በተለይም ለአርባ ዓመታት ያህል በአንድ ሞኖፓላዊ ድርጅት ህወሓት ተይዞ የሚገኘው የትግራይ ህዝብ ታሪኩንና መለያ ባህሉን (Indeginous culture) በጉልበት በማፈራረስ እና በመበረዝ በምትኩ የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ቅይጥና የተዳቀለ የካድሬዎች ግራ አስተሳሰብ እንዲተካ በማድረግ እርስ በርሱ እያናከሱ በላዩ ላይ ይህ ነው የማይባል ግፍ እየተፈፀመበት ይገኛል፡፡
ልብ በሉ!! ተወልደን ባደግንበትና እትብታችንን በተቀበረበት መንደር ዛሬ ይህ ዓይነት የስነ ልቦና ጦርነት በያንዳንዳችን ቤት ቢደርስብን ምን ይሰማናል? ትላንት ጫካ ገብተው ስለ ነፃነት ሲዘምሩ! በሰማእታት ስም ሲምሉ! ለህዝብ ሲያስተምሩና በሽዎች የሚቆጠሩ ለጋ ወጣቶችን ቀብረው ስልጣን ላይ የወጡ የፓለቲካ መሪዎቹ ያ ሁሉ ለህዝብ የገቡበትን ቃል ረስተው ዛሬ ብዙሃኑን ለልመናና ለስቃይ ዳርገው እነሱ በሙሱና ሲጨማለቁ! ከሕግ በላይ በመሆን በህዝብ መብት ላይ ሲቀልዱ! በገዛ ወገናቸው ላይ ሲጨክኑና ሲያሰቃዩ በውል ስናይ እውነት ምን ይሰማናል? የህወሓት/ኢሕአዴግ ስርዓት የሁሉም ዜጋ ሕገ መንግስታዊ መብትና ደሕንነት ጠብቆ በእኩል ከማስተዳደር! ከመጠበቅና እንደ መንግስት ከመስራት ይልቅ ራሱን ታች ወርዶ ከሕብረተሰቡ ወይም ተቃዋሚ ናቸው ከሚላቸው ሰዎች ጋር የሚናቆርና የሚያውክ ከሆነ ህዝቡ ለማን አቤት ይበል?
ዛሬ የምንኖረው በ21ኛው ክፍለ ዘመን የሰው ልጅ ከአካባቢው የእይታ አድማስ አልፎ ዓለምን መዳሰስ በጀመረበት” በተለይም ዴሞክራሲ” የሕግ የበላይነት” መልካም አስተዳደር” ሰብኣዊ መብትና የነፃነት ጥያቄዎች ድንበር አልባ (ዩኒቨርሳል) የሰብኣዊ ፍጡር እሴቶች በሆኑበት በሰለጠነ ዘመን ሆኖ ሳለ ነገር ግን ህዝባችን ብሎም ወጣቱ ትውልድ አደንቁረህ ግዛ በሚል የህወሓት/ኢሕአዴግ ያረጀ ያፈጀ ፈሊጥ ሳይወድ በግድ እንደ ወባ ክትባት የአንድ ፓለቲካዊ ቡድን ጠባብና ሞኖፓላዊ አስተሳሰብ ተሸብቦ እንዲያድግ የሚገደድበት ምክንያት ምንድን ነው? የሚሉ ጥያቄዎች ለሰሚ ብቻ ሳይሆን ለተመልካችም ግራ የሚያጋቡ የዘመናችን የሀገራችን እንቆቁልሽ ናቸው፡፡
የተከበራችሁ ውድ ኢትዮ}ያውያን ወገኖቼ ሆይ!!
በሀገር ቤት ቆይታዬ እስካሁን ድረስ በአእምሮዬ ውስጥ እየተመላለሱ የሚረብሹኝ ብዙ ነገሮችን ታዝቤያለሁ፡፡ ሁሉም ያየሁትንና የሰማሁትን የህዝቡን እሮሮ በዚህ አጭር ፅሑፍ ዘርዝሮ ለማቅረብ የሚከብድ ቢሆንም ከአዲስ አበባ ወደ ሰሜኑ ክፍለ ሀገራችን በተለይም አርባ ዓመታት ያህል በአንድ ነፃ አውጪ ነኝ የሚል ፓለቲካዊ ድርጅት በህወሓት ሞኖፓላዊ አገዛዝ ወድቃ በአካባቢው ነዋሪዎች አጠራር የፓሊስ ግዛት (police state) እየተባለ የሚነገርላት ትግራይ ለወራት ያህል በቆየሁበት ጊዜ ያጋጠሙኝን አስደማሚና አስነዋሪ ነገሮችን ቢያንስ ሕብረተሰቡ ማወቅ አለበት ብዬ በማስታወሻዬ ዘግቤ ከያዝኩዋቸው አንዳንድ ነጥቦች ውስጥ ጥቂቶቹን ቆንጠር አድርጌ ላካፍላችሁ፡፡
ፍርሓት (ወኔ ሰላቢ በሽታ)
ህዝቡን አስደንግጦ! አስፈራርቶ! አሸብሮና ወኔ ሰልቦ መግዛት በደርግ ጊዜም የነበረ ቢሆንም የዛሬው ግን የረቀቀና ዓይን ያወጣ ሁኔታ ነው ያለው፡፡ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴር የነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ ለኢትዮ}ያ ህዝብ ካወረሱትና ካበረከቱት ትልቁ ስጦታና ራዕይ “ፍርሃት” ነው፡፡ ፍርሃት በአሁኑ ጊዜ ህወሓት/ኢሕአዴግ ህዝቡን አንበርክኮና ፀጥ ረጭ አድርጎ በሀይል ለመግዛት የሚጠቀምበት ትልቁ የፓለቲካ መሳሪያው መሆኑን እኔ ከምናገረው በላይ ነው፡፡ ፍርሃት በሕብረተሰቡ ውስጥ ገብቶ ምን ያህል አስከፊና አስፈሪ ሁኔታ እንደፈጠረ በይበልጥ የተረዳሁት ዘመድ ጥየቃ ከቦታ ወደ ቦታ ስንቀሳቀስ በደረስኩበት ቤት ሁሉ የማገኛቸው ሰዎች አንዳንዶቹ በስጋትና በጭንቀት ተውጠው እንባ እየተናነቃቸው ሲነግሩኝ ውስጤ በጣም ይሰማኝ ነበር፡፡ አዎ!! ሁኔታውን በአካል ተገኝቶ ለተመለከተው ሰው እውነትም ባለቤት ያጣ ያልታደለ ህዝብ! ያልታደለች ሚስኪንዋ ድሃ ሀገር! የሚያሰኝ ነው፡፡
ከዚህ በመነሳት ጥያቄ ለመሰንዘር ግድ ሆነብኝ፡፡ “እናንተ ዜጎች አይደላችሁም ወይ? በሀገሪቱ ሕግ የለም ወይ? ለመንግስት አቤት የማትሉበት ምክንያት ለምንድን ነው? የተሰማችሁ ሀሳብ ሁሉ ለሚመለከተው አካል በግልፅ ለመናገርና ለመቃወም ለምን ትፈራላችሁ?” ብዬ ብጠይቃቸው የሰጡኝ መልስ የሁሉም ሃሳብ ተመሳሳይ ነው፡፡ “እኛ የሕግ ዋስትና የለንም፡፡ መንግስትም ራሱ ለሕግ ተገኝ ካልሆነ ለማን አቤት ይባላል” የሚል ነው፡፡
“ስማ ወንድማችን! እኛን የሚያስተዳድሩን እኮ መንግስት የላካቸው ካድሬዎችና ታማኞች ናቸው፡፡ በሕብረተሰቡ ዘንድ አፍ ጠባቂዎች እየተባሉ የሚጠሩ የተለያዩ የስለላ መረቦች በየመንደሩ በውስጣችን እንዳሉ እናውቃለን፡፡ ለመቆጣጠር እንዲመቻቸውም ከላይ እስከ ታች ሕዝቡን አንድ ለአምስት አደራጅተውታል፡፡ ቀጥሎም የቤተ ሰብ ሸንጎ የሚባልም አለ፡፡ ከዚህም አልፎ የፌዴራል ፓሊስ! ያካባቢው ፓሊስ! ሚሊሻና የተለያዩ ስውር ታጣቂዎች ሁሉም በአብዛኛው ጊዜ የሚጠብቁት የህዝቡን ድህንነትና የዜጎች ህልውና ቅድሚ በመስጠት ሳይሆን የኛን ነፃ እንቅስቃሴ የሚገድቡና አፋችንን የሚጠብቁ ሀይሎችም ናቸው፡፡ ሌላ ቀርቶ በቤተሰብ መካከልም መተማመን የለም፡፡ ባል ካፈነገጠ በሚስቱ ወይም በዘመዶቹ ሚስት ካፈነገጠች ደግሞ በባልዋ ወይም በልጆችዋ እየገቡ ትዳር እንዲፈርስ ወይም እንዲካሰሱ ያደርጋሉ፡፡ ከተናገርክ ደግሞ አፍ እላፊ እየተባለ ከስራ ትባረራለህ! መሬትህን ወይንም ንብረትህን ትነጠቃለህ! በህዝብ ስም ከውጭ የሚመጣ እርዳታም እንዳታገኝ ይደረጋል! ከዚህም አልፎ እንደ ጠላት የተፈረጁ የተቃዋሚ ፓለቲካ ድርጅቶች ስም እየተለጠፈብህ የትምክህተኞች አቀንቃኝ! አሸባሪ ! ከሃዲ! ወዘተ በሚል ሰበብ ተከሰህ ወደ አቦይ ታአገስ (እስር ቤት) ትገባለህ፡፡ ከዚያ በሗላ ጠያቂ የለህም፡፡ ወይም ሀገር ለቀህ ትጠፋለህ አሊያም ትሰወራለህ፡፡ ባጠቃላይ ሌላ ሰው ወይም ሕብረተሰቡ ተቃውሞ ወይም የፍትሕ ጥያቄ እንዳያነሳ ለማድረግ እኔን አይተህ ተቀጣ የሚል ሌላ ስውር መልእክት በሚያስተላልፍ መልኩ ግፍ ይፈፀምብሃል፡፡
በዚህ ምክንያት የሆድ ቁስል ይዘን እያወቅን እንዳላወቅን አፋችንን ይዘን ዝም እንላለን፡፡ ለማንስ አቤት እንበል፡፡ ከጎጥ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ አመራር ያለው የካድሬና የስለላ ሰንሰለት ነው፡፡ እኛ እኮ በሀገሪቱ ሕገ መንግስት አለ ሲባል በወሬ እንሰማለን እንጂ ሕጉ ፈፅሞ እኛን አይመለከተንም፡፡ ሕግና ስርዓት ቢኖርማ እንዲህ አይሆንም ነበር፡፡ እኛ እኮ እስካሁን ድረስ የምንተዳደረው በትጥቅ ትግሉ ጊዜ ከነበረው የድርጅቱ ሕግና ስርዓት የተለየ አይደለም፡፡ ድሮ ሲያስተዳድሩን የነበሩት የህወሓት ካድሬዎች ናቸው አሁንም ከላይ እስከ ታች አፋችሁን ያዙ እያሉ እየኰረኰሙ እየገዙን ያሉት እነሱ ናቸው ሌላ አዲስ ነገር አልመጣም” እያሉ የነገሩኝ ብዙ ናቸው፡፡ በተለይም የቅርብ ዘመዶቼና ጓደኞቼ በጆሮዬ ሹክ እያሉ “ከሰው ጋር ብዙ አታውራ፡፡ ጠንቀቅ በል፡፡ ሲቪል መስለው ካድሬዎች ይከታተሉሃል፡፡” በማለት ምክር ይለግሱልኝ ስለነበር ከሌላ ሰው ቀርቶ ከቅርብ ዘመዶቼ እንኳን ሳይቀር ነፃ ሆኖ ለማውራት በጣም ከባድ ነበር፡፡
