Netsanet: Februar 2015

Samstag, 28. Februar 2015

ሰበር ዜና: የወያኔ ሰላይ ከሆላንድ ተባረረ!

ከመሃል ያለው ኢዛና (እስራኤል ገደቡ) ለ'ኢንቨስትመንት" አዲስ አበበ ያለፈው ወር በሄደ ጊዜ
ሂሩት መለሰ – ከሮተርዳም
ሮተርዳም፣ ጥቅምት 28 ቀን 2015 – በስደት ስሙ አለማየሁ ስንታየው በመባል የሚታወቀው የህወሃት ሰላይ ከኔዘርላንድስ ተባረረ። አለማየሁ ስንታየሁ ቋሚ ነዋሪ ከነበረበት ከኔዘርላንድስ እንዲባረር የተደረገው በዚያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በከፈቱበት የስለላ ክስ መሆኑም ታውቋል።
የሮተርዳም ከተማ ፍርድ ቤት በአለማየሁ ላይ የተመሰረተውን የስለላ ክስና ማስራጃ ለረጅም ጊዜ ሲመረምር ከቆየ በኋላ የግለሰቡ የመኖርያ ፈቃድ እና ቤት እንዲነጠቅ፣ የሆላንድን ምድርም በአስቸኳይ ለቆ እንዲወጣ ውሳኔ አስተላልፏል። ከሆላንድ የምመራ ቡድን እንደተረዳነው ከሆነ – የግለሰቡ ቤት ሲፈተሽ ወያኔ የሰጠው እውነተኛ መታወቂያ እና በርካታ የስለላ ሰነዶች ተገኝተውበታል። በእርዳታ ስም የተቋቋመለት ድርጅትም ተፈትሾ ማስረጃዎች እንደተገኙ ለማወቅ ተችሏል።
alemayehu-sentayehu
ይህ ሰው ትክክለኛ ስሙ ዘለቀ ፎላ ይባላል። በደርግ ጊዜ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባል ሆኖ ለረጅም አመታት አገልግሏል። ወያኔ ስልጣን ሲቆጣጠር ለፖለቲካ ተሃድሶ አዋሳ ደቡብ ጦር ቅጥር ግቢ ተላከ። በተሃድሶ በነበረበት ጊዜ ቁጥራቸው ብዙ የሆኑ የሰራዊቱ አባላትን ለወያኔ በማጋለጥ ታማኝነቱን ሲያሳይ እንደነበር የዚህ ዜና ዘጋቢ እማኝ ነው። የበርካታ ኢትዮጵያውያን ደም በእጁ ያለው አለማየሁ ከተሃድሶው ከወጣ በኋላ እስራኤል ገደቡ (የፓልቶክ ስሙ ኢዛና) ከተባለ ወታደር ጋር በመሆን የሰላም ተጓዥ ነኝ ብሎ በመገናኛ ብዙሃን ሲታይ ነበር። አለማየሁ እና ኢዛና በየሃገሩ እየዞሩ ስለ አዲሱ ስርዓት መልካምነት ሲሰብኩ ከረሙ። ከዚያም አስመራ ድረስ ተልከው የሻእቢያውን መሪ ኢሳያስ አፈወርቂን በወታደሩ ስም ይቅርታ ጠይቀዋል።
አለማየሁ እና ኢዛና ለወያኔ በሰሩት ውለታ ሆላንድ ገብተው እንዲቀሩ ተደረገ። ይህም የተደረገበት ምክንያት በአውሮፓ የሚኖሩ ኢዮጵያውያንን ተቃዋሚ በመምሰልና በረቀቀ መንገድ እንዲያበጣብጡና እንዲሰልሉ ነው።
በሆላንድ ሃገር የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቆ ለወያኔ ቡድን የስለላ ስራ መስራት ወንጀል ነው። አለማየሁ የሆላንድ ዜግነት ቢኖረው ኖሮ ቅጣቱ የከፋ ይሆን እንደነበር ጉዳዩን እየተከታተሉ ያሉ የህግ ባለሙያዎች ተናግረዋል።
የአለማየሁ መባረር በተሰማ ግዜ በሮተርዳም ያሉ የህወሃት ደጋፊዎች የአቤቱታ ደብዳቤ በመጻፍ ፊርማ ማሰባሰብ ቢጀምሩም ሊሳካላቸው አልቻለም። የአቤቱታ ደብዳቤው ግለሰቡ እዚህ የተወለዱ ሁለት ለጆቹን እየመጣ እንዲጎበኝ ይፈቀድለት የሚል ነበር።
አለማየሁ ስንታየሁ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከሆላንድ ተባረረ። ኢዛና ግን አሁን የተቃዋሚ ጭንብሉን አውልቆ በግልጽ ወያኔ መሆኑን መናገር ጀምሯል። ኢዛና የሆላንድ ዜግነት ቢኖረውም በሆላንድ ሃገር ስራ ሰርቶ አያውቅም። የቀንና ማታ ስራው በፓልቶክ ላይ ነው። ባለፈው ወር ኢትዮጵያ የተጓዙ ዲያስፖራ ኢንቨስተሮችን እየመራ በቴሌቭዥን መግለጫ ሲሰጥ አይተነዋል። ይህ ትርኢት የወያኔ ኢንቨስተሮች በጨበጣ እንደሚንቀሳቀሱም ያሳየናል።