የሃሳብ ነፃነትና መደራጀት
የሃሳብ ነፃነትና መደራጀት በሕገ መንግስቱ ሰነድ ቁልጭ ብለው ከተቀመጡት መሰረታዊ” ሰብኣዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ውስጥ ዋነኞቹ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ መብቶች ከወረቀት አልፈው በመሬት ላይ አይታዩም፡፡ ሕጉ ለባለሰልጣናት እንጂ ለሰፊው ህዝብ ባዕድ ነው፡፡ ሕጉ የአንድ ድርጅት የበላይነት ጠባቂና መሳሪያ እንጂ የህዝቡንና የሀገሪትዋን ሉአላዊ ክብር የሚጠብቅ ሞሶሶ አይደለም፡፡ ሕጉ ሌሎችን በተለይም በጠላትነት ለሚያዩዋቸው ተቃዋሚ ድርጅቶችን ለመምታት” ለማሳደደድ” ለማሰርና ለማዳከም የሚጠቀሙበት ትልቁ መሳሪያ እንጂ ለእኩልነትና ለፍቅር የቆመ አይደለም፡፡ በሌላ አነጋገር የዳኝነት” የፍትሕ” የምርጫና ሌሎች የዴሞክራሲ ተቋማት የአንድ ድርጅት አገልጋይና መሳሪያ በሆኑበት” ባጠቃላይ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ኢሕአዴግ የተለየ ሃሳብ ያላቸውን ዜጎች እንደባላንጣ ፈርጆ ሰበብ አስባብ እየፈለገ በመምታት ራሱን አውራ ፓርቲ ነኝ ብሎ የሰየመ አምባ ገነናዊ ስርዓት በነገሰበት ሀገር ስለ የሃሳብ ነፃትነትና መደራጀት ብሎ ማንሳት አይቻልም፡፡ በተለይም አሁን ከአቶ መለስ ዜናዊ ህልፈት በሗላ ብሶበታል፡፡ በተለይም የመለስ ራእይ ወራሽ ነን የሚሉ ቡድኖችና ባለስልጣናት ራሳቸው በራሳቸው መተማምን አቅቷቸው ሁሉም ነገር በአንድ ፓርቲ ቁጥጥር ስር መሆን አለበት በሚል ጭፍን አስተሳሰብ ላይ በመመስረት ያለ ምሕረት እየጠረጉ ወደ ፍፁም ጠቅላይ (ቶታሊቶሪያን) የሆነ ስርዓት ተሸጋግሯል፡፡
ከዚህ በመነሳት ዛሬ በሀገራችን ሰላማዊና ሕጋዊ የትግል መንገድ ተከትለው ሕጋዊ ፈቃድ አውጥተው በመንቀሳቀስ ላይ በሚገኙ ተቃዋሚ የፓለቲካ ድርጅቶች ላይ እየደረሰ ያለው አፈናና ወከባ ይህን ነው ብሎ ለመናገር ይከብዳል፡፡ ባንድ በኩል ፈቃድ እየሰጠ በሌላ በኩል ደግም ህገ መንግስት የሰጣቸውን መብት እንዳይጠቀሙ በመከልከልና ብሎም በመገደብ መፈናፈኛ አሳጥቷቸዋል፡፡ ከህዝብ ጋር እንዳይገናኙ” አባላት እንዳይጠጉዋቸው” ህዝባዊ ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ እንዳያደርጉ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መሰናክል በመፍጠር የተለያዩ ፀረ ዴሞክራሲና ኢፍትሓዊ የሆኑ እርምጃዎች እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡ ሕብረተሰቡን በተለይም አዲሱ ትውልድ ለለውጥ ሊያነሳሱ ይችላሉ ብሎው የሚገምትዋቸው በአመራር ላይ የተቀመጡ ወጣት ምሁራን ላይ ሆን ብሎው በማነጣጠር በፀረ ሽብር አዋጅ እያመኻኙ ማሰር ስራዬ ብሎው ተያይዞውታል፡፡
ድርጊቱ ደረጃው ይለያይ ይሆናል እንጂ በሁሉም አካባቢ በሁሉም ተቃዋሚ ድርጅቶች ላይ የሚፈፀም ቢሆንም በተለይም ዓረና ትግራይ በሚባል በትግራይ ውስጥ በህግ ተፈቅዶለት በሚንቀሳቀስ ድርጅት ላይ እየተፈፀመ ያለው ግፍ እንደ ምሳሌ ወስደን ብናይ በመላ ሀገሪቱ ያለው አስከፊ የፓለቲካ ደባብ ትክክለኛ ገፅታ ማሳያ ይሆናል ብዬ አምናለሁ፡፡ ድርጅቱ በይፋ በሕግ ከተቋቋመ ጀምሮ አቅሙ በፈቀደው መጠን ይንቀሳቀሳል፡፡ ድርጅቱ የተፈጠረበት ሁኔታ መለስ ብለን ስናይ ትግራይ “የተለየ አመለካከት የያዘ ትግርኛ ተናጋሪ ቀርቶ የተለየ መልክ ያላት ወፍ እንኳን ዘወር አትልበትም በማለት ለአርባ ዓመታት ያህል የህወሓት ትልቁ መደበቂያ ምሽግና ብቸኛ የጓሮ አትክልት ሆኖ በቆየው ምድር ላይ” በመሆኑ ለዓመታት ያህል ስር የሰደዱ የተለያዩ የመጨቆኛ መረቦችንና ሞኖፓላዊ አስተሳሰቦችን ሰብሮ የመርፌ ቀዳዳን የምታህል መንገድ አልፎ በምትኩ ዴሞክራሲያዊና የሰለጠነ ራእይ ይዞ ወደ ሕብረተሰቡ ለመግባት ምን ያህል አስቸጋሪና ውስብስብ ትግል የሚጠይቅ መሆኑን ለመገመቱ አያዳግትም፡፡
ወደ ጠንካራ ሀገራዊ ድርጅት መፈጠር እንደ መሳለል ሆኖ ያገለግላል ተብሎ በሚሊኖች ዘንድ ተስፋ የጣለለት ዓረና በትግራይ አማራጭ ፓርቲ በመፈጠሩ የሚያስደነግጣቸውና እንደ ትልቅ ስጋት የሚያዩት የህወሓት መሪዎች ብቻ አይደሉም፡፡ ሌሎችም የኢትዮ}ያ መፈራረስና ጥፋት የሚመኙ በተለይም በትግራይ በትግራይ ምድር ላይ ኢትዮ}ያዊነት ማንነትና ሀገራዊ ራዕይ የሰነቁ ለህዝቦችዋ አንድነትና ክብር የሚሟጎቱ ሀገር በቀል ብሄረተኞች እንዳይበቅሉ የሚሰጉ እንደ ሻዕቢያና ጀሌዎቻቸው የመሳሰሉት ሀይሎች ይህቺን ባቄላ ካደረች አትቆረጠምም በማለት ዓረና ትግራይን ከእንጭጩ ለማጥፋትና ለማዳከም የዘወትር ተግባራቸውና ሕልማችው መሆኑን ህዝቡ ከጥዋቱ ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ ሌላውን ትተን በቅርቡ የብዙሃን መገናኛዎችንና ማህበራዊ ድህረ ገፆችን እየተጠቀሙ በዓረና አባላትና መሪዎቹ ላይ የተቀናጀ ጥቃት ለመፈፀም ምን እያሉ እንደሆነ በቀላሉ መገንዘብ ይቻላል፡፡ የሚገርመው አንዳንዶቹ እንዲያውም ለነገሩ ለይስሙላ ተቃዋሚዎች ነን ይበሉ እንጂ በተግባር ሲታይ ስውር አጀንዳቸው ከህወሓት/ኢሕአዴግ በላይ ዓረና ትግራይን እንደስጋት የሚያዩት መሆናቸውን በግልፅ የሚያመላክት ነው፡፡ ሆኖም ሀቁ “እኛም አውቀናል ጉድጓድ ጭረናል” እንደተባለው ሁሉ ጭቆና ያንገሸገሸው ህዝብ ነፃ እስካልወጣ ድረስ ይቅርና የወሬ ጋጋታ ሚሊዮን ጦርም ቢሰለፍ ከመታገል ወደሗላ ሊመልሰው የሚችል ምድራዊ ሀይል እንደማይኖር ሊያውቁት በተገባ ነበር፡፡
ከዚህ የተሳሳተ አመለካከትና ግምት በመነሳት በተለይም በመንግስት በኩል የዓረና ትግራይ ፓርቲ አባላት ለሆኑ ዜጎች የሚደርስባቸው ጫና” ግፍና አፈና ለመቀበል አይደለም ለማሰብም በጣም ያስቸግራል፡፡ ካድሬዎቹ ራሳቸው ከሳሽ” ራሳቸው መስካሪ” ራሳቸው ዳኛና አሳሪ እየሆኑ ማሰቃየት” ከህብረተሰቡ እንዲገለሉ ማድረግ” ከስራ ማባረር” ሀገር ያፈራውን ጥቅማ ጥቅም መከልከል የተለመደ ስራ ሆኗል፡፡  የትምክህት ሀይሎች አመለካከት አራማጆች” እንዲሁም በነሱ አጠራር አሸባሪዎችና ታሪካዊ ጠላቶቻችን ናቸው ከሚሉዋቸው ጋር በማዛመድ ተላላኪዎችና ወኪሎች ናችሁ” በመባል እየተወነጀሉ አብረው የጥቃቱን ሰለባ እንዲሆኑ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ከዚህ የተነሳም ማሕበራዊ ቀውስና ጫና እየደረሰባቸው ያበዱ ወይም የት እንደገቡ የማይታወቁ የድርጅቱን አባላት ቁጥራቸው ቀላል አይደለም፡፡ በዚህ ዓይነት በተመሳሳይ እየተከሰሱና እየተጠረጠሩ ቤታቸው የፈረሰ ቤተሰብ” የተፋታ ትዳርና ሳይወድ በግድ ከሞቀ ቤቱና ከቀዩ እየፈለሰ ወደ ስደት የሚጎርፈው ወጣት ቤቱ ይቁጠረው፡፡ ለአብነት የሚከተሉትን ግለሰቦች የደረሰባቸው ግፍ እንመልከት፡፡
  • መምህር ሀይሌ አሰመኽኝ የሚባል የህወሓት የቀድሞ ታጋይ የነበረና በሗላም በባድመ ጦርነት የቀኝ እጁን ተቆርጦ ወደ ቤቱ የተመለሰው ወገን የአረና ትግራይ አባል በመሆኑ ብቻ በአካባቢው ካድሬዎች በተደረገበት ክትትልና ወከባ ምክንያት እንዲያብድ ተደርጎ አሁን የት እንዳለ አይታወቅም፡፡ ቤተሰቡም ድርብ ድርብርብ ሃዘን ሆኖባቸው እያለቀሱ ይገኛሉ፡፡ በሸራሮ ከተማም በተመሳሳይ አካሃን አቶ ፍፁም ያሃንስ በሚባል ወገናችን በደረሰበት ተፅእኖ አብዶ የከተማው ህዝብ መቀጣጫ ሆኖ ይገኛል፡፡

  • በዛና ከተማ እና አካባቢዋ በጣም ታዋቂ የነበረው የድሮ የህወሓት ታጋይ ዛሬ የአረና አባል በመሆኑ ብቻ ካድሬዎቹ ሲከታተሉት ከቆዩ በሗላ እሱን የሚያጠቁበት የተለያየ ምክንያት በመፈለግ በቤተሰቡ ላይ ጫና በመፍጠርና በመካከላቸው ጣልቃ በመግባት የገዛ ዘመዶቹና ቤተሰቦቹ ሳይቀሩ እንዲከሱት እና ተባባሪ እንዲሆኑ በማድረግ በደረሰበት ተፅእኖ ከቤቱና ከቀዩ እንዲባረር ተደርጎ አሁን አዲስ አበባ ይገኛል፡፡ ይህንን እውነታ በግልፅ የነገረኝ ስሙን እንዲጠቀስ ያልፈለገው የመንግስት ሰራተኛ የሆነው የራሱ ወንድም ነው፡፡

  • ሌላ አንድ ወጣትም ተመሳሳይ ፈተና ገጥሞታል፡፡ ልጁ የአረና አባል አይደለም፡፡ ነገር ግን አንድ ቀን ወጣቱ ከአንድ የአረና ትግራይ አባል በመንገድ ተገናኝተው ቆሞው ሲያወሩ እንደአጋጣሚ ሆኖ ሌላ አንድ የሚያውቀው ልጅ ሰላም ብሎት አብሮት ትንሽ መንገድ ይጋዛል፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በሗላ ልጁ ወደ ስራ ቦታው ሄደና ገና ስራ ከመጀመሩ በፊት ለካስ መረጃ ተላልፎ ቆይቷል በአስቸካይ አስተዳደር ጋር ይጠራል እና ይገባል፡፡ ሃላፊውም “ከመቼ ጀምረህ ነው የአረና ትግራይ አባል የሆንከው?” ብሎ ድንገተኛ ጥያቄ ይጠይቀዋል፡፡ “የማናውቅ እንዳይመስልህ እውነቱን አውጣ” ብሎ ያስፈራራዋል፡፡ ልጁም በድንጋጤ የአረና አባል እንዳልሆነ ቢገልፅለትም ሃላፊው በፍፁም ሊቀበለው አልቻለም፡፡ እናም ከዛ በሗላ ከባድ ማስጠንቀቅያ ተሰጥቶት ወደ ስራው ተመልሷል፡፡
የልጁ አባትም አብረውት በዚሁ መስሪያ ቤት ውስጥ በዘበኝነት ተቀጥረው ይሰራሉ፡፡ አባትየውም በተመሳሳይ ተጠርተው ልጃቸው ዓረና እንደሆነ እና ስራቸው አደጋ ላይ ሊወድቅ እንደሚችል ተነግረዋቸው እሳቸውም ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶዋቸው ወደ ስራቸው ይመለሳሉ፡፡ ሁለቱም ማታ በቤት ከተገናኙ በሗላ አባትየው ልጃቸውን ቁጭ አድርገው የዓረና አባል መሆኑን እና አለመሆኑን ሲጠይቁትና ሲመረምሩት አመሹ፡፡ እሱም እንዳልሆነ ገለፀላቸው፡፡ በመጨረሻ አባትየው “በል ስማ ከዚህ በሗላ የአረና ትግራይ አባል ሁነህ ካገኘሁህ ግን ሰው ያላደረገውን ባንተ ላይ አደርጋለሁ” አሉት፡፡  ልጁም ገርሞት “ምን ታደርጋለህ አባዬ” ብሎ ሲጠይቃቸው እገድልሃለሁ አሉት በገዛ ልጃቸው፡፡ ይህን ቃል የነገረኝ ራሱ ልጁ ከጋደኞቹ ፊት ቁጭ ብለን ስናወራ ነው፡፡  ልጁ አሁን በአዲስ አበባ ከተማ በደህና ቦታ ተቀጥሮ እየሰራ የሚገኝ የመንግስት ሰራተኛ ነው፡፡ አሁን ልጁ ለስርዓቱ ያለውን ታማኝነት ለመግለፅና እንዲሁም ከአባቱ ጋር ተግባብቶ ለመኖር ሲል በማያምንበት ጉዳይ በየቀኑ ህወሓትን ደግፎ በየፌስቡኩ ሲሳደብ ይውላል፡፡
አብርሃ ደስታ
ለረጅም ጊዜ በቅርብ ርቀት ሲከታተሉት ከቆዩ በሗላ የመንግስት ጣት ተቀስሮባቸው የስርዓቱን የአፈና ሰለባ ከሆኑት ሰላማዊ ታጋዮች አንዱ በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የፓለቲካ ሳይንስ መምህር የሆነው ወጣት አብራሃ ደስታ ነው፡፡ ከመታሰሩ ጥቂት ቀናት በፊት በስልክና በአካል በመቐለ ከተማ ተገናኝተን አብረን ቁጭ ብለን በሰፊው እንድናወራ እና ይበልጥ ማንነቱን እንዳውቀው እድል አግኝቼ ነበር፡፡ አብራሃ በፅሁፍ እና በአካል ስታየው በጣም ይለያያል፡፡ ከምጠን በላይ ትሁት” ሕግና ስነ ስርዓት አክባሪ ሰው ነው፡፡ ረጋ ብሎ የመናገር እና የማስረዳት ችሎታው ከፍተኛ ነው፡፡ ተግባቢ ነው፡፡ አድማጭ ነው፡፡ በፍፁም አይጠጣም አያጤስም፡፡ ለስላሳ ይደግማል፡፡ በዩኒቨርሲቲው ማሕበረሰብ ዘንድም በስራ ችሎታቸውና በሞያ ብቃታቸው ከሚደነቁትና ከሚከበሩት ሰዎች አንዱ ነው፡፡
አብርሃ ደስታ ለሰላማዊና ሕጋዊ ዴሞክራሲያዊ ትግል ያለው ፅናትና እምነት በቃላት ብቻ ሳይሆን በተግባርም በሄደበት ሁሉ በህዝባዊ ስብሰባም ሆነ በግል ሲወያይ በሰላም ታግሎ እንዴት ለውጥ ሊመጣ እንደሚችል ሲያስተምር ቆይቷል፡፡ በስብሰባ በህዝብ ፊት ቀርቦ የማሳመን ችሎታውም ከሞያው ብቃት ተዳምሮ ዘመን የፈጠረው ታጋይ እየተባለ በብዙዎቹ ዘንደ ይነገርለታል፡፡ ብቃቱንና ፅናቱን የቀድሞ የአረና ትግራይ አመራር የነበረው እና በሀገራዊ ምርጫ ዋዜማ ባልታወቀና በረቀቀ ሁኔታ በጭካኔ የተገደለው የወጣቱ ታጋይ አረጋዊ ገብረዮሐንስ ወኔ ወራሽ ነው እየተባለ ይነገርለታል፡፡
አብርሃ ደስታ ህወሓትን በሃሳብ እንደተሸነፈና ከመሳደብ” ከማሸበርና በጉልበት ከማሰር በስተቀር በህዝብ ፊት በአደባባይ ቆሞ በሀገራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ በግልፅ ለመወያየት የሞራል መሰረትና ብቃት የሌለው የበሰበሰ ድርጅት መሆኑን በግልፅ ይናገር ነበር፡፡ይህም ህወሓቶች የተለየ ሃሳብ ይዞ በግልፅ መወያየት ያልለመዱት የፓለቲካ ባህል ስለሆነ እንደድፍረት በመቁጠር ጥርስ ተነክሶበት ከቆየ በሗላ እንደተለመደው አብርሃ ደስታን የሚያጠምዱበት ቀንና አጋጣሚ ሲከታተሉና ሲጠብቁ ከርሟል፡፡
በመጨረሻም ከትግል አጋሮቹ ጋር ቁጭ ብለን እያወራን እያለ ስለ የስርአቱን ምንነት” ያለው ክፋትና አፈና ከባህሪያቸው ጋር አያይዞ ብዙ ዝርዝር ነገሮች አወሳልን፡፡ ስለራሱ የግል ጉዳይም በማንሳት ከአንድ የደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርስቲ ጋር የዶክትሬት ፕሮገራም ይከታተል እንደነበረ እና በማያውቀው ሁኔታ ስለተቋረጠ ወደ ሚመለከተው አካል ሄዶ መማር እንዳልቻለ ነገረን፡፡  ለምን እንደተቋረጠ ቢጠይቅም ባለስልጣኑ በፌዝ “አንተ ስለ ትምህርት ታወራለህ፡፡ ያንተ መማር ይቅርና ሌሎቹ ካንተ ጋር ሰላምታ የሚለዋወጡ ሰዎችም ጭምር አደጋ ላይ ናቸው፡፡” ብሎ እንደ መለሰለት ነገረን፡፡ ከዚያቺ ደቂቃ ጀምሮ አብርሃ እንደሚያስሩት አስቀድሞ ያውቅ ነበርና ቁጭ ብለን በጋራ ስናወራ የአብርሃ ደስታን ፓለቲካዊ ብስለት ከሚናገራቸው ቃላት በላይ ከፊቱ የሚነበበው ልበ ሙሉነት” የአላማ ፅናትና ድፍረት ይታይበት ነበር፡፡ እንደሚያስሩት እያወቀ ምንም የፍርሃት መንፈስ ወይም ስጋት አይታይበትም፡፡ እኔም ገረመኝ፡፡ ለማመንም ከብዶኝ ነበር፡፡
አዎ!! በኔ እምነት በማስረጃ ላይ የተደገፈ ነገር ካለ አንድ ሰው ሕግ ፊት መቅረብ የለበትም የሚል ጭፍን እምነት የለኝም፡፡ ነገር ግን ዜጎች የተለየ እምነት ስለያዙ ብቻ ለአንድ ድርጅት የፓለቲካ ጠቀሜታ ተብሎ (politicaly motivated) ወይም በቂም በቀል (Revenge) ተነሳስቶ በሰላማዊያን ዜጎች ላይ የሚፈፀም የስም ማጥፋትና የክስ ሂደት ድራማ ግን ሕገ ወጥ ድርጊት ብቻ ሳይሆን በኢትዮያዊነታችን የርህራሄ ባህላችንም አኳያ ሲታይ ኢሰብኣዊነት” ከሃላፊነትና ከስነ ምግባር ውጭ ስለሆነ አልደግፈውም ብቻ ሳይሆን መወገዝ ያለበት ነው፡፡
በዚሁ መለኪያ በአብርሃ ደስታ ላይ የተፈፀመ እንግልትና እስር ሲታይ ከነ ብርቱኳን ሜደክሳ እና ሌሎች በቃሊቲና በማእከላዊ እስር ቤቶች ታጉረው ከሚገኙ የህሊና እስረኞች የሆኑት ወጣት ፓለቲከኞች ወንድሞቻችን ጋር ተመሳሳይነት አለው፡፡ የክሱ ቀደም ተከተልና አካሄድ ስናየው ሕጋዊ መሰረትና እውነትነት የሌለው መሆኑን የሚያሳየው መጀመሪያ እንደ እንስሳ በጉልበት መደብደብ” ከዚያ በሗላ ማሰር” ከተደበደቡና ከታሰሩ በሗላም ከዳኝነት በፊት ከሰብኣዊ አያያዝ ውጭ ለፐሮፓጋንዳ ጠቀሜታ ሲባል በቪድዮ እየቀረፁ ለፓብሊክ ማጋላጥ፡፡  ከዚያም ቀጥሎ ለይስሙላ ማስረጃ ፍለጋ መሄድ ሲሆን የመጨረሻ ዕድላቸው ደግሞ በወህኒ ቤት እንዲበሰብሱ ወይም የይቅርታ ወረቀት እንዲፈርሙ በማድረግ የትግል ወኔያቸው አኰላሽቶ መልቀቅ ነው ፡፡ ይህ የዜጎች ሰብኣዊ ክብርና ሕገ መንግስታዊ መብት የሚዳፈርና የሚፃረር” ከአንድ መንግስት ነኝ ከሚል አካል የማይጠበቅ ሕገ ወጥ ተግባር ከመሆኑም በላይ ኢትዮ}ያ የፈረመችባቸው ዓለም አቀፍ የሰብኣዊ ፍጡርና የሕግ እስረኞች አያያዝ ሕግጋትም የሚጥስ ነው፡፡