ኢህአዴግ 98ቢሊዮን ብር ነጠፈበት!! “ታላቅ ሥራ ተሰርቷል! እናመሰግናለን!” ኦባንግ

http://www.goolgule.com/eprdf-lost-98-billion-birr/

Screenshot - 28_02 002
ኢህአዴግ በዓለም ባንክ በኩል ከእንግሊዝ የዓለምአቀፍ ልማት ተራድዖ መ/ቤት ሊለግስለት ታቅዶ የነበረው 4.9 ቢሊዮን ዶላር (98ቢሊዮን ብር) የገንዘብ ድጋፍ ነጠፈበት፡፡ አቶ ሬድዋን አልነጠፈብንም ይላሉ፡፡ ኦባንግ ሜቶ በበኩላቸው “የታላቅ ሥራ ውጤት ነው፤ እናመሰግናለን” ብለዋል፡፡
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ጥቅምት 2፤2005 (October 12, 2012) “ኢህአዴግ በ600 ሚሊዮን ዶላር አጣብቂኝ ውስጥ ገባ!! ብያኔው ከጸና ኪሣራው በቢሊዮን ዶላር ሊደርስም ይችላል!” በሚል ርዕስ የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ያካሂድ ስለነበረው ፕሮግራም በዘገበበት ወቅት የሚከተለውን ዜና አትሞ ነበር፡- “ከ1998ዓም ጀምሮ የመሠረታዊ አገልግሎት ጥበቃ ፕሮግራም (Protection of Basic Services “PBS Program”) በሚል በአራት ተከታታይና ሁለት ተጨማሪ የገንዘብ ድጎማ የሚደረግባቸውን ፕሮግራሞች የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ ይህ መሠረታዊ የሆኑ አገልግሎቶችን ለማሟላት ተወጥኖ የሚካሄድ ፕሮጀክት በትምህርት፣ በጤና፣ በእርሻ፣ በንጹህ ውሃ አቅርቦት፣ በገጠር መንገድ ሥራ፣ ወዘተ መስኮች ላይ እንዲውል (PBS I, PBS I-AF (Additional Financing), PBS II, PBS 11-AF, PBS-Social Accountability Program and PBS III) በማለት በተለያዩ ደረጃዎች ለተከፋፈለው ኦፐሬሽን ማስፈጸሚያ የሚውለው ገንዘብ ከ13ቢሊዮን ዶላር የሚበልጥ ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ ከፍተኛው የዓለም ባንክ ድርሻ 2ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የተቀረው በሌሎች ለጋሽ መንግሥታት እና ድርጅቶች የሚሸፈን ነው፡፡ PBS III የተሰኘውን በሦስት ንዑሳን ፕሮግራሞች የተከፋፈለውን ፕሮጀክት ለማስፈጸም በአጠቃላይ የሚፈጀው 6.3ቢሊዮን ዶላር በላይ ነው፡፡”
ይህ ለመሠረታዊ ልማት እንዲውል በዓለም ባንክ በኩል የሚሰጠውን ገንዘብ የሚደጉሙት ምዕራባውያን አገራት ሲሆኑ አንዷ ተጠቃሽ አገር እንግሊዝ ናት፡፡ ሆኖም ኢህአዴግ ከምዕራባውያን በዓለም ባንክ በኩል የሚያገኘውን ገንዘብ ለራሱ የፖለቲካ መጠቀሚያነት እያዋለው መሆኑ ለዓለም ባንክ ተደጋጋሚ መረጃዎች ሲቀርቡ ቆይተዋል፡፡ በተለይ ሟቹ መለስ በቀጥታ በሰጡት ትዕዛዝ 424 የአኙዋክ ተወላጆች ከተገደሉ በኋላ ኢህአዴግ በቦታው ያሰማራው የመከላከያ ሠራዊት በሥፍራው የሚኖሩትን ከመኖሪያ ቀያቸው በማፈናቀል እምቢ ያሉትን በግድ በማስነሳት፣ በመግደል፣ አስገድዶ በመድፈር፣ በማሰቃየት፣ ወዘተ ግፍ ሲፈጽም መቆየቱ በተለያዩ ዓለምአቀፋዊ ዕውቅና ባገኙ ዘገባዎች ሲነገር ቆይቷል፡፡ የዓለም ባንክ ለመሠረታዊ ልማት በማለት የሚሰጠው ገንዘብ ኢህአዴግ ወታደሮቹን የግፍ ሥራ ላይ በማሰማራት ደመወዝ የሚከፍልበት መሆኑን በመጥቀስ ወደ ኬኒያ የተሰደዱ የክልሉ ነዋሪዎች አቤቱታ አቅርበው እንደነበር ጎልጉል በወቅቱ የዘገበው ዜና ነበር፡፡ ““ኢህአዴግ አንገቱን ታንቋል”፤ዓለም ባንክ ርምጃ ለመውሰድ ጫፍ ደርሷል” በሚል ርዕስ የተጻፈውን ዜና ለማንበት እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡http://www.goolgule.com/world-bank-and-eprdf/
ከዚሁ ጋር በተያያዘ “ሚስተር ኦ” በመባል የሚጠሩት አኙዋክ ተወላጅ ኢህአዴግ የዕርዳታ ገንዘብ ለሰብዓዊ መብት ረገጣና ለራሱ የፖለቲካ መጠቀሚያነት እንዳዋለው በመጥቀስ የእንግሊዝ መንግሥት ከግብር ከፋይ ዜጎቹ የሚያገኘውን ገንዘብ አምባገነንነት እየደገፈበት መሆኑን በተለይም የዓለምአቀፍ ልማት ተራድዖ መ/ቤቱ ተጠያቂ ስለሆነ ከዚህ እንዲታቀብ ክስ መመሥረታቸው ይታወቃል፡፡ የክሱ ሒደት እየተካሄደ ባለበት ባሁኑ ወቅት ሚስተር ኦ በተደጋሚ እንደመሰከሩት ኢህአዴግ ነዋሪዎችን በግዳጅ ከቀያቸው በማፈናቀል የሚያካሂደው የግዳጅ ሰፈራና የመንደር ምሥረታ ሕገወጥ መሆኑ በመቃወማቸው በተደጋጋሚ ከፍተኛ ድብደባ እንደረሰባቸው ተናግረዋል፡፡ ብዙዎች ለአካላዊ ሥቃይ ደርሶባቸዋል፣ ሴቶች ክብረንጽህናቸው ተደፍሯል፣ አዛውንትና ህጻናት ለአሰቃቂ መከራ ተዳርገዋል፤ ይህንንም እርሳቸው እንዳዩ ሚስተር ኦ ይመሰክራሉ፡፡
የሚስተር ኦ የፍርድቤት ጉዳይ ወደ ውሳኔ ሊደርስ ባለበት ወቅት የልማት መ/ቤቱ ይህንን ዓይነት ውሳኔ መውሰዱ ከፍርድ ቤቱ ጉዳይ ጋር የሚያያዝ እንደሆነ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ይናገራሉ፡፡ የልማት ተራድዖ መ/ቤቱ ቃል አቀባይ ግን የመ/ቤታቸው ውሳኔ ከሚስተር ኦ የፍርድቤት ጉዳይ ጋር ያልተያያዘ እንደሆነ መናገራቸውን የእንግሊዙ ዘጋርዲያን ጋዜጣ ዘግቧል፡፡ መ/ቤቱ ለዚህ ውሳኔ የደረሰው ኢትዮጵያ “የዕድገት ስኬት” እያስመዘገበች በመምጣቷ የመሠረታዊ ልማት አገልግሎት የገንዘብ ዕርዳታ የማያስፈልጋት በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡
ይህ መጠኑ እጅግ ከፍተኛ የተባለውና ለኢህአዴግ ንጹህ የውጭ ምንዛሪ ምንጭ የሚያስገኝ ገንዘብ እንደነጠፈበት መሰማቱን አስመልክቶ ጋዜጣው የኢህአዴግ ፅ/ቤት ሃላፊ የሆኑትን ሬድዋን ሁሴን በጠየቃቸው ወቅት የመለሱት አልነጠፈብንም የሚል እንድምታ ያለው ነው፡፡ “እነርሱ ያሉት ዕርዳታውን አንሰጥም ወይም እናቆማለን ሳይሆን ዕርዳታ አሰጣጡ እንደገና ይዋቀራል ነው” በማለት ሬድዋን ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡ ሆኖም 4.9 ቢሊዮን ዶላር (98ቢሊዮን ብር) ዕርዳታ ለመስጠት ከዓለምባንክ ጋር ስምምነት የነበረው የእንግሊዝ የልማት ተራድዖ መ/ቤት “ኢትዮጵያ አድጋለች” በማለት በ2015/2016 በፓውንድ 256ሚሊዮን ብቻ (5በመቶ) ዕርዳታ ለመስጠት መወሰኑን የኢህአዴግ ጽ/ቤት ሃላፊው ሬድዋን ሁሴን አላብራሩም፡፡
ኢህአዴግ ለዕርዳታ የሚሰጠውን ገንዘብ ዜጎችን ለማሰቃየት፣ ወታደር ለመቀለብ፣ ወዘተ እንደሚጠቀምበት በተደጋጋሚ ዘገባዎች እና ማስረጃዎች ሲወጡበት የከረመ ቢሆንም ማስረጃዎቹን ተከትሎ የዓለም ባንክ በዕርዳታ አሠጣጡ ላይ አንዳች ውሳኔ እንዳያደርግ ብዙ ሲደክም ቆይቷል፡፡ በዚህም ምክንያት ጉዳዩ ውሳኔ ሳይሰጥበት እንዲስተጓጎል በማድረግ ለሁለት ዓመታት ያህል እንዲጓተት ማድረጉን ከጉዳዩ ጋር ቅርበት ያላቸው ወገኖች ይመሰክራሉ፡፡
ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ኦባንግ ሜቶ ጉዳዩን ገና ከጅምሩ የሚያውቁትና ድርጅታቸው ለዓመታት ሲሰራበት የነበረ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ በመሆኑንም ይህንን የእንግሊዝ የልማት ተራድዖ መ/ቤት ውሳኔ የጋራ ንቅናቄያቸው ከደጋፊዎቹ ጋር በመሆን ያገኘው ድል እንደሆነ በፌስቡክ ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል፡፡ “ገና ከጅምሩ ከጋራ ንቅናቄያችን ጋር በመሆን ይህንን ሥራ በመደገፍ የተባበራችሁንን ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ፤ ታላቅ ሥራ ተሰርቷል፤ እናመሰግናለን” ብለዋል “ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ ሜቶ፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ አቶ ኦባንግ በተለይ ከጎልጉል ለቀረበላቸው አጭር ጥያቄ በሰጡት አስተያየት የጋራ ንቅናቄያቸው ደስታውን የገለጸው የልማት ገንዘብ በመቋረጡ ሳይሆን በልማት ስም የሚሰጠው ዕርዳታ ለሰብዓዊ መብት ረገጣ በመዋሉና ለዚህም ደግሞ ከበቂ በላይ ማስረጃ ድርጅታቸው ያለው በመሆኑ ነው፡፡ “አገር ብትለማ የሁሉም ደስታ ነው” ያሉት ኦባንግ አገርን በማልማት ሽፋን ደጋፊና ተቆርቋሪ የሌላቸውን ንጹሃን መበደልና የመኖር መብታቸውን መንፈግ ግን በየትኛውም መልኩ እርሳቸውም ሆነ አኢጋን የሚቀበለው እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡
ኢህአዴግ በቅርቡ አካሂዳለው ለሚለው ምርጫ እንደ ዕቁብ ዕጣ በማውጣትና በማስወጣት “አልደረሳችሁም” እያለ የተቀናቃኝ ፓርቲ አመራሮችን ከምርጫ እያስወገደ ባለበት፤ ሌሎችንም ሕጋዊ አይደላችሁም እያለ በተለጣፊ ድርጅት በማስበት ኅልውናቸውን እያሳጣ ባለበት ባሁኑ ወቅት በዜጎቹ ላይ የሚያካሂደውን መረን የለቀቀ የመብት ገፈፋ ለሥልጣን ያበቁትን ምዕራባውያንን ያስደሰተ እንዳልሆነ ይነገራል፡፡ የአውሮጳ ኅብረት ምርጫውን አልታዘብም ከማለቱ በተጨማሪ በሚዲያ ላይ የተጫነው አፈና በዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ድርጅት ይፋ ከሆነ ወዲህ ማነቆው በኢህአዴግ ላይ እየከረረ መምጣቱን ያሳያል፡፡ ኢህአዴግን ለሥልጣን ከማብቃት አልፋ ነፍጥ አንጋቢዎቹን የህወሃት መሪዎች ጸጉርና ጺም ከርክማ፤ ልብስ አልብሳ፤ ቋንቋ አስተምራ፤ የከተማ አኗኗር እንዴት እንደሆነ አሠልጥና፣ ቶሎ ባይገባቸውም ፕሮቶኮል አስተምራ፣ እስካሁንም ተንከባክባ እዚህ ድረስ ያቆየቻቸው እንግሊዝ እንዲህ ያለውን የውጭ ምንዛሪ ምንጭ ስታደርቅ “ቀጣዩስ ምን ይሆን?” የሚል ጥያቄ እንዲነሳ አድርጓል፡፡ “ምዕራባውያን መግደልም ማንሳትም ያውቁበታል” በማለት አስተያየት የሚሰጡ ወገኖች እንደሚሉት ቀጣዩ የኢህአዴግ ጉዞ በከፍተኛ ሁኔታ ለህወሃት ሲቀጥል ለኢህአዴግ አስጊ ከመሆን ባሻገር በውጭ ምንዛሪ እጥረት በየጊዜው የሚፈጠረውን ግሽበት በዕርዳታ ገንዘብ የሚያስተካክለው ኢህአዴግ እንዲህ ያለው የገንዘብ ማዕቀብ ክፉኛ ያነጥፈዋል ሲሉ ግምታቸውን ይሰጣሉ፡፡ ሙስናው መረን በለቀቀባት አገር ከሕዝብ እየተዘረፈ በተለያዩ አገራት ባንኮች በውጭ ምንዛሪ የሚከማቸውን ገንዘብ በሚካፈሉትም ላይ የድርሻ ቅነሳ የማስከተሉ ጉዳይ አብሮ የሚታይ እንደሆነ ይነገራል፡፡
ከዚህ ዜና ጋር ተያያዥነት ያለውን ጥቅምት 2፤2005 (October 12, 2012) ያተምነውን ዜና ከዚህ በታች እንደሚከተለው እንደገና አትመነዋል፡፡
ኢህአዴግ በ600 ሚሊዮን ዶላር አጣብቂኝ ውስጥ ገባ!!
ብያኔው ከጸና ኪሣራው በቢሊዮን ዶላር ሊደርስም ይችላል!
ኢህአዴግ ከዓለም ባንክ ያገኘውን 600 ሚሊዮን ዶላርና በተመሳሳይ ፕሮጀክት ወደፊት ሊያገኝ የሚችለውን ከፍተኛ ገንዘብ በተመለከተ አደጋ ውስጥ መውደቁ ተሰማ። ኢንስፔክሽን ፓናል (Inspection Panel – IP) የተሰኘ ተቋም ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያመለክተው ኢህአዴግ የቀረበበት ውንጀላ ከተረጋገጠ የሚያጣው ገንዘብ በቢሊዮን ዶላር እንደሚደርስ ታውቋል። ይፋ የሆነውን መረጃ አስመልክቶ ከኢህአዴግ ወገን እስካሁን በይፋ የተሰጠ ምላሽ የለም።
ግፍ የሚፈጽሙ መንግስታትን፣ በልማት ስም የሰብዓዊ መብት ጥሰት የሚፈጽሙ ወንጀሎችን መረጃዎችን በስፍራው በመገኘትና ከመሠረቱ ዘልቆ በመግባት አደራጅቶ ተጠያቂ የሚያደርገው ኢንክሉሲቭ ዴቨሎፕመንት ኢንተርናሽናል Inclusive Development International (IDI) ከሰለባዎቹ ውክልና ተሰጥቶታል። ተቋሙም በውክልናው መሰረት ለኢንስፔክሽን ፓናል በዝርዝር የሰለባዎቹን በደል በማተት አሳውቋል።
የኢህአዴግ መከላከያ ሠራዊት የሚያደርሰውን እስራት፣ ግርፋት፣ አስገድዶ መድፈር፣ ከመኖሪያ ቦታ ማፈናቀል፣ የግዳጅ ሰፈራ ወዘተ በማምለጥ ወደ ኬንያ የተሰደዱ የጋምቤላ ነዋሪዎች ይህ ሁሉ ግፍ የሚፈጽምባቸው የኢትዮጵያ መንግሥት በልማት ስም ከዓለም ባንክ በሚያገኘው የዕርዳታ ገንዘብ በመሆኑ ለባንኩ በላኩት የአቤቱታ ደብዳቤ አመልክተዋል።
አቤቱታውን መሠረት በማድረግ የሚደረገው ምርመራ ውጤት ይፋ ሲሆን፣ በሌሎች አገሮች እንደተደረገው በዕርዳታ ስም የሚገኝን ገንዘብ ኢህአዴግ ለፖለቲካ ተግባር መጠቀሙ ሲረጋገጥ፣ በመስከረም ወር መጀመሪያ አካባቢ ከዓለም ባንክ ተፈቅዶ የነበረው 600ሚሊዮን ዶላር ሊከለከል ይችላል፡፡
የዛሬ ዘጠኝ ዓመት አካባቢ በሟቹ ጠ/ሚ/ርና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ መለስ ዜናዊ ቀጥተኛ ትዕዛዝ በጋምቤላ ክልል በተለይ የተማሩ ወንዶች ላይ በማተኮር 424 ንጹሐን የአኙዋክ ተወላጆች በተገደሉበት ወቅት በሺዎች የሚቆጠሩት ወደ ጎረቤት አገር ኬንያ መሰደዳቸው ይታወሳል፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ክልሉ ሰላም የለም፡፡ በየጊዜውም የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ሲካሄዱበት ቆይቷል፡፡ በተለይም ለም የሆነውን እጅግ ሰፋፊ መሬት ለውጪ ባለሃብቶች በሳንቲም በመሸጥ ላይ የሚገኘው የኢህአዴግ አገዛዝ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በቀድሞው የደርግ ዘመን ሲካሄድ ከነበረው ባለፈ መልኩ እጅግ በሚያሰቅቅ ሁኔታ በመንደር ምስረታና አስገድዶ የማስፈር ፖሊሲ ከመኖሪያ ቀዬ የማፈናቀል ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን የኦክላንድ ተቋም፣ ሂውማን ራይትስ ዎች፣ … የመሳሰሉ ድርጅቶች ያወጧቸው ዘገባዎች ይጠቁማሉ፡፡
ከ1998ዓም ጀምሮ የመሠረታዊ አገልግሎት ጥበቃ ፕሮግራም (Protection of Basic Services “PBS Program”) በሚል በአራት ተከታታይና ሁለት ተጨማሪ የገንዘብ ድጎማ የሚደረግባቸውን ፕሮግራሞች የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ ይህ መሠረታዊ የሆኑ አገልግሎቶችን ለማሟላት ተወጥኖ የሚካሄድ ፕሮጀክት በትምህርት፣ በጤና፣ በእርሻ፣ በንጹህ ውሃ አቅርቦት፣ በገጠር መንገድ ሥራ፣ ወዘተ መስኮች ላይ እንዲውል (PBS I, PBS I-AF (Additional Financing), PBS II, PBS 11-AF, PBS-Social Accountability Program and PBS III) በማለት በተለያዩ ደረጃዎች ለተከፋፈለው ኦፐሬሽን ማስፈጸሚያ የሚውለው ገንዘብ ከ13ቢሊዮን ዶላር የሚበልጥ ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ ከፍተኛው የዓለም ባንክ ድርሻ 2ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የተቀረው በሌሎች ለጋሽ መንግሥታት እና ድርጅቶች የሚሸፈን ነው፡፡ PBS III የተሰኘውን በሦስት ንዑሳን ፕሮግራሞች የተከፋፈለውን ፕሮጀክት ለማስፈጸም በአጠቃላይ የሚፈጀው 6.3ቢሊዮን ዶላር በላይ ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ የባንኩ ድርሻ የሆነውን 600ሚሊዮን ዶላር ቦርዱ መስከረም 5ቀን 2005ዓም አጽድቋል፡፡
በአስገድዶ ማስፈር፣ መንደር ምስረታና ሌሎች በርካታ የሰብዓዊ መብቶቻቸው የተጣሱባቸው በኬንያ የሚገኙ ሦስት የአኙዋክ ስደተኞች ተወካይ ድርጅቶች በሰሜን አሜሪካ ከሚገኙ ሌሎች የሰብዓዊ ድርጅቶች ጋር በመሆን ባንኩ ሊሰጥ የወሰነውን ገንዘብ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጥቅም ከመዋል ይልቅ ለኢህአዴግ የፖለቲካ ዓላማ ማስፈጸሚያ እየዋለ መሆኑን በመጥቀስ ለባንኩ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጂም ዮንግ ኪም መስከረም 6፤ 2005ዓም ደብዳቤ ልከዋል፡፡ በጥያቄያቸውም መሠረት በዓለም ባንክ በኩል ወደ ኢትዮጵያ የሚፈሰው ገንዘብ “በልማት ስም የኢትዮጵያ መንግሥት በጋምቤላ ክልል ለሚያካሂደው የመንደር ምስረታ እየዋለ ነው” በማለት ይከሳል፡፡ ሲቀጥልም የአኙዋክ ሕዝብ ለዘመናት ከኖረበት መንደር በማፈናቀል “የተሻለ አገልግሎት ይሰጣችኋል” በማለት በግድ የማስፈር ተግባር እየተፈጸመ ሲሆን “የተባለው አገልግሎትም ሆነ ለእርሻ የሚሆን በቂ ቦታ እንዲሁም ለከብቶች የሚበቃ የግጦሽና የውሃ ቦታ የላቸውም” በማለት ሰፈራውን የተቃወሙ ሁሉ እጅግ ከፍተኛ የሆነ የሰብዓዊ መብት ረገጣ እየደረሰባቸው እንደሚገኝ ጠቁሟል፡፡ ይህንን ግፍ የሚፈጽሙት ደግሞ የዓለም ባንክ ለመሠረታዊ አገልግሎት ጥበቃ ፕሮግራም (Protection of Basic Services “PBS Program”) ስም ለልማት እንዲውል ከሚሰጠው የዕርዳታ ገንዘብ በመንግሥት ተቀጥረው ደመወዝ የሚከፈላቸው ሠራተኞች መሆናቸውን ገልጾዋል፡፡ ይህንን ጉዳይ ከዓለም ባንክ ጋር እንዲነጋገሩላቸው Inclusive Development International (IDI) የተባለውን ድርጅት መወከላቸውን አስታውቀዋል፡፡ (የደብዳቤው ሙሉ ቃል እዚህ ላይ ይገኛል)
ተመሳሳይ ጉዳዮችን በዓለምአቀፍ ደረጃ በመከታተልና በማስፈጸም የታወቀው IDI በመስከረም ወር አጋማሽ ላይ ጉዳዩ በቀጥታ ለሚመለከተው የመልሶ ማቋቋምና ልማት ዓለምአቀፍ ባንክና (International Bank for Reconstruction and Development (IBRD)) የዓለምአቀፍ ልማት ማኅበር (International Development Association (IDA)) ሥር ለሚገኘው የኢንስፔክተር ፓናል ባለ 18ገጽ ደብዳቤ ጽፏል፡፡ (የደብዳቤው ሙሉ ቃል እዚህ ላይ ይገኛል) ይህ የኢንስፔክተር ቡድን ከፍተኛ ሥልጣን ያለው መ/ቤት ሲሆን የዓለም ባንክ የሚሰጠውን ገንዘብ በትክክለኛ ቦታ ላይ አለመዋሉን በመጥቀስ ክስ የሚያቀርቡ ወገኖችን ጉዳይ በመከታተልና ቦታው ድረስ የራሱን ምርመራ በማካሄድ ውጤቱ ተግባራዊ እንዲሆን የባንኩን እጅ የማስጠምዘዝ ዓቅም ያለው እንደሆነ ከዚህ በፊት ያካሄዳቸው የምርመራ ውጤቶች ይጠቁማሉ፡፡
ይህ የመርማሪ ቡድን የቀረበለትን አቤቱታ መቀበሉንና በጉዳዩ ላይ የማንም ተጽዕኖ የማይደረግበትን የራሱን ምርመራ እንደሚያደርግ ከትላንት በስቲያ ባወጣው ባለ 8ገጽ መግለጫ ላይ አሳውቋል፡፡ ይህ የአቤቱታ ፋይል ቁጥር የተሰጠው ጉዳይ በግልባጭ ለባንኩ ፕሬዚዳንትና ለከሳሽ ተወካይ ድርጅት (IDI) እንዲደርስ ተደርጓል፡፡(የደብዳቤው ሙሉ ቃል እዚህ ላይ ይገኛል)
የጎልጉል የሰሜን አሜሪካ ዘጋቢ ባጠናከረው መረጃ መሠረት ቡድኑ ከያዝነው ዓመት የጥቅምት አጋማሽ በኋላ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ያቀናል። ቡድኑ ስደተኞቹ የሚገኙባቸውን፣ እንዲሁም ጉዳዩን በሚመለከት አስፈላጊ የሚላቸውን ቦታዎችና ግለሰቦች ሙሉ በሙሉ ያነጋግራል። ለስራው መሳካት የሚሆነውን ሁሉ በሚፈለግበት ቦታ በመገኘት በግንባር እንደሚያከናውን ለማወቅ ተችሏል።
በተለያየ ጊዜ ኢህአዴግ የሚፈጽመውን ግፍና በደል በማደራጀት ሥርዓቱ ላይ ከትጥቅ የጠነከረ ትግል ማካሄድ እንደሚቻል አስተያየት ሰጪዎች ተናግረዋል:: አያይዘውም በመላው አገሪቱ የሚፈጸመውን የሰብአዊ መብት ረገጣና የመብት ጥሰት በማሰባሰብ የኢህአዴግን የገንዘብ ምንጭ የማድረቅ፣ ብሎም በእርዳታ ገንዘብ የሚገነባቸውን የአፈና ተቋማት ማስለል እንደሚቻል አስታውቀዋል። ይህንን ታላቅ ስራ የሰሩትን አካላት ልምዳቸውን ለሌሎች በማካፈል አስፈላጊውን ስራ ሊሰሩ እንደሚገባም አሳስበዋል። (ፎቶ: ዘጋርዲያን)
***************************************
(http://www.goolgule.com/)

Freitag, 27. Februar 2015

አብዛኞቹ የመንግሰት ጋዜጠኞች የኢህአዴግ አባላት መሆናቸውን መረጃዎች አመለከቱ

የካቲት ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመንግስት የመገናኛ ብዙሃን ውስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ ጋዜጠኞች አብዛኞቹ የኢህአዴግ አባላት መሆናቸውን ኢሳት በደረሰው የአባላት ስም ዝርዝርና የስራ ድርሻ ሰነድ ለማረጋገጥ ችሎአል።