አብርሃ ለምሳሌ ያህል ጠቀስኩት እንጂ በሌሎች ክፍላተ ሀገር በወጣት ታጋይ ወንድሞቻችን ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃም አላማው ተመሳሳይ ነው፡፡ በኢትዮ}ያ በሀገር ደረጃ የትግል አንድነት እየተፈጠረ ከሄደና ወጣት ምሁራን ወደ ትግሉ እየተቀላቀሉና የፓለቲካ አመራሩን እየተኩ ከሄዱ ለህወሓት/ኢሕአዴግ ትልቅ ስጋትና የፓለቲካ ኪሳራ ነው ከሚል ስሌት የመነጨ የፍርሃት እርምጃ መሆኑን ያዳባባይ ሚስጢር ነው፡፡
የሚገርመው ግን ህወሓቶችና ኢሕአዴጎች በወገን ላይ አፈናና ግፍ መፈፀማቸው ብቻ አይደለም፡፡  ነገር ግን አምባ ገነኖች የህዝብ እሮሮና ብሶት የዶሮን ያህል ግምት ሳይሰጡ በሰራዊት ጉልበት” በጦር መሳሪያ ጋጋታና ክምር ተማምነው ግለሰቦችንና ታጋዮችን ባሰሩና ጭቆናውን እያከረሩ በሄዱ ቁጥር የህዝቡን ልብ የበለጠ እንዲሸፍትና ሽዎች ታጋዮች እንዲፈልቁ ያደርጋል እንጂ ትግሉን ማዳፈን እንደማይቻል ካለፈው ታሪክ ሳይማሩ አሁንም ተመሳሳይ ድራማ መስራታቸውን ነው፡፡ እንዲህ ከቀጠለ ደግሞ ወደዱም ጠሉም ዕድሜያቸውንም በዚያው መጠን እያጠረ መሄዱ የማይቀር ተፈጥራዊ ሂደት መሆኑንም በውል ሳይገነዘቡ መቅረታቸው ነው የሚያሳዝነው፡፡
ከላይ የተጠቀሱትን የመልካም አስተዳደር እጦት መንሲኤያቸው ሁሉም ከአንድ ወንዝ የሚቀዱ ናቸው፡፡ ይህ ማለት በሀገሪቱ ውስጥ ካለው ጠባብ የፓለቲካ ምሕዳር የሚመነጩ ናቸው ማለት ነው፡፡ የህወሓት/ኢሕአዴግ ስርዓት የህዝቡን መሰረታዊ ችግሮች ሊፈታ የማይችል” ዴሞክራሲያዊ ባህርይ የሌለው” መሰረቱን የተናደና የተፋለሰ ፓሊሲ የሚከተል በመሆኑ ብቻ የሚመነጩ ችግሮች ናቸው፡፡ መፍትሔውም የግለ ሰዎች መቀያየር ሳይሆን መሰረታዊ የአስተሳሰብ” የፓሊሲና የስርዓት ለውጥ ያስፈልገዋል ብዬ በፅኑ አምናለሁ፡፡ በኔ እምነት ማን ስልጣን ላይ ወጣ አይደለም ችግሬ፡፡  ዋናው ቁም ነገሩ ማን ምን ዓይነት ለህዝብ የሚጠቅም የፓለሲ ለውጥ ይዞ መጣ ነው መመዘኛዬ፡፡
ውድ ወንድሞቼና እህቶቼ
ከላይ በመጠኑም ቢሆን የጠቀሱኳቸው ነጥቦች ብዙዎቻችሁ እንደምትጋሩ እምነቴ ነው፡፡ በተለይም እኔም ባልሳተፍኩበት በዚሁ ዓመት አጋማሽ ላይ የትግራይ ክልላዊ መንግስት ያዘጋጀውን ፌስቲቫል ለመካፈል ከዲያስፓራ ወደ ትግራይ ክልል ሂዳችሁ በነበረበት ጊዜ ባለስልጣናቱ የህዝብ አዛኝ መስለው ለመታየት ሲሉ ቃጤማ አንጥፈው ለመቀበል ሙከራ ቢያደርጉም የህዝቡን እሮሮና መከራ ግን ለመሸፈን ስላልቻሉ በሕብረተሰቡ ውስጥ ማለት በመሬት ላይ ያለውን እውነታ ተገንዝባችሁ በየስብሰባውና በተናጠል ሲቀርቡ የነበሩ ጥያቄዎች የብዙዎቻችን ጥያቄ መሆናቸውን እገነዘባለሁ፡፡ በተጨማሪም ሰሞኑን በዓይጋ ድህረ ገፅ ላይ አባይ ወልዱ ሙሱናን በሚመለከት ሁለት ሽሕ ለሚሆኑ ካድሬዎች ሰብስቦ ያቀረበውን ካንገት በላይ ንግግር አስመልክቶ ህዝቡ የሚሰማውን ሃሳቡ እንዲሰጥ ተብሎ በተከፈተው የአስተያየት አምድ ላይ ከተሰጡት በመቶ የሚቆጠሩ አስተያየቶች ውስጥ አብዛኞቹ ቀደም ብዬ በክፍል አንድ ያቀረብኩትን ፅሑፍ በበለጠ የሚያጠናኩሩልኝ ሆነው በማየቴ ትእዝብታችን ብቻ ሳይሆን ብሶታችንም አንድ ዓይነት መሆኑን ለመገንዘብ ችያለሁ፡፡ የተሰጡ አስተያየቶችም በህዝባችን ላይ የተጫነው ሸክምና የተጋረጠው ቁስል በብዙዎቻችን ሆድና አእምሮ ውስጥ የታመቀ ብሶት ገንፍሎ እንደወጣ የሚያሳይ ሲሆን በሌላ መልኩ ደግሞ የጊዜ ጉዳይ እንጂ በልቡ የሸፈተ ህዝብ እንዳለ ቁልጭ አድርጎ የሚያመላክት ነው፡፡
አዎ!! የቀረቡት ወርቃማ አስተያየቶች” ጥያቄዎችና የለውጥ ፍላጎቶች ሁሉ ትልቅ ትርጉም ያላቸው ቢሆኑም ውጤት የሚኖረው በአግባቡ ተገንዝቦና አጢኖ መልስ ለመስጠት የሚችል የሚሰማ ጆሮ” ከጊዜው ጋር የሚመጥን አእምሮ” የህዝብንና የሀገርን ጉዳይ የሚያስቀድም ዴሞክራሲያዊ ተፈጥሮ ሲኖር ብቻ መሆኑን የግድ ይላል፡፡ ይህ ባለቤት ያጣ ሚስኪን ህዝባችን ከአፈና” ከፍርሃት” ከፍልሰትና ከውርደት ተላቆ የነፃነት አየር የሚተነፍስበት ስርዓት እንዲፈጠር ሁላችንም የሃሳብ ልዩነታቸንና ሕብረ ቀለማችንን እንደ ውበትና ፀጋ ተቀብለን በሚያገናኙን ጉዳዮች ዙሪያ ለጋራ ችግር በጋራ ለመፍታት ተባብረን መቆምና መጮኽ እንዳለብን ጊዜውም ራሱ እየተናገረ ነው፡፡
ቸር ይግጠመን
የዛሬው ፅሑፌ በዚሁ ይጠቃለላል፡፡ በሚቀጥለው የመጨረሻው ክፍል 3 ፅሑፌ የአቶ መለስ ዜናዊ አምልኮ በሕብረተሰቡ ዘንድ እየፈጠረ ያለው የስነ ልቦና ጫናና ሌሎች አንገብጋቢ ጉዳዮችን በማካተት ይቀርባል፡፡