በቀድሞው ኢቲቪ በአዲሱ አጠራሩ ኢቢሲ እና በኢትዮጵያ ሬዲዮ  ስር የሚሰሩ ዳይሬክተሮች፣ የዜና አዘጋጆች፣ የወቅታዊ ዘገባ አቀናባሪዎች፣ የስፖርት ጋዜጠኞች ፣ የካሜራ ባለሙያዎች፣ ቴክኒሻኖችና የተለያዩ የድጋፍ ሰራተኞች የህወሃት፣ የብአዴን፣ ኢህዴድ ወይም የደህዴግ አባላት መሆናቸው በሰነዱ ላይ በዝርዝር ተቀምቷል። ጋዜጠኞቹ የኢህአዴግን ፖሊስ ለህዝብ ከማስተዋወቅ ጋር በተያያዘ በየጊዜው በተደራጁበት ህዋስ ስር ግምገማ እንደሚደረግባቸውና ከኤ እስከ ዲ የሚደርስ ውጤት እንደሚሰጣቸው ከሰነዱ ለመራዳት ይቻላል።
የመንግስት የመገናኛ ብዙሃን በህዝብ ንብረት የሚተዳዳሩ ቢሆንም፣ የአንድ ፓርቲ አገልጋይ ለመሆናቸው ከዚህ በላይ ማስረጃ እንደሌለ አስተያየታቸውን የሰጡን አንድ የሚዲያ ባለሙያ ተናግረዋል።
ጋዜጠኞች የኢህአዴግ አባላት የሚሆኑት ጥቅማቸውን አስበው እንጅ በድርጅቱ አምነውበት ላይሆን እንደሚችል፣ ከሚሰሩት ስራ መናገር ይቻላል የሚሉት አስተያየት ሰጪው፣ አብዛኞቹ አጋጣሚውን ሲያገኙ ወደ ውጭ ወጥተው መቅረታቸው አባልነቱ ለጥቅም መሆኑን ያረጋግጣል ብለዋል፡፡ በሌላ ዜና ደግሞ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ህዳሴ የሚባለውን የኢህአዴግ አዲስ ልሳን ስፖንሰር እንዲያደርጉ እየታዘዙ ነው።
ኢሳት ከአዲስ አበባ ኢህአዴግ ኮሚቴ ጽ/ቤት በአስተዳደርና ፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወ/ጊዮርጊስ ተፈርሞ በወጣ ደብዳቤ ላይ ለማረጋገጥ እንደቻለው፣  በሁለት ሳምንት አንድ ጊዜ ታትሞ የሚወጣው ህዳሴ የተሰኘው የኢህአዴግ የፖለቲካ ልሳን ጋዜጣ በስፖንሰር ሺፕ ሰበብ በመንግስት መ/ቤቶች ባጀት ወጪ እንዲታተም እየተደረገ ነው።
ከጽ/ቤቱ የካቲት 5 ቀን 2007 ዓ.ም ከ5 በላይ ለሚሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር መ/ቤቶች በአድራሻቸው ተጽፎ የተሰራጨው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው እያንዳንዱ መ/ቤት ስፖንሰር ለማድረግ የተስማማበትን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድነት ቅርንጫፍ በአዲስ አበባ ኢህአዴግ ኮሚቴ ጽ/ቤት ስም ወደሚታወቀው ባንክ አካውንት ገቢ እንዲያደርጉ የሚያሳስብ ሲሆን ለአንድ ጊዜ ማሳተሚያ እስከ 300,000 ብር እንዲከፍሉ ታዘወዋል።





አዲዮስ ምርጫ… አዲዮስ ሰላማዊ ትግል!!!

February 27, 2015
Tilahun Zaga | fikireyohanis@yahoo.com
በዓጼው ዘመን የነበሩ ደራስያን አብዛኛዎቹ በቀኝ እጃቸው ብዕር በግራ እጃቸው ስልጣን የጨበጡ ናቸው፣ በዚህም መሰረት የዘመኑ ሹም የሰራው ብቻ ሳይሆን በሩቁ በማንኪያ የነካው ወጥ ሁሉ ይጣፍጥለታል፣ ወጡ እንዳይጎረና ዙሪያውን ከበው የሚያማስሉ ብዙ ሊቄዎች ስላሉ ነው፣ የዚያ ሁሉ ወጥ አማሳይ እጅ ያረፈበት ወጥ ደግሞ በየትኛውም መመዘኛ ሲታይ ላይጣፍጥ አይችልም
ከዚህ በተቃራኒው ግን አንድ ነበልባል ብዕር በቀኝ እጁ የጨበጠ ግራ እጁ ግን ባዶ የሆነ የብዕር ሰው በስራዎቹ እሳት ጫሪ፣ አነጋጋሪ፣ የአብዮትን ማዕበል የሚቀሰቅሱና በዓጼው ቢባል በደርጉ በብዕሩ የተቀመጡበትን ወንበር አንቀጥቃጭ ጉበኛው አቤ ነበር፣ አቤ በቀኝ እጁ የያዘው ብዕር ብቻ ነው
አቤ በዚያን ዘመን የግሽ ዓባይ ጎርፍ ከገጠር አምጥቶ ከቀለጠው ከተማ የዶለው ብቸኛ ፍጡር ነው፣ ብዕሩ በገነተ- ልዑል ግቢ ገብቶ ያልተሟሸ ይልቁንም በደረቅ የገጠር ቅኔ ቤት ተስሎ የወጣ፣ ቃላቱም ቱባ አገራዊና ሸካራ ለባለስልጣናቱም ጎርባጣ እንጂ ቤተ መንግስታዊ ለስላሳ አልነበሩም
ይህን ጽሁፍ ከላይ ለጠቀስኩት ርዕስ ማስተካከያ ደርዝ እንዲሆን አንድ ጸሃፊ ስለ አቤ ጉበኛው ከጻፉት መጣጥፍ የተዋስኩት ሲሆን በርዕሱ እንዲሁም በመግቢያው ላይ በጨረፍታ ለማሳየት እንደሞከርኩት የአምባገነኖች የዘመን ፍጻሜ ሲቃረብ ብዕረኞች የመድፈኞች ያህል ይገናሉ፣ ጋዜጠኞች የታንከኞች ያህል ያስተጋባሉ፣ ጸሃፊዎች የሮኬት ተኳሾች ያህል አቧራውን ያስነሱታል
እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ተማሪዎች እንቅስቃሴ በሃገራችን ብቻ ሳይሆን በአብዛኛው ተራማጅ በሚባሉ ክፍለ ዓለማት ባሉ ህዝቦች ዘንድ የተሞገሰ እንቅስቃሴ ነበር፣ እንቅስቃሴው ተራማጅ ብቻ ሳይሆን የሶሻሊስት ርዕዮት አቀንቃኝ ነበር፥ ከብዙ የህቡዕና አንዳንዴም የግልጽ ተቃውሞ እንቅስቃሴዎች በኋላ የዓጼውን ስርዓት ስር ከስር ቦርቡሮ የጣለው ይህ የተማሪዎች አብዮት እንደሆነ ይታመናል፥ ይህን የተማሪዎች አመጽ ተከትሎ ከገዥው ስርዓት ይሰጡ የነበሩ መልሶች ለምላሹም ይሰጡ የነበሩት አጸፋዊ መልሶች እና ጉልበት ላይ ብቻ ያተኮሩ የዓጼው ባለሟሎች እርምጃዎች ተማሪውን ወደእልህና ቁጭት የገፉ ናቸው
ይልቁንም ህቡዕ የነበሩ የእንቅስቃሴው አራማጆች በገሃድ እየወጡ ስርዓቱን መቃወማቸው የየዩኒቨርሲቲዎች ዓመጽ፣ የአውሮፕላን ጠለፋዎች፣ የመሬት ላራሹ ድምጾችና ሌሎችም፥ ዓጼውን ያደናበሩ በእውር ድንብር ይወሰዱ የነበሩ ግብታዊ እርምጃዎችም ትግሉን ከፍ ወዳለ ደረጃ ያሳደጉ ነበሩ
የዓጼው ስርዓት የመጨረሻው መጨረሻ ሲቀርብም ሁኔታውና ሂደቱ ያስፈራቸው ባለጊዜዎች በተለያዩ ጊዜያት ጠቋሚ ጽሁፎችን ያሰፈሩበት ሁኔታ እንደነበር ታሪክን ያስታውሷል፥ በዓጼው ስርዓት ገዥ ወንበር ላይ የነበሩት ጄነራል አቢይ አበበ በ19 መቶ 55 ለህትመት በበቃች አነስተኛ መድብላቸው አውቀን እንታረም ሲሉ የስርዓቱን ማብቃት የጠቆሙ ቢሆንም የዓጼው አገዛዝ ከገባበት ቀውስ ለመውጣት የሞከረበት አጋጣሚ እምብዛም ነበር
ጄነራል አቢይ በመጽሃፋቸው መግቢያ የህይወትን ምሬትና ጣፋጭነት በብዙ ከተነተኑ በኋላ፣ ድካማችን ለሃገራችንና ለመጪው ትውልድ ነው የሚል ሞልቶ ይሆናል . . . ሲሉ ይቀጥላሉ ይህን መናገር የሚገባው በአንድ የትውልድ ዘመን አብሮት ላለው ጓደኛው የሚያስብ አእምሮ ያለው ሰው መሆን አለበት፣ እንደሚታየው ከሆነ ድካማችን ለየግል ፍላጎታችን ሆኖ የድካማችንን ፍሬ በልቶ መሞት ብቻ ነው፣ ሞታችንም ቅጣታችን ነው እስከዚያው ድረስ ግን ግንብ በሌለው . . . ዘበኛ በማይጠብቀው ክፍት ወህኒ ቤት ውስጥ ሆነን እንደልባችን እየተቀናጣን፣ ለምኞታችን እየተገዛን ምንም የሚደርስብን አይመስለንም፣ ጊዜው በደረሰ ጊዜ ግን አይተነው የማናውቀው የብረት አጥር በዙሪያችን እንደነበረ ይከሰትልናል . . . ትልቁም የብረት በር እፊታችን ተደቅኖ ይታየናል፣ ያን ጊዜ መንጥቆ የሚያስወጣንም ዘበኛ ይገለጣል በአጠገባችንም ይንጎራደዳል፣ እንደከብት ስናግድ እና ስንታገድ የኖርንባትና ለማዳዎቹ አውሬዎች የሰባንባት መሬት ተራዋን ልትበላንና ሰብታም ሌላውን ለመመገብ አፏን ከፍታ ትቀበለናለች፣ ከዚህ የሚያድነን የለም. . ተመልሰን ልንወጣ አንችልምና የኛም ተራ በዚሁ ይወሰናል ሲሉ ጽሁፋቸውን መጪውን የህዝብ የቁጣ ዘመን በማሳሰብ ይቀጥላሉ
ሆኖም ግን ይህንና ሌሎች ህዝባዊ ጥያቄዎችን መመለስ ያልቻለው የዓጼው ስርዓት ጊዜው ደርሶ በ66ቱ የመረረ አመጽ ሲደረመስ፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ከሚታወቁትና በደርግ ወደ እስር ከተጋዙት እንዲሁም በጅምላ ከተረሸኑት 60ዎቹ ሚኒስቴሮች ውስጥ አስቀድመው አውቀን እንታረም ብለው የተናገሩት ጄነራል አቢይ አበበ አንዱ ናቸው
ከዚህ ትምህርት ያልወሰደው ደርግም በመጨረሻዎቹ የስልጣን ማገባደጃ ዘመኑ ቀድሞም ቢሆን ለዓይን ሙሉ ያልነበሩ ጸሃፍትን እያደነ መረሸን፣ እያፈነ መሰወር ስራዬ ብሎ ተያያዘው
እልም ባለ አጠቃላይ ሃገር አቀፍ ቀውስ ውስጥ የተዘፈቀው የደርግ መንግስት የወንበዴዎች ሃይልና ሴራ ማየል፣ የየጦር ክፍል አዛዦች መከፋፈል እንዲሁም ሃገሪቱ የተዘፈቀችበት ቅጥ ያጣ ሶሺዮ-ኢኮኖሚካል ቀውስ፣ ሃገሪቱን አልፎም ቀጠናውን ሙሉ በሙሉ የጦር አውድማ ያደረገ ነበር
እዚም እዚያም ሃገራዊ ግዳጆች፣ እዚም እዚያም አፈሳና የወጣቶች ትርምስ፣ እዚም እዚያም የጦርነት ድምጽና የግደል ተጋደል ዘመቻዎች ብዛት የደርጉ መንግስት የለት ተቀን የቤት ስራዎች ሆነው የነበዓሉ ግርማ “ኦሮማይ“ በወቅቱ ያለሰሚ ቢዳፈንም ውለው አድረው ግን በባለስልጣናቱ ጆሮዎች ላይ ማቃጨላቸው አልቀረም፣ የሆነው ሆኖ ግን በመጨረሻው መጨረሻ የሆነው ለዓጼው በተማሰው የጠለቀ ጉድጓድ መግባት ነበር፣ ከ1960ዎቹ መጨረሻ ጀምሮ በከፍተኛ ትጋት በከፍተኛ ትጋት የተማሰው ጉድጓድ አሁንም የሞላ አይመስልም፣ ምናልባትም አሁን ያሉትን ዘረኝነት ያሳበዳቸውን ጎርሶ የሚደፈን ከሆነ ጊዜ የሚያሳየን ይሆናል
አሁንም ከነዚህ ስርዓቶች ያልተማረው ህወሃት/ኢህአዴግ በመጨረሻው መጨረሻ ሰዓት እንኳ የሚጮሁትን የጣር ድምጾች፣ የሚያቃጭሉትን የማንቂያ ደወሎች ባለመስማት በየዕለቱ እየከፋ የሄደ ስርዓት መሆኑን እያሳየን ነው
የሰላና የተባ ብዕር ያላቸው ጸሃፊያን የእስር ቤት ግዞት፣ የነጻነት ጠያቂ ዜጎች የጅምላ ግድያ እና ሌሎች ሃገራዊ ስቃዮች ያላነቁት ህወሃት/ኢህአዴግ ህዝባዊ እንቅስቃሴዎችንና የመብት ጥያቄዎችን በሃይል ለመደፍጠጥ እየሄደበት ያለው መንገድ፣ ሩቅ የማይወስድና ምሪቱም ወደማይቀረው የተማሰ ጉድጓድ መሆኑን የተረዳው አይመስልም
በሃገራችን የተንሰራፋውን ጭቆና፣ የመብት ጥሰትና፣ ፍትህ አልባነትን ስንመለከት የህዝብ አብዮት ለመከሰቱ ምንም ጥርጥር እንዳይኖረን ያደርጋል፣ እንዲህ አይነቱ በገነገነ እምቅ የቁስል ስሜት የሚቀሰቀስ አብዮት ውጤቱ ምን ሊመስል እንደሚችል ሰሚ ጆሮ ካላቸው ሩቅ ዘመን ሳይሄዱ እነጋዳፊና ሙባረክ ላይ የሆነውን ማየት ይቻላል
አዲዮስ ምርጫ፣ አዲዮስ ሰላማዊ ትግል
የነጻነት መንገዶችን ሁሉ ቀርቅቦ የዘጋው ህወሃት/ኢህአዴግ፣ ምናልባትም ትንሽ ቀዳዳ ካገኘን ብለው በሃገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ህልውናቸው የመጨረሻው የገደል ጫፍ ላይ መሆኑ ብቻ ሳይሆን፣ እንደ አንድነት ያሉ በሰላማዊ የትግል ስልት የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሻሞ. . .ሻሞ ተወርውረው ለታማኞች መሰጠታቸውና ህልውናቸው መክሰሙን ስናይ ሌሎችም ባለሳምንቶች መኖራቸውን ለመናገር ነቢይ መሆንን አይጠይቅም፣ የነጻነት መንገዶች ሲዘጉ የአመጽ መንገዶች ወለል ብለው እንደሚከፈቱ አለማወቅ፣ ታሪክን ብቻ ሳይሆን ለነባራዊና ተጨባጭ ኩነቶች ዓይኖችን ማሳወር ነው፣ ስለዚህም አዲዮስ ምርጫ፣ አዲዮስ ሰላማዊ ትግል!!!

ምርጫ ለኢትዮጵያ ወታደርና ፓሊስ: – ለህወሓት ባርነት ወይስ ለኢትዮጵያ ነፃነት

ምርጫ ለኢትዮጵያ ወታደርና ፓሊስ: – ለህወሓት ባርነት ወይስ ለኢትዮጵያ ነፃነት
የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውትድርና ከፍተኛ ክብር አለው። ውትድርና ከሙያና ሥራ በላይ የነፃነትና የክብር መገለጫ፤ ሀገርን ከባዕድ ወረራ መከላከያ ጋሻ ነው ብሎ ያምናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ህግና ሥርዓት አክባሪ በመሆኑ ለፓሊስም ከፍተኛ አክብሮት አለው። የፓሊስ ሥራ ወንጀልን መከላከልና ወንጀለኞችን ወደ ፍርድ ማቅረብ መሆኑ በኢትዮጵያ ባህል የተከበረ ቦታና እውቅና አለው።
በህወሓት የአገዛዝ ዘመን ግን ይህ እየተቀየረ ነው። የህወሓት አዛዦች እየመሩት ያለው የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት ሀገርን ከባዕድ ጠላት ከመከላከል ጋር ምንም ዝምድና በሌላቸው ሁለት አበይት ተግባራት ላይ ተጠምዷል። በህወሓት አዛዦች የሚመራው ሠራዊት ዋነኛ ተግባር ለሰብዓዊ መብቶቻቸው መከበር እና ለፍትህ መስፈን የሚታገሉ ዜጎችን ማጥቃት ሆኗል። የጦሩ ሁለተኛው አቢይ ተግባር ደግሞ ለአዛዦች የግል ጥቅም ማካበቻ ገቢዎችን በሚያስገኙ ሥራ ላይ መሠማራት ነው።
የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ኢትዮጵያዊያንን ማጥቂያ ሠራዊት መሆኑ ሲቪሉን ሕዝብ ብቻ ሳይሆን የሠራዊቱንም አባላትን ጭምር ለህሊና ወቀሳ የዳረገ ጉዳይ ነው። ሆኖም ግን ይህ በህሊና ወቀሳ ብቻ ሊታለፍ የማይችል ወንጀል ነው። ሠራዊቱ በህወሓት እየታዘዘ የሚዘምተው በገዛ ራሱ ልጆች፣ እህቶች፣ ወንድሞችና ወላጆች፤ በገዛ ራሱ ጥቅሞች እና በገዛ ራሱ ላይ መሆኑ መገንዘብ ይኖርበታል። በገዛ ራሱ ጥቅሞች ላይ የሚዘምት አንድም ህሊና የሌለው አሊያም ነፃነት የተነፈገው ሰው ብቻ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ሠራዊቱ እየተራበና እየታረዘ አለቆቹ የታላላቅ ህንፃዎች ባለቤቶች፣ ባለፋብሪካዎች፣ የባንክና የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ባለአክሲኖች የሚሆኑበት ሥርዓት ከዳር ሆኖ የሚመለከት መሆኑ የሚገርም ነው። ሠራዊቱ ቤተሰቦቹን መመገብ አቅቶት እያለ የአዛዦቹ ልጆች ለሽርሽር ዓለምን ይዞራሉ። እንዴት ነው ሠራዊቱ እየደኸየና እየሞተ አዛዦቹ እየከበሩ የሚሄዱት? ይህ አዋራጅ ሁኔታ እንዲያበቃ መታገል የሠራዊቱ ግንባር ቀደም ኃላፊነት ነው። ሠራዊቱ ወይ ባርነትን አሜን ብሎ መቀበል አለበት አለበዚያም እሱም እንደነሱ ሰው መሆኑን ማሳየት መቻል አለበት። በኢትዮጵያ ውስጥ የህወሓት አገዛዝ ወድቆ የሕዝብ ይሁንታ ያገኘ መንግሥት መመሥረቱ በከፍተኛ ሁኔታ ከሚጠቅማቸው የኅብረተብ ክፍሎች ግንባር ቀደሙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ናቸው። በዚህም ምክንያት የሠራዊቱ አባላት ለሥርዓቱ መውደቅ በግልጽም በስውርም መታገል የዜግነት ብቻ ሳይሆን አዕምሮ ያለው ሰው ሆነው በመፈጠራቸው የተቀበሉት ግዴታ ነው።
ፓሊስን በተመለከተም ሁኔታው ተመሳሳይ ነው። ህወሓት የኢትዮጵያን ሕዝብ አፍኖ ለመግዛት የቻለው በዋኛነት የፓሊስን ኃይል ለአፈናው ተግባር የሚጠቀም በመሆኑ ነው። የተቃውሞ ድምጾች በተሰሙ ቁጥር የኢትዮጵያ ፓሊስ በወገኖቹ ላይ የሚያወርደው ዱላ የሚዘገንን ሆኗል። ሰላማዊ ሰልፈኞችን በጥይት መግደልና ማቁሰል፤ አረጋዊያንን፣ ሴቶችንና ሕፃናትን መግደል፣ ማቁሰል፣ መደብደብ በዚህ ተግባር የተሠማሩ ፓሊሶችን በቡድንም በግልም በህግ የሚያስጠይቅ ከባድ ወንጀል ነው። በህወሃት እየተመራ ያለው የኢትዮጵያ ፓሊስ ተግባራት ተበዳዮችን ብቻ ሳይሆን ራሱ ፓሊስንም ጭምር አንገት የሚያስደፋ ተግባር ነው። ለመሆኑ አንድ ተራ የኢትዮጵያ ፓሊስ ባልደረባ ከህወሓት አገዛዝ ምን ተጠቀመ? መልሱ “ምንም” የሚል ነው። ይልቁንስ በህወሓት የአገዛዝ ዘመን ፓሊስ የተናቀና የተዋረደ ሥራ ሆነ። በህወሓት አገዛዝ ፓሊስ እንደሰለጠነ አዳኝ ውሻ “ያዝ” ሲሉት የሚነክስ፣ የሚያደማ፣ የሚቦጭቅ ሆኗል። ይህ ለፓሊስ፣ ወንጀልም ውርደትም ነው። በህወሓት አገዛዝ መገርሰስ እና በምትኩ የህግ የበላይነት የሰፈነበት ሥርዓት መስፈን ፓሊስ ከሁሉ በላይ ተጠቃሚ ነው፤ ሰብዓዊ ክብሩን ያረጋግጥለታልና።
ዛሬ በኢትዮጵያችን ውስጥ የታዘዙትን የሚፈጽሙ የጦርና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ስላሉ ነው የህወሓት ሹማምንት ልባቸው ያበጠው። ለማስረጃ ያህል ሰሞኑን የህወሓቱ ሹም አባይ ፀሐዬ የአዲስ አበባ ዙሪያ ገበሬዎች በግዴታ መነሳታቸው የሚቃወሙትን ዜጎችን ሁሉ ”ልክ እናስገባቸዋለን” ብሎ በሸንጎ የዛተው የታዘዘውን የሚፈጽም የጦርና የፓሊስ ሠራዊት መኖሩን ተማምኖ ነው። እስከ መቼ የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊትና ፓሊስ ሕዝብን ማስፈራሪያ መሣሪያ ይሆናል?
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ የኢትዮጵያ የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ለራሳቸው እና ለወገናቸው የሚበጀው ሥርዓት የቱ እንደሆነ ያውቃሉ ብሎ ያምናል። በዚህም ምክንያት ስብዕናቸውን እያዋረደ እና እያደኸያቸው ያለውን የህወሓት አገዛዝን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር በመሆን ይፋለሙታል ብሎ ያምናል። ይህ ውሳኔ ግን ሠራዊቱ በጅምላ ሳይሆን እያንዳንዱ የሠራዊቱ አባል በግሉ የሚወስደው ውሳኔ እንደሆነ አርበኞች ግንቦት 7 ይገነዘባል።
በዚህም መሠረት ተደጋጋሚ ጥሪ እየተደረገለት፤ ጥሪውንም እየሰማ ከህወሓት ጋር ወግኖ ሕዝብን መውጋት የቀጠለ የሠራዊቱ አባል ላደረሰው ጥፋት በግል መጠየቁ የማይቀር መሆኑ ሊገነዘብ ይገባል። በእያንዳንዳንዱ የጦርና ፓሊስ ሠራዊት ባልደረባ ፊት የቀረበው ምርጫ “ለህወሓት ባርነት ታድራለህ ወይስ ራስህንና ሀገርን ነፃ ታወጣለህ” የሚል ነው።
ራስህንና ሀገርህን ነፃ ለማውጣት የመረጥክ የሠራዊቱና የፓሊስ ባልደረባ አሁኑኑ ሕዝባዊ ትግሉን ተቀላቀል። እስከዛሬ የበደልከውን ሕዝብ ለመካስ ምቹ ሁኔታ አለህ። በግልጽ የነፃነት ኃይሎችን እንድትቀላቀል፤ አሊያም አለህበት ሆነህ በውስጥ አርበኝነት እንድትደራጅና ተግባራዊ ሥራ እንድትጀምር መንገዱ ተመቻችቶልሃል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Donnerstag, 26. Februar 2015