sgbtsait@gmail.com

“አቦይ ስብሐት ጎበዝ ነኽ አለኝ” ያሉት ፓትርያርኩ ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱ ተፋጠው ዋሉ

abune-matyas
አቶ አባይ ጸሐዬ ፓትርያርኩን ጎበዝ አለ
አቶ አባይ ጸሐዬ ፓትርያርኩን ጎበዝ አለ

የሐራ ተዋሕዶ ዘገባ፦
ፓትርያርኩ የማኅበራት ገንዘብ ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ገቢ ኾኖ በማእከል ካልተመራ በሚል ከማኅበራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ጋራ የሚቃረን ግትር አቋም ይዘው ውለዋል፡፡
አቋማቸው ተቀባይነት ካላገኘ ስብሰባውን ለመምራት እንደሚቸገሩ በመግለጽ ምልአተ ጉባኤን ለማስገደድ ያደረጉት ሙከራ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱ ጽኑ አቋም ሳቢያ አልተሳካላቸውም፡፡
ጉዳዩ ‹‹ከአዲስ አበባ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ጋራ ብዙ የሠራኹበትና የደከምኩበት ነው፤ በቀላሉ የምተወው አይደለም›› በሚል ከአክራሪነት ጋራ የተገናኘ ጽሑፍ ሲያነቡ ውለዋል፡፡
ከተጀመረ ስድስተኛ ቀኑን ያስቆጠረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የመጀመሪያ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ በዛሬ፣ ጥቅምት ፲፯ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. ሙሉ ቀን ውሎው፣ የ፲፱፻፺፩ ዓ.ም. ሕገ ቤተ ክርስቲያን ለማሻሻል በቀረበውና የልዩነት አቋም በተያዘባቸው የረቂቁ አንቀጾች ላይ ጠንካራ ውይይት ሲያደርግ አምሽቷል፡፡
የማሻሻያ ረቂቁ፣ ባለፈው ዓመት ግንቦት የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ኹለተኛ ዓመታዊ መደበኛ ስብስባ ወቅት አንቀጽ በአንቀጽ ከተወያየበት በኋላ ተጨማሪ እርማትና ማስተካከያ አድርጎ ለአኹኑ ምልአተ ጉባኤ እንዲያደርስ የሠየመው ስድስት አባላት ያሉት የብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የሊቃውንትና የምሁራን ኮሚቴ ያቀረበው ነው፡፡
የማሻሻያ ረቂቁንና በኮሚቴው አባላት መካከል የልዩነት አቋም የተያዘበትን ቃለ ጉባኤ ባለፈው ቅዳሜ ከቀትር በፊት ውሎው የተናበበው ምልአተ ጉባኤው፣ ለዛሬ በቀጠረው መሠረት ነው ፍጥጫ የተቀላቀለበት ውይይት ሲያደርግ የዋለው፡፡
የልዩነት አቋሞች የተያዘባቸው ነጥቦች፡-
የሊቃነ ጳጳሳትን ተጠሪነት(ዝውውር እና ምደባ)
የማኅበራትን ተጠሪነትና የገንዘብ እንቅሰቃሴ ማእከላዊነት
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አመራር የተመለከቱት ይገኙበታል፡፡
ከስድስት የኮሚቴው አባላት መካከል በሦስቱም ነጥቦች ላይ የልዩነት አቋማቸውን በቃለ ጉባኤው ያስመዘገቡት የፓትርያርኩ ልዩ ጸሐፊ ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ ናቸው፡፡ ልዩ ጸሐፊው ከአምስቱ የኮሚቴው አባላት ተለይተው በያዙት አቋም÷ የሊቃነ ጳጳሳቱንና የማኅበራትን ተጠሪነትን ለቅዱስ ሲኖዶስ የሚያደርጉት የረቂቁ አንቀጾች ለፓትርያርኩ ይኹን በሚል እንዲተኩ፤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትም የፓትርያርኩ ልዩ ሀገረ ስብከት እንደኾነ የሚገልጽ በረቂቁ ያልነበረ አንቀጽ በግልጽ እንዲቀመጥ ተከራክረዋል፡፡

Dienstag, 28. Oktober 2014

Response to References made about Ginbot 7 in the Report of the Monitoring Group of Somalia and Eritrea (here after SEMG), Pursuant to UN Security Council Resolution 2111 (2013).

October 28,2014

FOR IMMEDIATE RELEASE
MEMORANDUM
TO: The United Nations Security Council Sanctions Committee
FROM: Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy.
DATE: October 27, 2014
SUBJECT: Response to References made about Ginbot 7 in the Report of the Monitoring Group of Somalia and Eritrea (here after SEMG), Pursuant to UN Security Council Resolution 2111 (2013).
Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy expresses its high regards to The United Nations Security Counciland would like to use this opportunity and bring to the attention its reservations regarding some references made about it in SEMG report of October 13, 2014.
1. The SEMG report states that “Ginbot 7 is a banned opposition group”. We would like to call the attention of the International Community to the infamous “Anti-Terrorism Proclamation” promulgated by the TPLF/EPRDF regime of Ethiopia with the aim of stifling political dissent. The dictatorial regime has used this proclamation as an instrument to label and criminalize Ginbot 7, as well as other political opposition organizations, human rights advocacy groups, civil society, journalists and bloggers inside and outside of Ethiopia.
2. Let alone the claim in the report that Ginbot 7 was established in 2005, which is categorically false, even the so-called Anti-Terrorism Proclamation was not promulgated until 2009.
Ginbot 7 was formed in 2008 after few members among its leadership spent almost two years in prison in the aftermath of the ill-fated election of May 15, 2005. As well known by the International community, the regime overturned the election results that clearly showed the opposition party Coalition for Unity and Democracy (CUD) has won the majority throughout the country. This is a fact corroborated by international election observes such as the European Union’s Election Monitoring Group that was present in Ethiopia to observe the election in 2005. Those who formed Ginbot7, then leaders of the CUD, were among the leaders thrown in prison on trumped up charges.
Ginbot 7 was formed as a political movement in order to advance justice, freedom, and liberal democracy in Ethiopia. Ginbot 7 believes that no meaningful and genuinely competitive elections can take place in the country due to the prevailing and ever worsening egregious human rights violations, the closing of political space, the harassment and persecution of members of the legal and peaceful political opposition. Furthermore, an entrenched minority ethnocratic dictatorship in Ethiopia has determined to perpetuate its hold on power by all and any means necessary.
3. SEMG’s claim in the report that Ginbot 7 was established by “Amhara elites” is grossly erroneous given the ethno-religious mix of its leadership and membership. The report’s characterization of Ginbot 7 as an organization established by “Amhara elites” is not only factually inaccurate, but a clear indication of the bias of the report. It seems like SEMG has bought lock, stock and barrel the dictatorial regime’s fabricated story of Ethiopian politics as an entirely ethnic based phenomena.
The SEMG could have easily established the facts by taking a cursory look at Ginbot 7′s website rather than unquestioningly accepting the regime’s characterization with regard to Ginbot 7′s multi ethnic membership and leadership, its organizational principle and its well established position on ethnic based politics in Ethiopia. No effort seems to have been made by the SEMG to balance its report by counterchecking its claims from Ginbot 7 or other sources instead of recycling the minority regime’s long standing targeting and demonization of the Amharas, the second largest ethnic group in Ethiopia.
4. The SEMG, despite its familiarity with political conditions in the Horn of Africa, fails to realize what is very obvious to all regarding the TPLF/EPRDF regime’s agitation, use of threat, torture and at times bribery when presenting helpless prisoners under its custody to echo unfounded guilt they are coerced to rehearse for interviews and media presentations. Hence, presenting forced confessions and unreliable information from such prisoners as evidence is beyond comprehension.
5. The SEMG’s claim to have retrieved information from an alleged Ginbot 7 fighter captured in Gonder is no different from what is explained above.
6. SEMG’s reference in its report to weapons’ serial numbers to suggest the source of certain weapons as being from Eritrea, clearly neglects the fact that numerous prisoners of war, weapons and ammunitions have exchanged hands between Ethiopian and Eritrean forces during their numerous wars.
7. Needless to say that the SEMG has been manipulated to construe that Ginbot 7 needs to extend its recruitment to the southern tip of Africa, while what Ginbot 7 objectively faces is the capacity to accommodate the tens of thousands forcing their ways into its fold from amongst the millions who support it. These are Ethiopians from very diverse backgrounds seeking a genuinely liberal democratic and just order, freedom and equality which have been denied to them by the brutal dictatorial regime of the TPLF/EPRDF.
8. It is unfortunate to note that the SEMG has been misguided to misrepresent Ginbot 7’s prevailing organizational reality that clearly demarcates boundary between its own political bodies from that of other organizations that may have opted to attain their objectives by any other means they deem appropriate.
9. Ginbot 7 found the claim in the report regarding persons SEMG suggests were received by Andargachew Tsege upon their arrival in Asmara and who have “joined a group of 30 to 60 Ginbot 7 fighters at Harena Military Camp” comical, simply because the arithmetic percentile between 30 and 60 is 100% and hence too large a difference for any wrong guessing.
10. The SEMG clearly states in its report that it was unable to verify the claims of the alleged Ginbot 7 fighters, which begs the question, then, as to why the SEMG had to dwell in its defamatory claims and tarnish the image of Ginbot 7.
11. The same can be said about SEMG’s statement in its report regarding its inability to assess the extent of this unsubstantiated support as compared with Asmara’s support of Ginbot 7 in the past.
12. The SEMG seems to be deliberately overlooking or otherwise incognizant of TPLF/EPRDF regime’s well recorded expertise in passport, travel document, and other forms of forgeries going back to its days as a guerrilla force. Had this not been the case, understanding the nature of documents presented to it by the regime’s security officials, should not have been beyond the comprehension of the SEMG.
The allegations by SEMG may be well calculated and deliberate distortions aimed at upholding the sanctions imposed on Eritrea. However, we fail to comprehend why Ginbot 7, or the Ethiopian people for whose rights our organization is struggling for, is interjected in these maneuvers.
Ginbot 7, however, would like to use this opportunity to assure all concerned, including the United Nation’s Security Council, that it is ready to give freely and candidly tangible explanations related to its mission and the achievements in the process of registering its just struggle.
Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy would like to respectfully conclude its MEMORANDUM by strongly affirming that it stands ready and willing to cooperate with the International Community, in good faith, and contribute everything within its capacity for sustainable regional peace and stability in the Horn of Africa.
We look forward to your timely reply.