ቻው! ቻው! በኢትዮጵያ የካሩቱሪ ቅኝ ግዛት (ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
መልካም የጉዞ ፍታት ለካራቱሪ: በኢትዮጵያ የካሩቱሪ አሟሟ አስከሬን ምርመራ
በምዕራብ ኢትዮጵያ በምትገኘው በጋምቤላ ክልል ካሩቱሪ እየተባለ ከሚጠራው ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል የውጭ የግብርና ልማት ድርጅት ጋር የወያኔ ወሮበላ የዘራፊA post-mortem on Karuturistan, Ethiopiaቡድን ስብስብ ባደረገው ስምምነት መሰረት ሲተገበር የቆየው የመሬት ቅርምት የመድረክ ላይ ተውኔት ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚጠቅም እና በእውነትም ለዕድገት የእራሱን ድርሻ ሊያበረክት የሚችል ቢሆን ኖሮ እጅግ በጣም ጥሩ ነገር ነበር፡፡ ሆኖም ግን በተግባር እየሆነ ያለው ነገር በሸፍጥ እና በመሬት ዘረፋ ላይ ያተኮረ ዕኩይ ምግባር በመሆኑ ለኢትዮጵያ ህዝብ እጅግ በጣም አስከፊ እና ጎጅ በመሆን አስጠያፊ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል፡፡
ባለፈው ወር “የኢትዮጵያ ሳራማ የረግረግ ቦታ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት/Ethiopian Meadows Plc“፣ “በኢትዮጵያ የጋምቤላ አረንጓዴ ሸለቆ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት/Gambella Green Valley Plc“ እና “በኢትዮጵያ የካሩቱሪ የግብርና ምርት ውጤቶች አምራች ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት/Karuturi Agro Products Plc (Ethiopia)“ እየተባሉ የሚጠሩትን የግል የርሻ ንግድ ድርጅቶች አካትቶ በመያዝ ጋምቤላ እየተባለ የሚጠራውን የኢትዮጵያ የግዛት ክልል ለም መሬት በመዝረፍ ሲንቀሳቀስ የቆየው ካሩቱሪ ዓለም አቀፍ የህንድ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት/Karuturi Global, Ltd ምንም ዓይነት የመድረክ ላይ ትወና ሳይደረግና የፕሮፓጋንዳ ጥሩንባ ሳይነፋ በድብቅ እና በሚስጥር የሞቱ መርዶ ይፋ ተደርጓል፡፡
በግብርና ልማት ስራዎች ላይ የተሰማራው ካሩቱሪ እየተባለ የሚጠራው የህንድ የግብርና የንግድ ድርጅት ከመጠን በላይ በተጋነነ መልኩ “በኢትዮጵያ፣ በኬንያ እና በህንድ የጽጌረዳ አበባዎችን የሚያመርት እና ወደ ውጭ የሚልክ ታላቅ ዓለም አቀፍ ድርጀት ነው እየተባለ ይነገርለታል፡፡ እ.ኤ.አ በ2008 ካሩቱሪ በምዕራብ ኢትዮጵያ በጋምቤላ ክልል 300,000 ሄክታር መሬት እጅግ በጣም ርከሽ በሆነ ኪራይ ወሰደ፡፡ የመሬት ኪራዩ ከፍተኛ የሆነ የፕሮፓጋንዳ/ቅስቀሳ ጫጫታ የበዛበት ወይም ደግሞ አስቸጋሪ የሆነ የማሳመኛ የክርክር ጭብጥ የተደረገበት በመሆን ከዓለም ከፍተኛ የሆነ የምግብ እህል አምራች ድርጀት ተብሎ ለካራቱሪ የመሰረት ድንጋዩን በመጣል ታዋቂነቱን አበሰረ፡፡ የካራቱሪ የጽጌረዳ ምርት ግን በተደሰኮረለት መጠን ሳይጓዝ ቀርቶ በመጨረሻ የጋምቤላ ክልል “የአበባ አስከሬን” መሆኑ በይፋ ተረጋገጠ፡፡
እ.ኤ.አ በ2011 የጋርዲያን ጋዜጣ የመጀመሪያ የዓይን መክፈቻ የሆነውን ዘገባውን ባወጣ ጊዜ ጋምቤላ በምዕራብ እንግሊዝ የምትገኘውን ከጥንታዊቷ የዌልስ (የሚተረክለት ንጉስ አርተር እና የካሜሎት ግዛታቸውን የሚያህል መሬት) ግዛት ጋር እኩል የሚሆን የመሬት ስፋት ያለው መሆኑን ይፋ አድርጎ ነበር፡፡ እንግዲህ ካሩቱሪ አብዛኛውን የጋምቤላን ክልል መሬት ለ99 ዓመታት በኪራይ የሚወስደው ከሆነ በትክክለኛ እና እውነታን በተላበሰ መልኩ እንዲሁም ይፋ በሆነ መልኩ የመሬት የባለቤትነት ይዞታን ከማረጋገጥ አንጻር ጋምቤላ “የካሩቱሪ ቅኝ ” ተብላ መሰየም ይኖርባታል በማለት ግልጽ አድርጌ ነበር፡፡
ካሩቱሪ እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ ከሚጠራው ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ጋር የመሬት ነጠቃ እና ቅርምት ስምምነቱን ከፈጸመ በኋላ ወያኔ የካሩቱሪን ስምምነት በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን ለሚያፈስሱ የሁሉም የውጭ መዋዕለ ንዋይ አፍሳሾች ሁሉ ብቸኛ ተምሳሌት አድርጎ በማቅረብ በብቸኝነት በተቆጣጠራቸው የመገናኛ ብዙሀን ሌት ከቀን ፕሮፓጋንዳውን መልቀቅ ጀመረ፡፡ እ.ኤ.አ በ2011 አሁን በህይወት የሌለው የወያኔ መሪ መለስ ዜናዊ የእራሱን ባዶ ስብዕና ከፍ ከፍ በሚያደርግ መልኩ እየተመጻደቀ ኢትዮጵያ በምግብ እህል እራሷን እንደምትችል ታዕምራዊ የሆነ መፍትሄ ማግኘቱን በይፋ ደሰኮረ፡፡ በዘመናችን አስጨናቂ ሆኖ ለዘለቀው ለኤች አይቪ ኤድስ ፈዋሽ መድኃኒት የተገኘለትን ያህል ነበር ቡራ ከረዩ ሲል የከረመው፡፡ ለዘመናት በኢትዮጵያ ምድር ላይ ሲያንዣብብ እና በጥቁር ፈረስ ላይ ሆኖ የምጽዓት ቀንን ሲጠብቅ ለቆየው አሰቃቂ የረኃብ መቅሰፍት የመለስ የሚስጥር መሳሪያ ካሩቱሪ ሆኖ ተገኘ፡፡ መለስ እንዲህ በማለት የውሸት ዲስኩሩን በድፍረት በማሰማት አምባርቆ ነበር፣ “በአምስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያ ምንም ዓይነት የምግብ እህል እርዳታ አትፈልግም፡፡“
በአጭሩ እ.ኤ.አ በ1991 መለስ በዙፋኑ ላይ ከተቀመጠ በኋላ ኢትዮጵያውያን/ት በቀን ሶስት ጊዜ ምግብ የሚበሉ ከሆነ የእርሱ መንግስት ስኬት በዚያ የሚለካ መሆኑን በይፋ ተናግሮ ነበር፡፡ የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት/ኮንግረስ የውጭ እርዳታ አጽዳቂ ኮሚቴ ሰነድ አባሪ 2 እ.ኤ.አ በ2015 ያወጣው ዘገባ እንዲህ ይላል፣ “ኢትዮጵያ በዓመት በነፍስ ወከፍ 471 የአሜሪካ ዶላር ሀገራዊ ገቢ (Gross Domestic Product/GDP) በማግኘት እና የአሜሪካንን የምግብ እና አስቸኳይ እርዳታ ከሚቀበሉ የመጀመሪያዎቹ ሀገሮች አንዷ በመሆን አስከፊ የምግብ ዋስትና እና በምግብ ንጥረ ነገር እጦት ከሚሰቃዩ በዓለም ካሉ ሀገሮች መካከል የመጨረሻዋ ደኃ ሀገር ሆና ትዘልቃለች፡፡“ እንግዲህ እንደዚህ ያለ ሁኔታ በተንሰራፋበት ከባቢ አየር ውስጥ ነው የምግብ እህል እርዳታ አያስፈልጋትም እየተባለ በመለስ ሲደሰኮር የቆየው!
ለካቱሪ ስለተሰጠው ስለ300,000ው የጋምቤላ የመሬት ኪራይ (በእርግጥ ስጦታ ቢባል ይሻል ነበር) ጉዳይ እስከ አሁን ድረስ ምላሽ ያላገኙ በርካታ ጥያቄዎች አሉ፡፡ ይኸ በተለየ መልኩ የሚያስደንቅ ሊሆን አይችልም፡፡ የድብቅነት ባህሪ የተጠናወተው የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ አመራር (በጫካ በነበረበት ጊዜም እንኳ ቢሆን) ምንም ዓይነት ግልጽነት ወይም ደግሞ ተጠያቂነት በሌለው ሁኔታ ሁልጊዜ የጨለማ አካሄድ ድርጊትን ነው ሲከተል የቆየው፡፡ ለወያኔ ሁሉም ነገር የመንግስት ሚስጥር ነው፡፡ መለስ ከሞተ ከሶስት ዓመታት በኋላ እንኳ የሞቱ መንስኤ ምን እንደሆነ እንዳይታወቅ እስከ አሁን ድረስ ከፍተኛ ሚስጥር ሆኖ ተይዞ ይገኛል፡፡ በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ውስጥ በመንግስት ላይ መንግስት በማቋቋም ሚስጥራዊ ምርምር የሚያደርግ ተቋም ያለበት የዕኩይ ምግባር አራማጅ ድርጅት ነው፡፡ በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ዋና ስብስብ የዉስጥ አመራር ያሉት በዓለም ዉስጥ ካሉ ውስጥ እጅግ በጣም አጭበርባሪ፣ ሸፍጠኛ፣ ጮሌ አታላይ፣ ተከታታይ ደባ ሰሪ፣ ጠማማ፣ ማቋረጫ የሌለው ክፋት፣ አውዳሚ፣ ሰይጣናዊ፣ ስውር ደባ እና መሬት ላይ በየትኛውም ቦታ የሚገኙ የማካቬሊያን ዓይነት የፖለቲካ አሰራሮች የሚተገብሩ ጭራቆች ናቸው፡፡
ከዋናዎቹ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ አባላት ውጭ ያሉ ጥቂት አመራሮች ከካሩቱሪ ጋር የተፈጸመውን ስምምነት ወይም ደግሞ ከሌሎች የመካከለኛው የዓረብ እና የኢስያ ሀገሮች መዋዕለ ንዋይ አፍሳሾች ጋር የተደረጉትን ስምምነቶች ፍንጭ ሊያውቁ ይችሉ ይሆናል፡፡ ይህንን የመሰለ ድብቅነት ከግንዛቤ በመውሰድ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ሁልጊዜ ቢያንስ ሁለት ስምምነቶችን የሚያካሂድ መሆኑ መሰረታዊ ጭብጥ ያለው ይመስላል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ አንደኛው ለህዝብ ፍጆታ ሲባል ላይ ላዩን ለሽፋን የሚያደርገው አስመሳይ ስምምነት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ምንም ዓይነት የማስመሰያነት ድርጊት የሌለበት እና ከጠረጴዛ ስር ሰው ሳያየው የተደረገ ስምምነት ነው፡፡ ከዚህ አንጻር መለስ እና የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ድርሻቸውን (ኪስ የሚሞላ ጉርሻቸዉን) አግኝተዋል የሚል ግምት አለኝ፡፡ ስለዚህ ስለሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ልማት፣ ዕድገት፣ ሰላም እና ፍቅር ደንታቸው አይደለም!
እውነት ለመናገር በመጀመሪያ ደረጃ በካሩቱሪ “የመሬት ኪራይ ስምምነት” ላይ የነበረኝ እንቆቅልሽ ጮሌዎቹ አታላዮች፣ አጭበርባሪዎች የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የጓዳ ዱለታ አራማጆች ካሩቱሪ ጋምቤላ ላይ መዋዕለ ንዋዩን እንዲያፈስ አታለውት ይሆን የሚል ጥያቄ ነበረኝ ። ወይም ደግሞ ካሩቱሪ በስግብግብነት ምንም ዓይነት ግንዛቤ ሳይኖረው እና ሳያጣራ ወደ ጋምቤላ ክልል ዘው ብሎ በመግባት ገንዘቡን እና ጊዜውን ያባከነ እርባናየለሽ ፕሮጀክት ነውን? ማንኛውም የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ተወካይ የሆነ ሁሉ ከውጭ መዋዕለ ንዋይ አፍሳሽ ጋር ስለማንኛውም የመሬት ኪራይ ስምምነት ትክከለኛና ሕጋዊ ውል ሊፈጽም ይችላል ብሎ ማመን ይቻላልን?
እውነታው ተፍረጥርጦ ሲታይ ግን የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ እና አሁን በህይወት የሌለው መሪው በአንክሮ ሲፈተሹ የጥንት የግሪክ አስመሳይ እና የቅጥፈት አማልዕክት ተመልሶ የመወለድ ዓይነት ተምሳሌቶች ናቸው፡፡ እነዚህ የዕኩይ ምግባር አራማጆች የአጭበርባሪነት፣ የቀጣፊነት እና የውሸት መረጃ ጌቶች ናቸው፡፡ እንደዚህ ያሉ አይን አውጣ ቀጣፊዎች ናቸው፣ እናም ባለፉት አስርት ዓመታት ጊዜ ውስጥ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ታዕምራዊ እና አስደናቂ በሆነ መልኩ በየዓመቱ በአማካይ በ11 በመቶ የምጣኔ ሀብት ዕድገት አስመዝግቧል በማለት የዓለምን ህዝብ ሙሉ በሙሉ በሚባል መልኩ እንዲታለል ያደረጉ ፈጣጣ ቀጣፊዎች ናቸው፡፡ (“የዓለም ባንክ እና የኢትዮጵያ የዕድገት እና ትራንስፎረማሽን ዕቅድ“ በሚል ርዕስ ባቀረብኩት ትችቴ ላይ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ (የቅጥፈት የድንፋታ አጋሮቹ የዓለም ባንክን፣ የዓለም አቀፉን የገንዘብ ድርጅት፣ የዩናይት ስቴትስ አሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት መምሪያ እና የልማት ዕገዛ ቡድን የዓለም አቀፍ የድህነት ወትዋች አቃጣሪዎችን ጨምሮ) ሁሉም ኢትዮጵያ ባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ በየዓመቱ በአማካይ በ11 በመቶ የምጣኔ ሀብት ዕድገት አስመግባለች የሚለው ድፍረት የተሞላበት ነጭ ውሸት፣ ተራ ቅጥፈት እና የቁጥር ጨዋታ (የቁጥር ቅጥፈት) መሆኑን ከጥርጣሬ በላይ በሆነ መልኩ ያረጋገጥኩ መሆኔን ግልጽ አድርጌ ነበር፡፡)
ያም ሆነ ይህ ስለ ኢትዮጵያ መሬት ኪራይ (ስጦታ ቢባል ይሻላል) ስለሚታወቀውም ሆነ ስለማይታወቀው ጉዳይ ካሩቱሪንን ጨምሮ ደሳለኝ ራህማቶ የተባሉት የኢትዮጵያ ልሂቅ እና በገጠር መሬት ላይ እውቅ የሆኑ ተመራማሪ እ.ኤ.አ በ2011 “መሬት ለመዋዕለ ንዋይ አፍሳሾች፡ መጠነ ሰፊ የመሬት ዝውውር በኢትዮጵያ/LAND TO INVESTORS: Large Scale Land Transfers in Ethiopia“ በሚል ርዕስ ባቀረቡት ትችት በርካታ ጉዳዮችን አንስተው ነበር፡፡ ደሳለኝ እንዲህ የሚል የመከራከሪያ ጭብጥ አቅርበው ነበር፣ “የግብርና እና የገጠር ልማት ሚኒስቴር/Ministry of Agriculture and Rural Development(MoARD) እና የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ባለስልጣን የተባሉት መንግስታዊ ድርጅቶች ከመዋዕለ ንዋይ አፍሳሾች ጋር የስምምነት ውል የመፈጸም ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል፡፡ የኮንትራት ስምምነት ሰነዶቹ ቀላል እና መዋዕለ ንዋይ በሚፈስስባቸው ፕሮጀክቶች ላይ አስቸጋሪ የሆነ ግዴታን የሚጥሉ አይደሉም፡፡ መዋዕለ ንዋይ አፍሳሾች ምን ዓይነት ሰብሎችን ማምረት እንደሚፈልጉ እና በየትኛው ገበያ ወስደው መሸጥ እንዳለባቸው መዋዕለ ንዋያቸውን በሚያፈስሱበት ሀገር ምንም ዓይነት ጣልቃገብነት ሳይደረግባቸው መፈጸም እንደሚችሉ በሰነዱ ላይ በግልጽ ተቀምጧል፡፡ መዋዕለ ንዋይ አፍሳሾች ያመረቷቸውን ምርቶች ለአካባቢው ወይም ደግሞ ለሀገር አቀፍ ገበያዎች ማቅረብ እንዳለባቸው የሚያስገድድ ሁኔታ ሳይኖር ይልቁንም ምርቶቹን ለውጭ ሀገር ገበያ ማቅረብ እንዲችሉ የሚያበረታቱ ናቸው፡፡ የሀገሪቱን የምግብ ዋስትና ፍላጎት ከማሳካት አንጻር የተደረገ ስምምነት የለም፡፡ የፕሮጀክት ኃላፊዎች/Project managers ለማህበረሰቡ መሰረታዊ አገልግሎቶችን የማቅረብ ወይም ደግሞ በእነዚህ ዘርፎች ላይ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ የስምምነት ግዴታ የለባቸውም… “