torchure ሚሊዮኖች ድምጽ -ሃብታሙ አያሌው ቶርቸር እየተደረገ ነው !



October 28,2014

ክስ ሳይመሰረትበት ለአራት ወራት በማእከላዊ እስር ቤት የሚገኘው የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ ወጣት ሃብታሙ አያሌው፣ ከፍተኛ ኢሰብአዊ ግፍ እየተፈጸመበት እንደሆነ ታወቀ።
“ወደ ፖለቲካው የማትመለስ ከሆነ ትወጣለህ። አለበለዚያ እዚሁ ነው የምትሞተው” በማለት አማራጭ ቢያቀርቡለትም፣ ሃብታሙ መሞትን እመርጣለሁ የሚል መልስ የሰጣቸው ሲሆን፣ እየደረሰበት ባለው ስቃይ በጣም እየታመመ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። “እስኪ ትግሉን እናስቀጥላለን የሚሉ ሰዎች ያድኑህ ? “ ሲሉ አሳሪዎቹ በስቃዩ የሚደሰቱ ሲሆን፣ ከባለቤቱ በስትቀር ጠበቃዉም ሁሉ ሳይቀር እንዳያየው ተደርጓል።
በተመሳሳይ ሁኔታ ዳንኤል ሺበሺ፣ የአንድነት የድርጅት ጉዳይ ም/ሃላፊ ፣ በታፈነና አየር በማያስወጣ ክፍል ዉስጥ እንዲታሰር በመደረጉ በተደጋጋሚ ለተቅማጥና ተያያዥ በሽታ መጋለጡን፣ እንዲሁም የመተንፈስ ችግር እንዳለበት ለማወቅ ችለናል። “የፓርቲያችሁ የገንዘብ ምንጭ ምንድን ነው ? አንድነት ዉስጥ ያሉ ጠንካራ አባላት እነማን ናቸው ? “ በሚል ጥያቄ የቀረበለት ዳንኤል ሺበሺ፣ ክብሩን በሚነካ መልኩ እንደሚሰደብም የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
ሃብታሙ አያሌው ፣ በእርሱ ላይ እይደረሰ ያለው ግፍ በማንም ዜጋ ላይ መድረስ እንደሌለበት በመግልጽ “የግፈኛው አገዛዝ እንዲያበቃ የኢትዮጵያ ሕዝብ መነሳት አለበት” ሲልም ለህዝቡ የትግል ጥሪ አስተላልፏል።
የአንድነት ራዲዮ የዘገበዉን እንደሚከተለው ያድምጡ !

Montag, 27. Oktober 2014

Meles’ Legacy Is Tripping The TPLF

October 27, 2014

by Kaleab Tessema
Let it be known that I never personally met or spoke with Meles, nor did I have the ability to read his mind. What I will say, just like everyone else, I can perceive the character of the man through his actions—the actions of a divider of people, murderer of the innocent, and thief of a nation’s potential.PM Meles Zenawi of Ethiopia
Thus, after the death of Meles an undisclosed illness, some people were speculating that the Tigray People Liberation Front (TPLF) would take the opportunity to abandon their fascist form of government and intractable “divide and rule” policies. Not only to end this cruel policy, the TPLF became worse than their late capricious prime minister. The TPLF hid Meles’ death from the people for about a month while his political party the Tigray People Liberation Front (TPLF) schemed and plotted to continue his legacy of oppression. Right now, they are brutally beating and harassing the people who disagree with their policies. While Andargachew Tsige was interrogated briefly by the regime’s security apparatus on Woyanne owned TV, we heard people being tortured in the background. The victims were screaming in excruciating pain. It is unprecedented that a government dare to show a shocking and a disturbed voice to the public.
Funny enough, the Woyanne groups are uneducated who do not care about people; they just perpetuate their own interests to buy more time to run the country for another twenty two years by preaching and adulating their late prime minister’s policies. Of course, Hailemariam Desalegne outcries about Meles’ greatness and a visionary leader, that brought a sustainable democracy which embraces all ethnicities in the country. it is quite clear that Meles was the one who picked Hailemariam as his deputy prime minister and if Hailemariam idolizes his late boss, no one would be surprised. In addition to that, Meles knew that Hailemariam is too much to divulge his repugnancy towards Amhara ethnic group which made him very loyal and closer friend to Meles.
I have been scrupulously watching the regime and its supporters on how they disseminate invidious discrimination of propaganda about Amhara by calling ‘NEFTEGNA’ to create an ethnic cleansing with other ethnics in order to stay in power which is dangerously wrong. There is no doubt that Meles and his party had a deep hatred towards Amhara. Even after Meles died, the so-called ruling political coalition, EPRDF junta government, each and everyone has anti-Amhara sentiment. I still do remember when Shabia and Woyanne were in the bush, their core principle of the slogan was first to break the back bone of Amhara. Of course, no one deny that Amaras have been suffered since the TPLF gripped the power.
Sadly enough, the TPLF brutal killing of innocent Amharas peasants in the southern part of the country was not enough; the TPLF tried to inject some sort of sterilizer into Amhara women that would make them unable to conceive. Further, a few years ago a report given to Woyanne parliament about the disappearance of 2.4 million Amharas in the census conducted was an evidence. The TPLF tried any means necessary to reduce the number of Amhara population. These diabolic actions on Amharas, it is not new, it is already in the record.
It is fact that Today’s TPLF and its surrogates control vast areas of wealth in Ethiopia. Of course, whether like it or not, many Tigryans are beneficiary more than any one of the Ethiopian ethnic group under the TPLF rule. For no reason, Amharas have been made the main target of vilification, and demonization by TPLF for the last twenty-two years. I know some of the TPLF’s sympathizers will not agree with the facts that I reveal about the TPLF ethnic junta is doing to the innocent Amharas in the south. At this point of time, the Woyanne propaganda on Amhara they created racial antipathy between other ethnic groups is not a lasting, it is a transient.

What are the Meles’ Legacies?

Since Meles’ passing, the TPLF have had a hard time to replace their late prime minister. The TPLF tried to look for a person whose ethnic origin is Tigryan or Eritrean who has a tendency to prevaricate about Ethiopian history, but they might think they would excoriate for the replacing their own ethnicity, and then the TPLF, after assiduously thinking, artfully and systematically appointed Hailemariam Desalegne as prime minister of Ethiopia whose ethnicity is from Welayita to divert the attention of the people. Funny enough, Hailemariam is a vulnerable prime minister who is not a decision maker where under surveillance of the TPLF. Every one knows in Ethiopia that Hailemariam is a puppet prime minister who takes an order from the TPLF cabal.
Having said that, Meles was a ferocious and a perfidious person who mortified the nation and its people in the eyes of the world in the twenty first century. Let us not forget that, Meles was the one who made Ethiopia landlocked and ninety million people left without port. He also publicly said that “Ethiopian’s history is only 100 years old, and its flag is a piece of rag.” At one time, I was surprised by his flippant remarks about Tewoderos and Menilik that he was comparing himself claiming that Ethiopians for the first time got a peace under his rule. Surprisingly enough, a despicable and a traitor person comparing himself to those great men and a true sons of Ethiopia who protected Ethiopians from foreign invaders is a bluffing and a gimmick. Anyway, that was his usual prating.
Going back to my point, the regime is worshiping of the late dictator to persuade his policy whose actions were anti-Ethiopian that put the country on a dangerous path of the division along ethnic and language line based federalism. At the matter of fact, Meles was a one-man rule who had an absolute power and spun the Woyane for the last twenty one years. Now the regime tries to preach personal cult of a tyrant leader by bemusing the true dictatorial legacy of Meles.
Meles was a capable of dissimulation to stay in power by creating an idea where most people agree with it, like ‘Renaissance Dam’, to divert the issues and muzzling the political dissents. When Meles wants to detain the people who disagree with his policies, he blackmails by creating false documents that involves with terror activities, and when he gets a big criticism from the people, he immediately changes his mind to release those who falsely put in prison. Then after brutally tortured and demeaned, the prisoners were required to sign a letter of apology to Meles Zenawi with preconditions.
Now, the Meles’ legacy is the word of God for Woyanne, which is not working well as worked well for him. Since Meles died, mass killings and incarceration have doubled in the country. As the result, these criminal acts made Ethiopians more united inside and outside against the TPLF than before. For example, recently in Washington D.C., the brave and courageous young people occupied the Woyanne Embassy and brought down the provocative TPLF flag, then hoisted the true colors of the Ethiopian flag. Thus, the dubious policies being made by Meles that put the present brutal regime into a deeper political quagmire. Arresting and torturing the people will not bring any solution for TPLF; rather, it aggravates civil strife and instability in the country.
Finally, I call on opposition forces to stand up and be a voice for defenseless people who have been physically and verbally assaulted by the brutal regime in Ethiopia. It is about time to put aside their differences and to work together at this critical time, otherwise, the TPLF continues to repress the people and dismember the country. I do not have a moral authority to tell the opposition what to do, but I would like to share my humble opinion to the opposition forces that unity is paramount in order to remove the Tigryan ruling oligarchy.