ለፕሮጀክቶቹ የተደረጉ የአካባቢ ስነምህዳር የጉዳት ትንታኔ ጥናቶች/impact assessment አሉ ቢባልም እንኳ የውሸት እና በጣም ጥቂት ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያት መሬቱ ሁልጊዜ አደገኛ ለሆነ የአፈር መሸርሸር እና ለአፈር መከላት አደጋዎች በመጋፈጥ ከፍተኛ የሆነ የአካባቢውን የተፈጥሮ ሀብት ውድመት ያስከትላል፡፡ (አጽንኦ ታክሎበታል፡፡)
የካሩቱሪ ከመጠን ያለፉ ጥረቶች፣
በጋምቤላ በ99 ዓመታት በተገባው የመሬት ኪራይ ውል በደሳለኝ ዕይታ መሰረት ካሩቱሪ የሚጠበቁበት ዝርዝር ነገሮች ምንድን ናቸው? የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ሁሉንም ነገር ደብቅ ስለሚያደርግ እውነታዎችን ለማረጋገጥ የምችልባቸው እውነታዎቸ የሉም፡፡ ሆኖም ግን ከብዙ ትንታኔዎች እና ጥናቶች በመነሳት በካሩቱሪ ላይ የዋህነት የተንሰራፈበት፣ ምኞት የተንጸባረቀበት፣ ስግብግብነት የታጨቀበት፣ እና ደባ የተሸረበበት ሁኔታ ለመኖሩ ሊያረጋግጡ የሚችሉ የተጋጥሞ መረጃዎች ተገኝተዋል፡፡
ካሩቱሪ እ.ኤ.አ በ2008 ከጋምቤላ ክልል በርካሽ የኪራይ መጠን መሬት ሲያገኝ ከአምላክ በወርቃማ ሳህን ላይ ምግብ እንደመና የወረደለት ነበር የመሰለው፡፡ በኢትዮጵያ የካሩቱሪ ኃላፊ የሆኑት ካርምጅት ሴክሆን እንዲህ በማለት ገለጻ አድርገው ነበር፣ “መሬቱን አላየንም፡፡ እነርሱ ሰጡን፣ እኛ ደግሞ ተቀበልናቸው፡፡ በእውነት እንደዚህ ነው የሆነው፡፡ መሬቱን የማየት አጋጣሚ እንኳ አላገኘንም (በድል አድራጊነት እንደ ጅብ በመሽከምከም ሳቁን ለቀቀው)፡፡ መሬቱን አደሉን፡፡ የሆነው የኸ ነው፡፡ በጣም ቆንጆ የሆነ ለም መሬት ነው፡፡ በዚያው ላይ ደግሞ ዋጋው ርካሽ ነው፡፡ በእርግጥም በጣም ርካሽ ነው፡፡ በህንድ ውስጥ እንደዚህ ያለ መሬት በፍጹም የለንም፡፡“
የሴክሆን የደስታ ቅዠት የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ በኢትዮጵያ እጅግ በጣም ውድ የሆነውን ለም መሬት በጣም ርካሽ በሆነ ዋጋ ለካሩቱሪ የሰጠው መሆኑን እና ካሩቱሪም በተሰጠው መሬት ላይ የፈለገውን ነገር ማድረግ የሚችል የመሆኑን እውነታ ያረጋግጣል፡፡ በዚህ ታላቅ የሆነ የሎተሪ ቲኬት ባለዕድልነትን በመያዝ አንድ ሰው በዚህ መሬት ላይ ምን ማድረግ ነው የሚጠበቅበት?!
ካሩቱሪ በዓይኑ ሳያይ ያገኘውን መሬት ከተቀበለ በኋላ ስለአዋጭነቱ፣ ስለትርፍ ኪሳራው፣ ስለዕዳውና ስለአጠቃላይ ሁኔታው “ተገቢ የሆነ ጥንቃቄ” በተሞላበት ሁኔታ ማሰላሰል መጀመሩን ሊገልጹ የሚችሉ የተገጣጥሞሽ መረጃዎች አሉ፡፡ (“ተገቢ የሆነ ጥንቃቄ” ለሚለው ሀረግ እንግዳ ለሆናችሁ አንባቢዎቼ ሀረጉ አንድ ገዥ ወይም ደግሞ መዋዕለ ንዋይ ለማፍሰስ የተዘጋጀ ባለሀብት ስለአንድ የንግድ ባህሪ ስላለው ፕሮጀክቱ ስለሀብት፣ ዕዳ፣ ወዘተ አዋጭነት ጥልቅ እና አሳማኝ በሆነ መልኩ የማሰላሰል የማጥናትና የማሰብ ሂደት ነው፡፡)
እ.ኤ.አ በ2009 ካሩቱሪ ጋምቤላ ክልል በተሰጠው የኪራይ መሬት (ነጻ ስጦታ) ላይ የመሰረተ ልማት የማሻሻያ ስራዎችን መስራት ጀመረ፡፡ ከባሮ ወንዝ (በአካባቢው የአኟክ ኗሪ ማህበረሰቦች ኡፔኖ እየተባለ በሚጠራው ወንዝ) እና ከገባሮቹ ከአልዌሮ እና ጂካዎ ወንዞች ላይ የሚነሱትን የጎርፍ አደጋዎች ለመቀልበስ ካሩቱሪ የጎርፍ መቀልበሻ ቦዮችን (የወንዞቹን የተፈጥሮ የፍሰት አቅጣጫ ለመቀልበስ) እና ሌሎችን የግንባታ ስራዎች ሲገነባ ቆይቷል፡፡ ገና ከመጀመሪያው ጀምሮ የካሩቱሪ የንግድ ስትራቴጅዎች ነገሮችን ሁሉ ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ ማየት ጀምሮ ነበር፡፡ ርካሽ የሆኑ የማምረቻ መሳሪያዎችን ከህንድ ወደ ኢትዮጵያ አስገባለሁ የሚል ዕቅድ ነበረው፡፡ ሆኖም ግን የህንድ የማምረቻ መሳሪያዎች በጣም ትልቅ ለሆነ የግብርና የንግድ እርሻ ሊያገለግሉ እንደማይችሉ ወዲያውኑ አስልቶ በማረጋገጥ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ እ.ኤ.አ በ2010 ካሩቱሪ በአሜሪካ የግብርና መሳሪያዎች አምራች ከሆነው ጆን ዲሬ ከተባለው ድርጅት ለማስመጣት ትዕዛዝ ሰጠ፡፡
ካሩቱሪ የእራሱን የሰለጠነ የሰው ኃይል ሊያሟላ የሚችል ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ የመረጠ አይመስልም፡፡ ሆኖም ግን እ.ኤ.አ በ2009 የመጨረሻዎቹ ወራት አካባቢ የሰለጠነ የሰው ኃይል እንደ ጋምቤላ ባለ እሩቅ ቦታ ያውም በጣም ጥቂት በሆኑ ዘመናዊ አገልግሎቶች የችግሩን ውስብስብነት የበለጠ የተወሳሰበ ያደርገዋል፡፡ የችግሩ ውስብስብነት ጉዳይ እንዳለ ሆኖ ከህንድ ሀገር ወደ ጋምቤላ የሚመጡት የቴክኒክ ባለሙያዎች እገዛ እንደዚህ ያለ ታላቅ የግብርና የንግድ ፕሮጀክት ድርጅትን ለመምራት ልምድ የለውም፡፡ እንደዚህ ያሉት የዕቀቅድ ኪሳራዎች ወዲያውኑ ሳይውሉ ሳያድሩ ወጭን በማናር፣ የስራ ፕሮግራምን በማዘግየት፣ የስራ ማስኬጃ ወጭዎችን በከፍተኛ ሁኔታ በማናር እና ገቢን በመቀነስ ግልጽ የሆነ ችግርን ይፋ አደረጉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ከአካባቢው የሚገኙትን የሰለጠነ ጉልበት የሌላቸውን ሰራተኞች በዘመናዊ የግብርና ቴክኒክ በማሰልጠን ብቁ ለማድረግ በሚደረገው ጥረትም የእራሱ የሆኑ ችግሮች ነበሩበት፡፡ ችግሮች በችግሮች ላይ እየተደራረቡ በካሩቱሪ ላይ የችግሮች ሁሉ ቁልሎች ተፈጠሩ፡፡
እ.ኤ.አ መጋቢት 2011 “ኢትዮጵያ፡ ለሽያጭ የቀረበች ሀገር“ በሚል ርዕስ በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ እና በካሩቱሪ ድርጅት መካከል ስለተደረገው ስምምነት ለመጀመሪያ ጊዜ ትችት አቅርቤ ነበር፡፡ በቀደምቶቻቸው ተጠብቆ የኖረውን የጋምቤላ ህዝቦችን ለም መሬት የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ከወገኖቻችን ላይ እየነጠቀ ለውጭ ሀገር ዜጋ አሳልፎ መስጠቱን ማመን አቅቶኝ ነበር፡፡ የካሩቱሪ የመሬት ኪራይ ውል መሬቱን ለማግኘት ለተዋዋለው ኩባንያ የዘመናችን ምርጥ ውል ተብሎ ሊጠራ እንደሚችል ምንም ዓይነት ጥያቄ ሊያስነሳ አይችልም፡፡ “በሳምንት በ150 ፓውንድ ወይም ደግሞ 245 የአሜሪካ ዶላር ከ2,500 ካሬ ኪሎ ሜትር በላይ ስፋት ያለው ያልተነካ ድንግል ለም መሬት ይህም ማለት በእንግሊዝ ሀገር ከምትገኘው ከዶርሴት ግዛት ጋር እኩል የሆነ መሬት ለ50 ዓመታት ከግብር ነጻ በሆነ መልኩ ልታገኝ ትችላለህ፡፡ እንግዲህ እንዲህ ባለ ሁኔታ ነው የጋርዲያኑ ጆን ቪዳል አዲስ የተቋቋመውን እኔ ካሩቱሪ ቅኝ ግዛት እያልኩ የምጠራውን ድርጅት ተወካይ በደስታ ተውጦ እንደ ጅብ የሚያሽካካውን ካርምጅት ሴክሆንን በቪዲዮ በመቅረጽ ለዕይታ እንዲበቃ ያደረገው፡፡
ሴክሆን የካሩቱሪን ሊታመን የማይችል ዕድል ማግኘት አስመልክቶ ለቪዳል ገለጻ በሚያደርግበት ጊዜ እራሱን በደስታ ሲቃ ውስጥ ሆኖ የሚናገር መሆኑን የሚያስተውል አይመስልም ነበር፡፡ “መሬቱ ምንም ዓይነት ነገር ሊበቅልበት የማይችል ነገር የለም፡፡ ለመጀመር ያህል 20,000 ሄክታር ለፓልም ዘይት፣ 15,000 ሄክታር ለሸንኮራ አገዳ እና 40,000 ሄክታር ለሩዝ፣ ለምግብ ዘይት እና ለጥጥ ምርት እርሻ የሚውል ይሆናል፡፡ የውኃ ማጠራቀሚያ፣ የጎርፍ መቀልበሻ እና መንገዶችን ለ15,000 በከተማ ለሚኖሩ ህዝቦች የግንባታ ስራ እናካሂዳለን፡፡ ይህ የመጀመሪያው የፕሮጀክት ምዕራፍ ነው፡፡ በሶስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ 300,000 ሄክታር መሬትን በ60,000 ሰራተኞች እናለማለን፡፡ እዚህ ያለውን የሀገሪቱን ህዝብ እንመግባለን…“ (ካሩቱሪ እዚህ ያለውን የሀገሪቱን ህዝብ እንመግባለን ያለውን ባዶ የማጭበርበር ጉራ መሰረት በማድረግ ነው እንግዲህ መለስ በአምስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያ በምግብ እህል እራሷን ትችላለች በማለት ያወጀው፡፡ ሰማይ ቅርቡ ተግባር እሩቁ የሆነው ባለራዕይ መሪ!)
እ.ኤ.አ ኦክቶበር 2011 ካሩቱሪ እንዲህ ከሚለው የአሌክሳንደር የግጥም ስንኝ የመጀመሪያውን ምርጥ ትምህርት ወስዷል፡፡
በጠባብ ጎዳና ሞኞች ሲንጋጉበት፣
ከላይ ታች እያሉ ሲንፈላሰሱበት፣
ለጊዚያዊ ጥቅም ሲርመሰመሱበት፣
ሳሩን ተመልክተው አደጋን በመፍራት፤
ይህን እና ያንን አመዛዝነው በውነት፣
አማልዕክት ፈሪዎች ታቀቡ ከድርጊት፡፡
እምነተቢስ እምነት በኃይል ተጀቡኖ፣
ደግ እና ክፉውን ሳይመረምር አምኖ፣
መድረሻውን ሳያይ መነሻውን ይዞ፣
በቁንጽል መረጃ እውነታን ፐውዞ፣
ሰክም ሰከም ሲል አዕምሮው ደንዝዞ፣
ጥቅምን ለማሳደድ በሸፍጥ ተመርኩዞ፣
ሩጫን ተማምኖ ማሰብን ሰርዞ፣
ሁሉም ገደል ገብቶ በቅዠት ተናዞ፣
ሲያነባ ይኖራል እንደ ባህር አዞ፡፡
እ.ኤ.አ በጥ ቅምጥ 2011 ካሩቱሪ የባሮን (ኡፔኖን) ወንዝ እና የገባር ወንዞችን መብረቃዊ ማዕበል በመጋፈጥ የተሰሩትን የጎርፍ መከላከያ ግንባታዎች በጎርፍ በማጥለቅለቅ እና የካሩቱሪን 80 ኪ/ሜ ርዝመት ያለውን የጎርፍ መቀልበሻ እንዳለ እንዲሰጥም በማድረግ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል፡፡ ቅጽበታዊ በሆነ መልኩ ካሩቱሪ 50,000 ሜትሪክ ቶን የሚሆን የበቆሎ ሰብሉን ለምልክት እንኳ ሳያስቀር አደገኛው ጎርፍ ሙጥጥ ጥርግ አድርጎ ዶግ አመድ በማድረግ አውድሞበታል፡፡
የካሩቱሪ ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆነው ሳይ ራማክሪሽና ካሩቱሪ የተባለው የእርሱ ኩባንያ 15 ሚሊዮን ዶላር ግምት ያለው ንብረት በጎርፉ ምክንያት እንደወደመበት ይፋ አድርጓል፡፡ በዚያ በደረሰው አሰቃቂ ውድመት ምክንያት የማይሰማ በድን መሆኑን እንዲህ በማለት ገልጾ ነበር፣ “የዚህ ዓይነት የጎርፍ አደጋ እስከ አሁን ድረስ ከዚህ በፊት ተከስቶ አይተን አናውቅም፡፡ ይህ አገር ምድሩን የሚያጥለቀልቅ እብድ የጎርፍ ውኃ ነው፡፡ ድንቄም እብድ ለመሆኑ ማን ነው እብዱ ጃል“!? እብዱ የባሮ ወንዝ ነው ወይስ ካሩቱሪ? ካሩቱሪ ከተፈናጠጠበት ፈረስ ላይ ወርዶ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ውይይት ቢያደርግ ኖሮ አብዛኛው ለማልማት ሲል ተረክቦት የነበረው መሬት ሁሉ በጎርፍ ከሚጥለቀለቀው አካባቢ መሆኑን ይገነዘብ ነበር፡፡ ለዚህም ነው የአካባቢው ማህበረሰብ ያንን መሬት አብዛኛውን ጊዜ ለእንስሳት ግጦሽ እና ለአደን ተግባራት ያውለው የነበረው፡፡ ይህንን ያህል ነው እንግዲህ ስለካሩቱሪ የጥንቃቄ ሂደት፡፡ እ.ኤ.አ በ2011 በጋምቤላ የተከሰተው የጎርፍ መጥለቅለቅ አደጋ ለካሩቱሪ የመጥፎ ዕድል ምልክት ነበር፡፡
እ.ኤ.አ ሚያዝያ 2013 ካሩቱሪ በኬንያ መንግስት በ11 ሚሊዮን ዶላር የግብር ማጭበርበር ክስ ከፍተኛ ቅጣት ተጥሎበታል፡፡ ለአነስተኛ አርሶ አደሮች እርዳታ የሚያደርገው ዴቭሊን ኩዬክ ግሬን/Devlin Kuyek of GRAIN የተባለው ለትርፍ ያልቆመ ድርጅት የሚከተለውን ምልከታ አከናውኗል፣ “የግብር ማጭበርበር ብቻ አይደለም የተፈጸመው፣ ሆኖም ግን ካሩቱሪ የሰብአዊ መብትን በመደፍጠጥ፣ ደካማ የሆነ የጉልበት ስራዎችን በማሰራት፣ የአካባቢ ስነምህዳር ውድመት አደጋን፣ወዘተ…በማስከተል ጨምር ክስ ተመስርቶበታል፡፡ የዓለም ባንክ ቡድን ካሩቱሪ በኢትዮጵያ ለሚያደርገው የልማት እንቅስቃሴ እንኳ የፖለቲካ አለመረጋጋት አደጋ ዋስትና አልሰጠውም፡፡“
እ.ኤ.አ ሰኔ 2013 በጋምቤላ የሚገኘው የካሩቱሪ ፕሮጀክት እጅግ በጣም ከፍተኛ በሆኑ ችግሮች ተተብትቦ የሚገኝ መሆኑ ግልጽ ሆኖ ነበር፡፡ በዚያው ዓመት ካሩቱሪ ከተከራየው ጠቅላላ መሬት ውስጥ 5 በመቶውን ብቻ ነበር ማልማት የቻለው፡፡ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ካሩቱሪ የያዘውን የኪራይ መሬት የይዞታ መጠን እንዲቀንስ አስፈራርቶት ነበር፡፡ ኩባንያው ከፍተኛ የሆነ ዕዳን አጠራቅሟል፣ እናም የመስሪያ ሀብት/ካፒታል የማግኝት ችግር ላይ ወድቆ ነበር፡፡ ታላላቅ መዋለዕለ ንዋይ አፍሳሾች በአስተዳደሩ እና በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ እያደጉ በሚመጡት በፖለቲካው ችግሮች ላይ ከፍተኛ የሆነ የማማረር ችግር ይታያል፡፡ ሌሎች መዋዕለ ንዋያቸውን በጋምቤላ ላይ ለማፍሰስ ቃል ገብተው የነበሩ ባለሀብቶች ወደዚያ በተከሰተው ማጭበርበሪያና ፍልምያ ከህዝብ ጋር ፊታቸውን እንደማያዞሩ ግልጽ አድርገዋል፡፡