ESAT Special Interview with Benyam Bekele about Mezenger killing in Gamb...

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ 3 አመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት



የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በዛሬው ቀን በዋለው ችሎት 3 አመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት፡፡ ፍትህን ሲያሳትም የነበረውና ሁለተኛ ተከሳሽ የሆነው ማስተዋል ህትመትና ማስታወቂያ በ10 ሺህ ብር ቅጣት ተጥሎበታል፡፡ 

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጥቅም 3/2007 ዓ.ም የመንግስትን ስም ማጥፋት፣ ህዝብን ማነሳሳትና የህዝብን አመለካከት ማናወጽ በሚሉ ሶስት ክሶች ጥፋተኛ የተባለ ሲሆን አሁን የተፈረደበት በትኛው እንደሆነ ባይታወቅም በአንደኛው ክስ ነው ተብሏል፡፡ የጥፋነኝነት ክሱ በተነበበት ወቅት ግን ‹‹መንግስት ይገድላል፣ ያፍናል፣ ይጨቁናል ብሎ ጽፏል፡፡›› በሚል ጥፋተኝ ነው ተብሏል፡፡

አቃቢ ህግ የቅጣት ማክበጃ ያላቀረበ ሲሆን ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝም ሆነ ጠበቃው የቅጣት ማቅለያ አላቀረቡም፡፡ በሌላ በኩል የጋዜጠኛው ጠበቃ አምሃ መኮንን ይግባኝ እንደሚጠይቁ አስታውቀዋል፡፡

(ነገረ ኢትዮጵያ)

Sonntag, 26. Oktober 2014

የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ም/ቤት ተሰብስቦ ውሳኔዎችን አሳለፈ

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ብሔራዊ ምክር ቤት ዛሬ ከጠዋቱ 3፡30 ጀምሮ በመሰብሰብ የስራ አስፈጻሚውን የ10 ወር ዕቅድ መርምሮ በሙሉ ድምጽ ማጽደቁንና በተጓደሉ የኤዲቶሪያል ቦርድ አባላት ምትክ ምርጫ ማካሄዱን የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ለፍኖተ ነፃነት ገለጹ፡፡
እንደ አፈ ጉባኤው ገለጻ የዲሲፕሊን ጥሰት የፈጸሙ የፓርቲው የብሔራዊ ምክር ቤት አባላት ጉዳይ ላይ ምክር ቤቱ ሰፊ ውይይት ካካሄደ በኋላ በሥራ አስፈጻሚ በኩል ወደ ዲሲፕሊን ኮሚቴ እንዲመራ በመወሰን ስብሰባው መጠናቀቁን አፈ ጉባኤው ለፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል ገፀዋል፡፡
1546209_718191084932495_4741612790237882908_n
10702104_718191194932484_28106377305738686_n

1505243_718191134932490_6358908736255763742_n

Samstag, 25. Oktober 2014

ኢትዮጵያ - ምእራባውያን - አንዳርጋቸው - የወደፊት እጣ - ለትግል መነሳት

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
በአሸባሪው መንግስታዊ ዘራፊ እና አፋኝ ቡድን የታፈነው አቶ አንዳርጋቸው ጸጌ ወያኔ ለመፍታትም ሆነ ለመግደል ዝግጁ አይደለም ። ግደሉት አሊያም ስቀሉት ቢባሉ እንኳን በፍጹም አያደርጉትም። ምእራባውያኑ ከአፍ ወሬ ውጪ ምንም የሚተገብሩት ነገር የለም ፡ እስክንድር ነጋ በቂ ምሳሌ ሊሆን ይችላል ከሰብአዊ መብት ድርጅቶች ጀምሮ እስከ አሜሪካው የውጪ ጉዳይ አናት ኬሪ ድረስ ድምጻቸውን ቢያሰሙም ለይስሙላ እና ለብሄራዊ ጥቅማቸው እንዲሁም ነገ ሌላ መንግስት ቢተካ እንዲህ ብለው ነበር እንዲባልላቸው እና እዳ ማውረጃ ንግግራቸው ለትግሉ ምንም የሚያበረክተው አሊያም ለአንዳርጋቸው የሚፈይደው ነገር የለም ።

ለአንዳርጋቸው ይሁን በእስር ለሚማቅቁት ወገኖቻችን የሚፈይደው ዋናውና አንዱ ጉዳይ የኛ ጠንክረን መታገል እና አንድ እርምጃ መጓዝ ሲሆን የዛን ሰአት የኛን መጠናከር እና መታገል የተመለከቱ ም እራባውያን ምን እንርዳችሁ ከምን ደረሳችሁ ምናምን ማለታቸው እና መጠየቃቸው ግድ የሚልበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም ፡፤ አሁን የሚፈለገው የኛ መታገል እና መታገል ብቻ ነው። የነጮቹ የከንፈር ልብላቤ ከብሄራዊ ጥቅም ሚዛን ሂደት ምስረታ ላይ ስለተመረኮዘ ከንግግር ውጪ ምንም አይፈይድም:

ልብ ማድረግ ያለብን ከማ እከላዊ አፍሪካ እስከ አፍጋኒስታ ከሊብያ እስከ ኢራቅ በተለያዩ የአፍሪካ እና የመካከለኛው እንዲሁም የኢስያ ሃገራት ም እራባውያኑ የሚያካሂዱት የፕሮክሲ ጦርነት የተነሳ ሌላ ዙር ቀውስ በምስራቅ አፍሪካ እና ውጥረት እንዲከሰት ስለማይፈልጉ ከወያኔ ጋር እጅና ጓንት ሆነው ለመስራት አለመቦዘናቸው የሚያመለክተው እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሃገራት ላይ በአሁኑ ሰአት ሊፈጠር የሚችለውን አመጽ እና ችግር መቆጣጠር ይዞ የሚመጣውን ውጤት እርግጠኛ ሆነው ለማወቅ አለመቻላቸው ከወያኔ ጋር እንዲተሳሰሩ አድርጓቸዋል።ምንሊክሳልሳዊ

እንዲሁም ደቡብ ሶማሊያ ላይ ነዳጅ መኖሩን ስካን አድርገው ስላረጋገጡ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ25 አመት በኋላ እንግሊዝ ኤምባሲዋን ሞቃዲሾ የከፈተች ሲሆን ይህን ተከትሎ ከ100 በላይ የብሪታንያ ካምፓኒዎች ካልተረጋጋችው ሶማሊያ ፍቃድ እንደተሰጣቸው ለማረጋገጥ ተችሏል። ይህንን ከሶማሊያ ሊያገኙትን ብሄራዊ ጥቅም ሊያስጠብቅ የሚችለው አገር ቢኖር ወታደሮቹን ለሞት እየገበረ የሚተባበራቸው የወያኔው መንግስት ብቻ ስለሆነ ያላቸውን ሃይል ሁሉ በመጠቀም ሕዝብን በዲፕሎማሲያዊ ቋንቋ በመደለል የአምባገነኖች እድሜ እንዲረዝም ሚናቸውን ይጫወታሉ።

ብቸኛው እና ዋናው ጉዳይ ትግሉ/ጦርነቱ በመሃል እና በዳር አገር ከተፋፋመ ፣ ሕወሓት እና አመራሩ አደጋ ውስጥ መግባት ሲጀምሩ የዛን ወቅት ም እራባውያኑ በሌላው አለም እንደለመዱት ይመጡና አንዳርጋቸውን እንደ ጆከር ካርድ ለመጠቅም ይሞክራሉ። በቃ ወያኔ አንዳርጋቸውን እንዲፈታ እና የተኩስ አቁም ተደርጎ ድርድር እንዲጀመር ያደርጋሉ ከዚህ ውጭ ግን የሃይል ሚዛኑ በወያኔ እጅ ባለበት የመንግስትን ወንበር ተቃዋሚዎች ባላዩበት ሁኔታ ምእራባውያኑ የሚያሰሉት ከወያኔ ጋር ያላቸውን ቁርኝት ነው። ይህንን ለመበጠስ ደሞ የግዴታ የተኩስ ትግል መጀመር አለበት ። ወያኔም ቢሆን የትጥቅ ትግሉ በመሃል አገር እና በዳር አገር ሲስፋፋበት ጭንቀት ውስጥ ስለሚገባ ከአጣብቂኙ ለመውጣት ሲል ያለውን አማራጭ ለመጠቀም ይሞክራል። ወያኔ ደጋፊዎቹን እና ካድሬዎቹን ብእጥቅም ስለገዛቸው ጦርነት ከተስፋፋበት ያለውን ሃይል ሁሉ ወደ ዛው ስለሚያጋድለው ለካድሪዎቹ ጥቅሞች ጊዜ ስለማይኖረው አብዮታዊ መበላላት በፓርቲው ውስት ስለሚፈጠር እድሜውን ማቀጨጭ ከዛም መጣል ይቻላል። መታገል ካልቻልን ባሁኑ አካሄዳችን ወያኔን እንድማንጥለው ማወቅ አለብን።

አንዳርጋቸው የት እንዳለ ባልታወቀበት ሁኔታ ቶርቸሩ ባልቆመበት ሁኔታ ላይ 500 ሚሊዮን እነ ብሪታንያ እየሰጡ ባለበት ሁኔታ ወያኔ እና የየመን መንግስት የሚፈልጉትን ነገር እንዲያደርጉ ቀድመው ላይሰንስ አድርገዋቸውል ለማለት መገመት ብቻ ሳይሆን ያስደፍራል።አስር ጊዜ ወያኔዎችን የሚያጥላላ ነገር ከመጻፍ በየመንገዱ ሰልፍ ከመውታት በጋራ ተሰባስበን ሳንናናቅ እና ከኛ በላይ አዋቂ የለም ብለን ሳናስብ አንዱ ለ አንዱ ዝቅ ብሎ የወያኔን ስልጣን አደጋ ውስጥ የሚከት ከባባድ እንቅስቃሴ ማድረግ ከቻልን በትግላችን ስኬት ምእራብያውያኑን ማሳመን እንደምንችል ማወቅ አለብን። ህዝባችንንም ነጻ ማውጣት እንደምንችል መረዳት ግድ ይላል።#ምንሊክሳልሳዊ

ሰበር ዜና ሽብርተኛው ማን እንደሆነ ዳግም ተረጋገጠ፡፡Accused killer's long terror roots

ሽብርተኛው ማን እንደሆነ ዳግም ተረጋገጠ፡፡ በአሜሪካው የሽብርተኛ ዳታ ቤዝ ውስጥ ስሙ የሚገኘው ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ፡ ዳግም የሽብርተኛ አቀንቃኝ ስለመሆኑ ፎክስ ኒውስ አጋለጠ። በአሜሪካን መንግስት በሽብርተኝነት በጥብቅ ከሚፈለግ የአል ሸባብ አመራር ጋር አቶ መለስ ዜናዊና ተከታዮቻቸው ሲፈራረሙ፡ ሲተቃቀፉ፡ ሲገባበዙ እንደነበር ተጋልጧል። 




የይለፍ ሚስጥር ቁልፍ ሰብሮ መረጃ የሰረቀው ግለሰብ ጥፋተኛ ተባለ

Azeb  Mesfin, wife of Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi
አቶ ዮናስ ካሳሁን የተባለ ግለሰብ የወ/ሮ አኪኮ ስዩምን ኢ-ሜይል አድራሻ የይለፍ ቃል (ፓስወርድ) ያለ ግለሰቧ ፈቃድ ባልታወቀ መንገድ በመጠቀም ግለሰቧ ከተለያዩ ሰዎችና ድርጅቶች ጋር የምታደርገውን የመረጃ ልውውጥ ወደራሱ አድራሻ በመላክ፣ በማጥፋትና ለ3ኛ ወገን አሳልፎ በመስጠት ወንጀል ጥፋተኛ ተባለ፡፡ ግለሰቡ በአሁኑ ሰዓት በፖሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኝ ሲሆን የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት ፍ/ቤቱ ለሰኞ ጠዋት ቀጠሮ ይዟል፡፡ የኦርኪድ ቢዝነስ ግሩፕ ባለቤትና ስራ አስኪያጅ የሆነችው የግል ተበዳይ ወ/ሮ አኪኮ ስዩምን የኤሌክትሮኒክ አድራሻ ባልታወቀ መንገድ አልፎ የግል የመረጃ ልውውጦቿን ወደራሱ አድራሻ መላኩና ለሶስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠቱ በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ መረጋገጡም ታውቋል፡፡ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ዘርፍ የፎረንሲክ ምርመራ ዳይሬክቶሬት ለኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ከኤሌክትሮኒክስ አድራሻ (ኢ.ሜል) መረጃ የመስረቅና የማጥፋት ወንጀል ዙሪያ ሙያዊ ድጋፍ እንዲያደርግለት በጠየቀው መሰረት፤ ተጠርጣሪው ወንጀሉን ለመፈፀም በህገ-ወጥ መንገድ የተበዳይዋን የወ/ሮ አኪኮ ስዩምን የኤሌክትሮኒክ አድራሻና የይለፍ ቃል (ፓስወርድ) ባልታወቀ መንገድ በመጠቀም ግለሰቧ ከተለያዩ ሰዎች እና ድርጅቶች ጋር የምታደርገውን የመረጃ ልውውጥ ወደ ራሱ ከመላኩም በተጨማሪ ኢ/ር ግርማ ገላው ለተባለ ሶስተኛ ወገን መላኩን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ያረጋገጠ ሲሆን ግለሰቧ በተለያዩ ወቅቶች ለተለያዩ የንግድ ስራዎች ከተለያዩ ድርጅቶች ጋር መልእክት የተላላከችበትን ቀናት በአገራችንና በአውሮፓውያን ዘመን ቀመር በግልፅ አስቀምጦ ለፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ዘርፍ የፎረንሲክ ምርመራ ዳይሬክቶሬት ልኳል፡ ከኦርኪድ ቢዝነስ ግሩፕ ሦስት ጠበቆች አንዱ የሆኑትን አቶ ወገኔ ካሳሁንን አነጋግረን በሰጡን ምላሽ፤ ተከሳሽና ተበዳይ ቀደም ሲል የፍቅር ግንኙነት እንደነበራቸውና ግንኙነታቸው መቋረጡን፣ ከዚያ በኋላ የተበዳይዋን የኢሜል ሳጥን በመስበር በርካታ መረጃዎችን እንደሰረቀ በመታወቁ መረጃዎቹን እንዲመልስላት ራሷም በአማላጅም ጠይቃው እንደነበር ጠበቃው ተናግረዋል፡፡ “ተጠርጣሪው መረጃዎቹን እንድመልስልሽ 40 ሚሊዮን ብር ክፈይኝ፤ ያለበለዚያ መረጃውን አልመልስም” ማለቱን የጠቆሙት ጠበቃው፤ ከዚያም ወመረጃዎችን በመያዝ ክስ መመስረቱን ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ “ምስክሮች እንድናቀርብ ፍ/ቤቱ ጠየቀን፤ በምስክርነትም ራሷ ተበዳይና የሰረቃቸውን የኢ-ሜይል መረጃዎች እንዲመልስላት አማላጅነት የላከቻቸው ሰዎች ቀርበው የሚያውቁትን አስረዱ” ያሉት ጠበቃው፣ ከዚህ ሁሉ ሂደት በኋላ ተጠርጣሪው በበቂ ሁኔታ መከላከል ባለመቻሉና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲም ሆነ ምስክሮች በበቂ ሁኔታ ጥፋተኝነቱን በማረጋገጣቸው ባለፈው ረቡዕ ፍ/ቤቱ ጥፋተኛ ብሎታል ብለዋል፡፡ ፍ/ቤቱ የቅጣት ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ ተጠርጣሪው ማረሚያ ቤት እንዲቆይ ያዘዘ ሲሆን የቅጣት ውሳኔውን ለመስጠት ለሰኞ ጠዋት 3፡30 ሰዓት ቀጠሮ ይዟል፡፡ “በአገራችን የግለሰቦችን የመረጃ ሳጥን በህገ-ወጥ መንገድ በመስበር ጥፋተኛ የተባለ ሰው ስሰማ የመጀመሪያዬ ነው” ያሉት የኦርኪድ ቢዝነስ ግሩፕ ጠበቃ፤ እነዚህ ወንጀሎች በአገራችን አዲስ ናቸው፤ በ1949 የወጣው የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ላይ አልተካተቱም፤ በአዲሱ ላይ ግን ተካተው ይሄው እየሰሩ ነው ሲሉ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ ኦርኪድ ቢዝነስ ግሩፕ በኮንስትራክሽን ዘርፍ፣ በውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ፣ በአስጐብኚ ድርጅትና ማሽነሪዎችን በማከራየት እንዲሁም በትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማራ ኩባንያ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡
Source : Addis Admas

Freitag, 24. Oktober 2014

ጄነራል ኃይሉ ጎንፋ ያሉበት የኦነግ ከፍተኛ አመራር ጄነራል ከማል ገልቹን ከስልጣን ማንሳቱን አስታወቀ -

kemal_gelchi በአስመራ የሚገኘውና በጀነራል ከማል ገልቹ ይመራ የነበረው ኦነግ መሪውን ከስልጣን ማንሳቱን ዘ-ሐበሻን ጨምሮ በተለያዩ ሚዲያዎች በበተነው መግለጫ አስታወቀ።
በዶ/ር ኑሮ ደደፎ፣ በምክትላቸው ብርጋዴር ጄነራል ሃይሉ ጎንፋና በአቶ ዳባ ጉተማ በኩል የበለጠ መረጃ ታገኛላችሁ በሚል የኦነግ ከፍተኛ አመራር ባወጣው መግለጫ ብርጋዴር ጀነራል ከማል ገልቹ ከስልጣን እንዲነሱ የተደረገበትን ምክንያት አብራርቷል። ዘ-ሐበሻ መግለጫውን ኦነግ የሕግ ጉዳዮችና የውጭ ጉዳዮች ኃላፊ ከዶ/ር ኑሮ ደደፎ ለማረጋገጥም ችላለች።
በሌላ በኩል ከስልጣን ተነሱ የተባሉት ጀነራል ከማል ገልቹም እንዲሁ በበኩላቸው መግለጫ ሊሰጡ ይችላሉ እየተባለ ሲሆን ዘ-ሐበሻ እርሳቸውን ለማግኘት ያደረገችው ጥረት አልተሳካም።
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/35658#sthash.8mJOdJ4V.LXZa258n.dpuf

ሰበር ዜና የአ.አ ከንቲባ ጽ/ቤት ጠባቂ ፖሊሶች ተታኮሱ_ ነገረ ኢትዮጵያ








የአዲስ አበባ መስተዳደር ማዘጋጃ ቤት (ከንቲባ ጽ/ቤት) ውስጥ የሚሰሩ ፖሊሶች ዛሬ በግምት ከቀኑ 6 ሰዓት አካባቢ እርስ በእርሳቸው መታኮሳቸውን አስተዳደሩ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡
ፖሊሶቹ የተታኮሱት በከንቲባው ጽ/ቤት ውስጥ የሚሰሩ ፖሊሶች በነበራቸው ግምገማ በተፈጠረ አለመግባባት እንደሆነ ታውቋል፡፡ ፖሊሶቹ የተታኮሱት ከስብሰባው እንደወጡ እንደሆነም ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡
በከንቲባ ጽ/ቤት ፖሊሶች በተታኮሱበት ወቅት የአትክልት ተራን ጨምሮ በአካባቢው የሚገኘው ማህበረሰብ በድንጋጤ ውስጥ እንደነበርና አብዛኛው ከተኩሱ በኋላ ወደ አስተዳደሩ ቢሮ በማቅናቱ በከንቲባው ጽ/ቤት አካባቢ በርከት ያለ ህዝብ እንደሚገኝ ምንጮቻችን ጠቅሰዋል፡፡

ፖሊሶቹ በተታኮሱበት ወቅት ገላጋዮች መሃላቸው በመግባታቸው በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለና ይህም በግምገማው ወቅት ለገላጋይ ያበቃ አጨቃጫቂ ጉዳይ እንደነበራቸው ያሳያል ተብሏል፡፡