ካሩቱሪ የወንጀል ድርጊቶችን ፈጽሟል በሚል በጋምቤላ ባለስልጣኖች ምርመራ ተካሄደበት፡፡ የመሬት ልማት ዕቅዱ እና የካሩቱሪ የእርሻ ማልማት ልምዶች በአካባቢው ስነምህዳር እና የስነህዝብ ሁኔታዎች እንዲሁም በየብስ እና በውኃ አካላት ላይ ግበልጽ የሚታይ ጉዳትን አስከትለዋል፡፡ በሺዎች የሚቆጠሩ በመንደር ምስረታ የተፈናቀሉ ማህበረሰቦች በሰብሎቻቸው ላይ እና በግጦሽ መሬቶቸ ላይ ስለደረሰው ጉዳት በተደጋጋሚ ሲያማርሩ ይደመጣሉ፡፡ የአካባቢው ኗሪዎች የጋራ በሆኑት የግጦሽ መሬቶች ላይ እና ለእንስሶቻቸው በሚውለው ውኃ ውሱንነት ላይ የመረረ ቅሬታ አሰሙ ፡፡ የአካባቢው ኗሪዎች ካሩቱሪ ቃል በገባው የውል ስምምነት መሰረት የማህበረሰብ ዘመናዊ አገልግሎቶችን እንዲያቀርብላቸው እና መልካም ነገሮችን እንዲሰራላቸው እና የአካባቢውም የአኗኗር ባህሎች እንዲከበሩላቸው ጠየቀው ምንም መልስ አላገኙም ።
የጋምቤላ ቀደምት ህዝቦች መኖሪያ የነበረው ገነት በአሁኑ ጊዜ ወደ ገሀነም የቅዠት መኖሪያ በካሩቱሪ አማካኘት ተቀየረ፡፡
በካሩቱሪ ፕሮጀክት ተቀጥረው የነበሩት ጥቂት የሆኑ ሰራተኞች ለስራቸው ተመጣጣንኝ ለሆነ ምንዳ እና ለተሻለ የስራ ሁኔታ ነበር ሲታገሉ የቆዩት፡፡ ካሩቱሪ ለሰራተኞቹ ስለሚከፍለው ምንዳ በሚመለከት ዓለም አቀፍ የመሬት ህብረት/International Land Coalition የተባለ ዓለም አቀፍ ድርጅት ያጠናው ጥናት ዘገባ ውጤት እንዲህ ይላል፣ “በኢትዮጵያ በባኮ እርሻ ልማት (ከጋምቤላ በስተሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ በሚገኘው ሌላው የእርሻ ልማት ድርጅት) ተቀጥረው በመስራት ላይ የሚገኙት የቀን ሰራተኞች በቀን 10 የኢትዮጵያ ብር (0.50 የአሜሪካ ሳንቲም ) ይከፈላቸዋል፡፡ ይህም በሀገሪቱ በእንሰት እርሻ ልማት ተቀጥረው የሚሰሩት የቀን ሰራተኞች ከሚያገኙት 20 ብር (1 የአሜሪካ ዶላር ጋር ሲነጻጸር በግማሽ ያነሰ ሆኖ ይገኛል፡፡ የካሩቱሪ ድርጅት የጥበቃ አባሎች መሳሪያ የታጠቁ ከሆነ በወር 300 ብር (15 ዶላር) የሚከፈላቸው ሲሀን መሳሪያ ያልታጠቁ ከሆነ ደግሞ በወር 200 ብር ደመወዝ (10 ዶላር) ይከፈላቸዋል፡፡ ካሩቱሪ ከዚህ በተጨማሪ በጣም አንገብጋቢ በሆኑ የስራ መደቦች ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ የእርሻ ልማት ሰራተኞችን ከህንድ ሀገር በማምጣት ቀጥሮ ሲያሰራ መቆየቱ ተረጋግጧል፡፡
ታላላቆቹ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች እና የአካባቢ ስነምህዳር ጥበቃ ቡድኖች በጋምቤላ በተካሄዱት የሰብአዊ መብት ድፍጠጣ ወንጀሎች ላይ ምዘና እና ግምገማ madreg jemeru፡፡ እ.ኤ.አ በ2012 ሂዩማን ራይትስ ዎች የተባለው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ‘ሞትን ተቀምጦ መጠበቅ፡ በኢትዮጵያ በጋምቤላ ክልል የግዳጅ የመንደር ምስረታ ፕሮግራም/Waiting Here for Death’ Forced Displacement and Villagization in Ethiopia’s Gambella’ በሚል ርዕስ እንዲህ የሚል ዘገባ አውጥቶ ነበር፣ “በጋምቤላ ክልል ምዕራባዊ ግዛት የመንደር ምስረታ ፕሮግራም በሚል ሰበብ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ቀደምቶቻቸው ይኖሩባቸው ከነበሩበት ቀያቸው በግዳጅ ተፈናቅለዋል፡፡“ እ.ኤ.አ በ2012 ኦክላንድ ኢንስቲትዩት የተባለው ዓለም አቀፍ ድርጅት “በጋምቤላ ክልል በቋሚ ኗሪ ማህበረሰቦች ላይ በመሬት ማልማት ሰበብ የሚደረግ የሰብአዊ መብት ረገጣ ያልተሰሙ ድምጾች/UNHEARD VOICES OF THE HUMAN RIGHTS IMPACT OF LAND INVESTMENT ON INDIGENOUS COMMUNITIES IN GAMBELLA“ በሚል ርዕስ በጋምቤላ ክልል ከመሬት ማልማት እና ከመንደር ሰፈራ ፕሮግራሞች ጋር በተያያዘ መልኩ በሰዎች ላይ ሲፈጸሙ የቆዩትን የሰብአዊ መብት ረገጣዎች አጠቃላይ ሁኔታ አመላክቷል፡፡
እ.ኤ.አ ጥቅምት 2014 የባህላዊ ቅርስ ጥበቃ/Cultural Survival የተባለው ዓለም አቀፍ ድርጅት እንዲህ የሚል ዘገባ አቅርቧል፣ “በኢትዮጵያ በጋምቤላ ክልል የቋሚ ኗሪ ህዝቦች ሞት፣ ንብረትን ማጣት እና ከዚህ አስከፊ የሆነ ችግር ውስጥ ለመውጣት የሚደረግ ዘለቄታዊ ትግል“ በሚል ርዕስ ባወጣው ዘገባ መሰረት “የመንደር ምስረታ ፕሮግራም ከህወሀት በፊትም ችግር የነበረበት ነበር“ በማለት ዘገባውን ግልጽ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ በ1986 የባህላዊ ቅርስ ጥበቃ/Cultural Survival የተባለው ዓለም አቀፍ ድርጅት በሩብ ዓመቱ ያወጣው ዘገባ እንዲህ የሚል ነበር፣ “የኢትዮጵያ መንግስት 17,553 አባወራዎችን/የቤተሰብ ኃላፊዎችን ከትግራይ በማንሳት እስከዚያ ድረስ ሰፈራ ወዳልተካሄደባቸው የጋምቤላ ክልል ድንግል እና ለም መሬቶች እየወሰደ በማስፈር እና ከዚያ ሌላ እንደዚያ ያለ ቋሚ ማህበረሰቦች የሚኖሩባቸው እንደ አኟክ ያሉ ማህበረሰቦች እንዳልነበሩ መንግስት ምስክርነቱን ሰጥቷል“ ብሎ ነበር፡፡
ካሩቱሪ በጋምቤላ ሲያካሂድ ከነበረው ፕሮጀክቱ ጋር በተያያዘ መልኩ ሁሉንም የሚካሄዱበትን የሰብአዊ መብት ረገጣ ውንጀላዎች አልፈጸምኩም በማለት ሲያስተባብል ቆይቷል፡፡ በእርሱ ፕሮጀክት እና በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የሰፈራ መንደር ፕሮግራም መካከል ምንም ዓይነት ግኑኘት የለም በማለት ሲያስተባብል ቆይቷል፡፡ ካሩቱሪ ይቀርቡበት የነበሩትን ክሶች ፍጹም መሰረተቢስ እና የምዕራቡ ዓለም ጭፍን የጥላቻ መገለጫዎች ናቸው በማለት ምላሽ ሲሰጥ ቆይቷል፡፡
እ.ኤ.አ ሚያዝያ 2014 የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ የልማት መምሪያ እና የዓለም ባንክ በጋምቤላ ህዝቦች ላይ መጠነሰፊ የሆነ ጉዳት ላደረሱ ፕሮጀክቶች የገንዘብ እርዳታ እንዲያደርጉ የህግ ተጠያቂነት ወይም ደግሞ ውስጣዊ ድርጅታዊ ምርመራ መደረግ ተጀመረ፡፡ እ.ኤ.አ መስከረም 24/2012 በተጻፈ ደብዳቤ ስማቸው ያልተጠቀሰ የአኟክ ብሄረሰብ ተወላጅ የሆኑ በጋምቤላ የኢትዮጵያ መሰረታዊ አገልግሎቶች ጥበቃ ፕሮጀክት/Basic Services Project (PBS) በሚል የዓለም ባንክ በሚሰጠው የገንዘብ እርዳታ ህዝቡ በከፍተኛ ደረጃ የጉዳት ሰለባ መሆኑን በመግለጽ ይህንን አስመልክቶ በጉዳዩ ላይ ምርመራ እንዲካሄድ ጥያቄ አቅርቦ ነበር፡፡ በዚህም መሰረት የምርመራ ቡድን እንዲቋቋም ተደርጎ እ.ኤ.አ ጥቅምት 2014 የዓለም ባንክ የምርመራ ቡድን/Inspection Panel አስተማማኝነት ያለው ዘገባ በማቅረብ በድረ ገጽ እንዲለቀቅ ተደረገ፡፡ በጥናት ቡድኑ ዘገባ መሰረት የዓለም ባንክ አውቆም ይሁን ሳያውቅ በፕሮጅክቱ አማካይነት በጋምቤላ ህዝቦች ኗሪ ማህበረሰብ ላይ ጉዳት ያደረሰ መሆኑን በግልጽ አመላክቷል፡፡
እ.ኤ.አ ጥር 2015 ካሩቱሪ ፕሮጀክቱን መዝጋቱን ይፋ አደረገ፡፡ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የግብርና ኢንቨስትመንት እና የመሬት አስተዳደር ኤጀንሲ ዳይሬክተር የሆኑትን አበራ ሙላትን ሪፖረተር ጋዜጣ ጠቅሶ እንደዘገበው ካሩቱሪ ውስጣዊ አስተዳደሩን ተከትሎ ለኪሳራ ተዳርጓል በማለት ይፋ አድርጓል፡፡ በዚሁም ተመሳሳይ ዘገባ መሰረት የካሩቱሪ ዋና ስራ አስፈጻሚ/Chief Executive Officer የሆኑት ራም ካሬቱሪ እንዲህ የሚል ዘገባ አሰምተዋል፣ “15 ሚሊዮን ዶላር ሊያወጣ የሚችል ዋጋ ያላቸው የማምረቻ መሳሪያዎች ድርጅቱ ያለበትን ዕዳ ለመክፈል በሚል በመሸጥ ላይ ናቸው፡፡ ካሩቱሪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ከዳሽን እና ከዘመን ባንኮች ብድር የወሰደ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ኩባንያው ያለበት ብድር ከ170 ሚሊዮን ብር በላይ መሆኑን እና ዋና ስራ አስፈጻሚው ይህንን ዕዳ በዚህ ወር መጨረሻ ከፍሎ ለማጠናቀቅ እና ከዕዳ ነጻ ለመሆን እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡“
የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የመሬት ማጭበርበር የቁማር ጨዋታ፣
የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ለካሩቱሪ ያደረገው የመሬት ኪራይ (ነጻ ስጦታ) እ.ኤ.አ በ1960ዎች እና 70ዎቹ በዩናይትድ ስቴትስ በተለይም በፍሎሪዳ ግዛት ሲደረግ የነበረውን የመሬት ማጭበርበር ዘረፋ አስታወሰኝ፡፡ በዚያን ጊዜ የመሬት አጭበርባሪዎች በጣም ውብ የሆኑ የደን መሬቶችን በጣም ጥቂት በሆኑ ዶላሮች በጸሐያማዋ ፍሎሪዳ ለመኖሪያ ቤት ህንጻ ግንባታ መስሪያነት ማስታወቂያዎችን ያወጡባቸው ነበር፡፡ ከአካባቢያዊ ስነምህዳር አንጻር በማየት ጠንከር ያለ ገለጻ ያደርጉ ነበር፡፡ ያ የተዋበ እና ድንቅ የደን መሬት በእርግጥ ረግረጋማ መሬት ነበር፡፡ ፍሎሪዳ የገዙትን ያንን የተዋበ መሬት ወይም ደግሞ ገና ወደፊት ለመግዛት ዕቅድ ያላቸው ገዥዎች ለማየት በሚሄዱበት ጊዜ ሻጮቻቸው በዓይኖቻቸው አተኩረው በመመልከት የጉዳቱ ሰለባ ለሆኑ ሰዎች የእናንተ ንብረት ከዚያ ከምታዩት ጫካ አድማስ አለፍ ብሎ ነው ይሏቸው ነበር፡፡ እነዚህ የጉዳት ሰለባዎች መንገዶችን እንሚሰሩላቸው፣ መሰረታዊ አገልግሎቶችን እንደሚያቀርቡላቸው እና በቅርቡም የልማት ቦታዎች ግንባታ እንደሚጀመር ያረጋግጡላቸው ነበር፡፡ ሆኖም ግን ስምምነቶቹ ከጠረጴዛው ላይ ያሉ ስለሆነ ዛሬውኑ መፈረም እንዳለባቸው ይገልጹለቸው ነበር፡፡ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች እነዚያን እረግረጋማ መሬቶች በስልክ ግንኙነት በማደረግ ገዟቸው እናም ለምንም ነገር የማይጠቅም ኢንቨስትመንት ነው በማለት ገንዘቡን በቸክ ገቢ ያደርጉላቸው ነበር፡፡ ሁሉም ከስረው ቀሩ።
እንደዚሁም ደግሞ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ዓይነ ሰፊ በሆኑ የዲስፖራ መዋዕለ ንዋይ አፍሳሾች እና በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ አማካይነት የመሬት ልማት እየተባለ እየተሰጣቸው የማጭበርበር እና የዘረፋ ስራ ሲካሄድ ተመልክቻለሁ፡፡ አንዱ ዋና የማጭበርበር ዘዴ ግዥው በሚፈጸምበት ጊዜ በአሜሪካ ዶላር ገንዘብ (በሀገሬው ገንዘብ አይፈቀድም) የተወሰነ ክፍያ መክፈል እና ቀሪውን ደግሞ በቀጣይነት ለመክፈል ስምምነት ማድረግ ነው፡፡ የዚህ ዓይነት ስምምነት ሰለባ የሆኑት አስቀድመው የከፈሉት ገንዘብ ሳይመለስ እና ቃል የተገባላቸውም የኮንዶሚኒየም ቤት ግንባታ ሳይገነባ ከስረው ይቀራሉ፡፡
ሌላው የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ኢትዮጵያውያንን/ትን ለማታለል የሚጠቀሙበት እና ለማመን የሚያስቸግረው ዘዴ የመኖሪያ ቤት ልማት ፕሮጀክት በሚል በአዲስ አበባ ከተማ ቦታ ለማግኘት ሲባል የኮንዶም የግንባታ ስራ ለመጀመር አስቀድሞ በአሜሪካ ዶላር ክፍያ እንዲፈጽሙ ይደረጋሉ፡፡ የግንባታ ስራው ለመጠናቀቅ ትንሽ ሲቀረው አጭበርባሪዎቹ መሬት አዳዮች ዲያስፖራ ኢትዮጵያውያን መዋዕለ ንዋይ አፍሳሾችን መጠኑ ከፍ ያለ ገንዘብ (የኮንትራት ስምምነቱን ሶስት ጊዜ ያህል በመጨመር) እንዲከፍሉ ወይም ካልሆነ ደግሞ ይህንን በመጀመሪያ ያስገቡትን ገንዘብ መልሰው እንዲወስዱ ይነግሯቸዋል፡፡ የመሬት ዘረፋው አጭበርባሪዎች በዲያስፖራው የተሰጣቸውን የመጀመሪያውን ክፍያ ለግንባታ ካዋሉ በኋላ ለመጠናቀቅ ትንሽ የቀረውን የኮንዶሚኒየም ግንባታ ቤት በአሁኑ ጊዜ የቤት ገበያ ዋጋ እየጨመረ ስለሆነ በከፍተኛ ዋጋ ለሌላ ሊሸጡት ይችላሉ ፡፡ የመጀመሪያዎቹ መዋዕለ ንዋይ አፍሳሾች ያልተጠናቀቀውን የኮንዶሚኒየም ቤት የንብረት ባለቤትነት ጥያቄ በሚያቀርቡበት ጊዜ አጭበርባሪ ዘራፊዎቹ ፈቃደኛ ባለመሆን ይቃወማሉ፡፡ መዋዕለ ንዋይ አፍሳሾች ጉዳዩን ወደ ህግ በመውሰድ አሸናፊ ቢሆኑም አጭበርባሪ ዘራፊዎቹ ይግባኝ ይጠይቁ እና በሌላ ዳኛ እንዲታይ በማድረግ እነርሱ በሚፈልጉት መልኩ እንዲሻር እና ለእነርሱ በሚጠቅም መልኩ እንዲወሰንላቸው ያደርጋሉ፡፡ ምን ዓይነት አጭበርባሪነት ነው እባካችሁ! በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የቤት ልማት ግንባታ ሰበብ የሚጭበረበሩ የዲያስፖራ ኢትዮጵያውያን/ት የተሰበረ ልብ እንዴት የሚያሳዝን ሁኔታ ነው!
የከተማ የቤት ልማት የማጭበርበር ድርጊቶች “የናይጀሪያ 419 ማጭበርበር” እየተባለ የሚጠራውን አስታወሰኝ፡፡ (እ.ኤ.አ በ1990ዎቹ የመጨረሻዎቹ እና በ2000ዎቹ የመጀመሪያ ወራት አካባቢ የጫካውን ዳክየ ማሳደድ በሚል በምንም ዓይነት መልኩ ሊደረስበት የማይችልን በፋክስ ማሽን የተከናወነን የገንዘብ ማጭበርበር ጉዳይ አስመልክቶ ጥቂት ደንበኞቸን በመወከል ጉዳዩን ይዠው ነበር፡፡) አጭበርባሪዎቹ መንግስታዊ በሆነው በናይጀሪያ ብሄራዊ ፔትሮሊየም ኮርፖሬሽን ዳይሬክተር ስም የተጻፈ ደብዳቤ በማስመሰል በፋክስ እንዲላክ ያደርጋሉ፣ ወይም ደግሞ በናይጀሪያ ልዑል፣ ጀኔራል ወይም ለአዕምሮ የበላቤትነት ከፍያ ገቢ እንዲደረግ በሚል በማጭበርበር ብዙ ገንዘብ (አብዛኛውን ጊዜ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ) ከናይጀሪያ እንዲወጣ ይደረጋል፡፡ የገንዘብ ዝውውሩ ከተጠናቀቀ በኋላ የማጭበርበር ድርጊት የተፈጸመበት የጉዳት ሰለባ ከተላከው ገንዝብ ውስጥ የተወሰነ መቶኛ ድርሻ እንደሚሰጠው ይነገረዋል፡፡ አንድ ዋና ማነቆ የሆነ ቸግር አለ፡፡ ይኸውም የጉዳት ሰለባው ለማስፈጸሚያ ሂደቱ በሚል በርካታ የሆነ በሺዎች የሚቆጠር ገንዘብ እንዲልክ ይጠየቃል፡፡ ወዲያውኑ አጭበርባሪዎች ገንዘቡን እንዳገኙ እራሳቸውን በመሰወር የውኃ ሽታ ይሆናሉ፡፡ ይህም ማለት በአዲስ አበባ ከተማ በኮንዶሚኒየም ቤቶች ግንባታ ላይ እንደሚደረገው የማጭበርበር ስራ ማለት ነው!
ካሩቱሪ እንደ ፈሎሪዳ ዓይነት የመሬት ማጭበርበር ድርጊት ተፈጽሞበት እንደሆነ እስከ አሁን ድረስ እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ በሁሉም ዘንድ አካባቢው የጎርፍ ጥቃት ያለበት መሆኑ እየታወቀ አንድ ኩባንያ እንዴት በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ በማውጣት ለኪሳራ እንደተዳረገ ለእኔ ሊታሰብ የማይችል አስቸጋሪ ጉዳይ ነው፡፡ ካሩቱሪ የስነ ምህዳር (የአካባቢ ጉዳትን ጨምሮ) ዝርዝር ጥናት አላካሄደምን? ካሩቱሪ ከአካባቢው ማህበረሰብ መሪዎች እና ከህዝቡ ጋር ውይይት አላደረግምን? ምናልባትም አድርጎ ሊሆን ይችላል፣ ሆኖም ግን በሰከነ እና ጥንቃቄን በተላበሰ መልኩ ሳይሆን የጥናቱን ውጤት ወደ ጎን በመተው በችኮላ ወደ ስራው ገብቶበት ሊሆን ይችላልን? ካሩቱሪ የአካባቢ ጥናት አካሂዶ ቢሆን ኖሮ የጥናት ውጤቱ ሊሰጠው የሚችለው መረጃ ያ አካባቢ ለፕሮጀክቱ ሊሆን የሚችለው ለግጦሽ እና ለአደን እንጅ በየጊዜው የሚከሰት የጎርፍ አደጋ የሚከሰትበት አካባቢ በመሆኑ ምክንያት ለሰብል ልማት ሊውል አይችልም የሚል ይሆን ነበር፡፡ ካሩቱሪ የሰራቸው አነስተኛ የጎርፍ መቀልበሻዎች፣ የመስኖ መፋሰሻዎች እና ቦዮች ኃይለኛውን እና ታላቁን የባሮን (ኡፔኖን) ወንዝ እና የገባሮቹን ጎርፍ ሊከላከል ይችላል ተብሎ ይታሰባልን? ምናልባትም በጣም ላልገረም እችላለሁ፡፡ በፍሎሪዳ የመሬት ማጭበርበር የተሳተፉ የመሬት ባለቤት አታላዮችም የአካባቢውን ረግራጋማ ቦታዎች ሁሉ በሙሉ አንጠፍጥፈን ለልማት ስራ እናውለዋለን የሚል ዓላማ ሲያራምዱ ነበር፡፡ በረግራጋማ ቦታ እና በጎርፍ አካባቢ መካከል ጉልህ የሆነ ልዩነት ይኖራልን? የሰርከስ ታላቅ ባለሙያ የሆነው ፒ.ተ. ባርነም በአንድ ወቅት እንዲህ ብሎ ነበር፣ “በእያንዳንዷ ደቂቃ የሚወለድ ሞኝ ሞልቷል“፡፡
የጋምቤላ ህዝቦች እና ሌሎች አናሳ ብሄረሰቦች ከቀደምቶቻቸው የተረከቧቸውን መሬቶች ደህንነት ለመጠበቅ የአጋር ጓደኞቻቸውን ሙሉ ድጋፍ ይሻሉ፣
እ.ኤ.አ እስከ 2006 ድረስ ስለጋምቤላ ወይም ደግሞ እዚያ አካባቢ ስለሚኖሩት ህዝቦች ብዙም ነገር አላውቅም ነበር፡፡ ታዋቂው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የሆነው ሂዩማን ራይትስ ዎች “በጋምቤላ ክልል በሰው ልጆች ላይ የተፈጸመ ወንጀል/Crimes Against Humanity in Gambella Region“ በሚል ርዕስ እ.ኤ.አ ታህሳስ 2003 በመለስ ዜናዊ እና በእርሱ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ በተቀነባበረ ሴራ በምዕራብ ጋምቤላ የአኟክ ህዝቦች ላይ የጅምላ ግድያ እልቂት፣ አስገድዶ መድፈር እና ማሰቃየት እስከፈጸሙበት ጊዜ ድረስ ስለአካባቢው ብዙም አላውቅም ነበር፡፡ በእርግጥ እ.ኤ.አ በ2005 በኢትዮጵያ ተካሂዶ በነበረው ሀገር አቀፍ ምርጫ የተከሰተውን ውዝግብ ተከትሎ መለስ ዜናዊ በማን አለብኝነት እና በአረመኔነት እኩይ ምግባሩ በሰላማዊ መንገድ ቅሬታቸውን ለመግለጽ ወደ አደባባይ በወጡ ንጹሀን ዜጎች ላይ የጥይት እሩምታ እንዲከፈት አድርጎ ሮጠው ያልጠገቡ እምቦቃቅላ ህጻናተን እና ሌሎቹን ወገኖቼን ሁሉ በአደባባይ ማስጨረስ ከጀመረ በኋላ ነው ፍላጎት ያደረብኝ እና ወደ ኢትዮጵያ ፖለቲካ ዘው ብየ በመግባት ነገሮችን ሁሉ መከታተል የጀመርኩት፡፡ ያ የመለስ አሰቃቂ የንጹሀን ዜጎች እልቂት የጣለው ጠባሳ በህይወቴ ላይ ልዩ የሆነ አጋጣሚን በመፍጠር በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጥበቃ ላይ ሙሉ በሙሉ እንድገባ እና የዜግነት ድርሻዬን እንድወጣ አድርጎኛል፡፡
በጋምቤላ ህዝቦች ላይ ስለተፈጸመው የሰብአዊ መብት ወንጀል ለመጀመሪያ ጊዜ እ.ኤ.አ በመስከረም 2006 ነው ሙሉ ለሙሉ ግንዛቤ ያገኘሁት፡፡ ኦባንግ ሜቶ የተባሉት የኢትዮጵያ ወጣት የሰብአዊ መብት ተሟጋች እና የጋምቤላ የአኟክ ህዝቦች የፍትህ ምክር ቤት ዳይሬክተር/Anuak People’s Justice Council Director “በዴሞክራሲ ላይ የተፈጸመ ክህደት/Betrayal of Democracy“ በሚል ርዕስ አዘጋጅተውት በነበረው ዘገባ ላይ በካሊፎርኒያ ዩኒቨርስቲ ሎስ አንጀለስ/University of California, Los Angeles (UCLA) በመገኘት ንግግር እንዳደርግ በተጋበዝኩበት ወቅት መለስ በጋምቤላ ህዝቦች ላይ የፈጸመው እልቂት ገና ትኩስ ነበር፡፡ ኦባንግ ያንን ዘጋቢ ሰነድ በካናዳ ከሚገኘው ከሳስካቸዋን ዩኒቨርስቲ/University of Saskachewan ጋር በመተባበር ነው አዘጋጅተውት የነበረው፡፡ ኦባንግ “ያ ዘጋቢ ሰነድ በመንግስት ዴሞክራሲ አለ እየተባለ በሚሰበክባት ሀገር እንደዚህ ያለ አሰቃቂ የሰብአዊ መብት ድፍጠጣ በኢትዮጵያ ተንሰራፍቶ እንዳለ እና በአሁኑ ጊዜም በአኟክ ማህበረሰብ እና በሌሎች ህዝቦች ላይም ቀጥሎ እንዳለ መረጃ የሚያቀርብ ሰነድ ነው” በማለት ነበር ገለጻቸውን ያደረጉት፡፡
ከኦባንግ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ፊት ለፊት የተገናኘነው እ..ኤ.አ በ2006 የጸደይ ወቅት ኤች. አር 4423 (የኢትዮጵያ የ2005 የማጠናከሪያ ድንጋጌ)/H.R. 4423 (Ethiopia Consolidation Act) የሚለው ሰነድ በዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ጉዳዮች ንኡስ ኮሚቴ ተዘጋጅቶ በተጠናቀቀበት ጊዜ ነበር፡፡ ያንን ዕለት በንኡስ ኮሚቴው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ ሆኘ በካሊፎርኒያ ዩኒቨርስቲ ሎስ አንጀለስ ላይ ያደረግሁትን ንግግር አስታወስኩ፡፡ ኦባንግ የምስክርነት ቃላቸውን በሚሰጡበት ወቅት ከመነጋገሪያው ጀርባ ሆኘ በአጽንኦ እመለከት ነበር፡፡ ኦባንግ በታላቅ ስቃይ ላይ ያሉ ይመስሉ ነበር፡፡ እንዲህ ሲሉ አዳምጥ ነበር፣ “በዛሬው ዕለት ስለአኟክ ወገኖቻችን እናገራለሁ፡፡ እኔ የአኟክ ማህበረሰብ ተወላጅ ነኝ፡፡ ጋምቤላ ነው ተወልጀ ያደግሁት፡፡ ስሜታዊነትን በተላበሰ መልኩ ንግግር የማደርግ ከሆነ እባካችሁን ችግሬን ተገንዝባችሁ ይቅርታ እንድታደርጉልኝ እጠይቃለሁ፡፡“
ኦባንግ በርካታ ኢትዮጵያውያን/ት በታደሙበት ቦታ ንግግር ወደሚደረግበት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ፈጠን ብለው በመሄድ እንዲህ በማለት ንግግራቸውን ቀጠሉ፣ “አሁን ንግግር በማደርገበት ጊዜ ዛሬ አብዛኞቻችሁ የእኔን ፊት በመመልከት ኢትዮጵያዊ እንዳልሆንኩ አድርጋችሁ ልትገምቱ ትችላላችሁ፡፡ ለጥቂት ኢትዮጵያውያን/ት ጀርመን ልመስል እችላለሁ፡፡ በዛሬው ዕለት እንኳ ልገለል እችላለሁ፡፡ አኟክ የምትለዋን ቃል የተነፈሷት ብቸኛው ሰው ሊቀመንበር ስሚዝ ናቸው፡፡“ የኦባንግ ንግግሮች እየሞቀ እንዳሚሄድ የቦንብ ባሩድ እኔም እየሞቀኝ መጣ፡፡ ኦባንግ ስለምን ይናገሩ እንደነበር በእርግጠኝነት አውቅ ነበር፣ ሆኖም ግን እንደዚህ ያለውን የቤት ዉስጥ ጉድ በመድረክ አደባባይ የዩኤስ የተለያዩ ግዛቶች የምክር ቤት አባላት በጥንቃቄ እየመዘገቡ በሚይዙበት ሁኔታ አያለሁ የሚል የስነ ልቦና ዝግጅት አልነበረኝም፡፡
ኦባንግ እውነታውን አፍርጠው እና አፍረጥርጠው እንደዚያ ባለ ግልጽ እና ድፍረትን በተላበሰ መልኩ ያቀርቡታል የሚል ግምት አልነበረኝም፡፡ አይበገሬው ኦባንግ እውነተኛ የአርበኝነት ወኔን እና በእራስ መተማመንን በተላበሰ መልኩ ንግግራቸውን እንዲህ በማለት ቀጠሉ፣ “አኟኮች የኢትዮጵያ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ዜጎች ናቸው፡፡ ኢትዮጵያውያን/ት ይህንን እውነታ የመቀበል ግዴታ አለባችሁ፡፡“ ይህንን በምሰማበት ጊዜ ጭንቅላቴን ዝቅ በማድረግ ብቻ ኃፍረትን በተከናነበ መልኩ መሬት መሬቱን መመልከት ጀመርኩ፡፡ ኦባንግ እውነታውን አፍርጠው እንደተናገሩ አሳምሬ አውቃለሁ፣ ሆኖም ግን ይህንን አውንታ በአደባባይ በምስለ ትዕይንት/ኤግዚቢሽን ከሌሎች ኢትዮጵያውያን/ት ጋር በኃፍረት አንገታችንን ደፍተን እናየዋለን የሚል ግምት አልነበረኝም፡፡ ኦባንግ ስለአኟክ ህዝቦች እልቂት በማውሳት ለእነርሱ የሚጠቅም አንድ ነገር መደረግ እንዳለበት እንዲህ በማለት የተማጽዕኖ ንግግራቸውን ቀጠሉ፣ “በጣም አናሳ የሆንን ብሄረሰብ ነን፡፡ የአኟክ ህዝብ ብዛት ከ100,000 አይበልጥም፡፡ ይህም እኔን ጨምሮ ቢሆን ነው፡፡“ በአኟክ ህዝቦች ላይ የተፈጸመውን እልቂት የአሜሪካ ህዝብ እንዲገነዘበው እዚህ በአሜሪካ ምክር ቤት አባላት/የኮንግረስ አባላት ፊት ቆሜ ለፍትህ እና ለርትዕ ስል ጩኸቴን በማሰማት ላይ እገኛለሁ በማለት ተናግረዋል፡፡ ኦባንግ እዚህ የመጣሁት ወገኖቼ በኢትዮጵያ መንግስት በመወረር ተጨማሪ ሰቆቃ እንዳይፈጸምባቸው የሰይጣናዊ አካሄዱን ለማስቆም እና ለእነዚህ ምስኪን ወገኖቼ የአሜሪካ የምክር ቤት አባላት እገዛ በእጅጉ እንደሚያስፈልጋቸው በማመን ነው በማለት አጽንኦ በመስጠት ንግግራቸውን ቀጥለዋል፡፡ ንግግራቸውን በመቀጠል 1,600 የሚሆኑ ወንድሞቻቸቸው፣ እህቶቻቸው፣ ዘመዶቻቸው፣ ጓደኞቻቸው እና ጎረቤቶቻቸው በኢትዮጵያ መንግስት ታጣቂ ኃይሎች ተገድለዋል፣ እንዲያልቁም ተደርገዋል ብለዋል፡፡ ሌሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖች ደግሞ በኡሁኑ ጊዜ በመጠለያ ውስጥ ሆነው እርዳታ ጠባቂ ናቸው፡፡ በዚያ የጩኸት ማሰሚያ የስብስባ አዳራሽ ውስጥ በአሁኑ ጊዜ በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የዘር ማጽዳት ወረራ በአደገኛ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ አስቸኳይ እርዳታ እንዲደረግላቸው እዚያ በመገኘት እየጮኹላቸው ያሉት ብቸኛው ኢትዮጵያዊ ኦባንግ ብቻ ነበሩ፡፡ ቪቫ ኦባንግ! ኢትዮጵያዊው ጀግና የሰብአዊ መብት ተሟጋች!
ኦባንግ ስለአኟክ ህዝቦች ተስፋየለሽ የጨለማ ህይወት እንዲህ በማለት ተናግረዋል፣ “በአሁኑ ጊዜ የአኟክ ህዝቦች ተስፋ የላቸውም፡፡ እናም የዓለም አቀፉ ማህበረሰብም ደንታቢስ በመሆን ማድረግ ያለበትን የሞራል ግዴታ ባለመወጣቱ በፈተናው ወድቋል፡፡“
በዚያ ዕለት በዚያ የመሰብሰቢያ አዳራሽ በመገኘት ለፍትህ እና ርትዕ ሲባል በዩኤስ አሜሪካ የምክር ቤት አባላት ፊት ፍቅርን በተላበሰ መልኩ በጽናት ቆሞ ለህዝቦቹ የተናገረ ከኦባንግ ውጭ ማንም አልነበረም፡፡ በምስል ትዕይንት ማሳያው ጀርባ ተቀምጨ እራሴን በህፍረት ማቅ ውስጥ ተወሽቆ አገኘሁት፡፡
እውነታው ተግልጦ እና ተፍረጥርጦ ሲታይ ግን እራሳቸውን ኢትዮጵያዊ/ት አድርገው የሚቆጥሩ በርካታ ናቸው፣ ሆኖም ግን የአኟክን ወይ ደግሞ ሌሎችን በቋሚነት ሰፍረው የሚኖሩትን አናሳ ብሄረሰቦች በደቡብ ኢትዮጵያ የኦሞ ማህበረሰብ ህዝቦችን ጨምሮ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ/ት መሆናቸውን ያለመቀበል ሁኔታ ይታያል፡፡ አናሳ ማህበረሰቦችን በተመለከተ በአሁኑ ጊዜ እንኳ የተሳሳተ እንዲያውም በእጅጉ የከፋ ነገር አለ፡፡ በአሁኑ ጊዜ ስለእነዚህ አናሳ ማህበረሰብ የጎሳ ቡድን ወገኖቻችን ደንታ የሌለን ስንቶቻችን እንዳለን ቤት ይቁጠረው፡፡ ያ ዕልቂት ከተፈጸመበት ከአስር ዓመታት በኋላም እራሴን በታላቅ ኃፍረት ውስጥ ተደብቆ አገኘሁት፡፡ የኢትዮጵያን ቅርስ እና ኩራት እወዳለሁ የሚል ኢትዮጵያዊ/ት ሁሉ የጋምቤላን ወይም ደግሞ የአሞን ህዝቦች ወንድምነት እና እህትነት ሙሉ በሙሉ በማይቀበሉት ወገኖቻችን ላይ ልናፍር ይገባል፡፡ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ በአሜሪካ በፍሎሪዳ ግዛት እንደተደረገው የመሬት ማጭበርበር ዝርፊያ ቅሌት ሁሉ በጋምቤላ ክልል ቀደምቶቻችን ለዘመናት ሰፍረውበት የኖሩትን ለም እና ድንግል መሬት በማጭበርበር እና በመሸጥ ባደረጉት ቅሌት ሊያፍሩ ይገባል፡፡ የጋምቤላ ህዝቦች በመንደር ሰፈራ ፕሮግራም እና በተፈጸመባቸው የግድያ እልቂት የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ሊያፍር ይገባል…
በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ እና በእነርሱ የድብቅ የጥቅም ተጋሪ የሸፍጥ ኢንቨስትመንት ዘራፊዎች (በቅርቡ ለእንግሊዝኛ ቋንቋ ዘራፊዎችን ከኢንቨስትመንት ጋር ለማቆራኘት የተጠቀምኩበት) በጋምቤላ ወይም ደግሞ በኦሞ ህዝቦች ወገኖቻችን ላይ የሚፈጸመውን የመሬት ነጠቃ እና የግድያ እልቂት ስናይ ማልቀስ፣ መጮህ እና እሪ ማለት አለብን፡፡ በምንም ዓይነት ሁኔታ ዝም ማለት የለብንም፡፡ ደግመን ደጋግመን እሪ እንበል፡፡
እንደ ጋምቤላ ህዝቦች ሁሉ በአሁኑ ጊዜ በደቡብ ኢትዮጵያ በኦሞ ወንዝ ሸለቆ የሚኖሩ ወገኖቻችንም እንደዚሁ የአካባቢ ስነምህዳር አደጋ ተጋፍጦባቸው ይገኛሉ፡፡ ይህ የከፋ ችግር፣ ወገኖቻችንን ለረኃብ፣ በቋሚነት ከሚኖሩበት ቦታ የመፈናቀል እና ለግጭት መንስኤ መሆን ብቻ አይደለም አሳሳቢ ሆኖ የሚገኘው፣ ሆኖም ግን እነዚህ ህዝቦች ለዘመናት ሲኖሩበት የነበረው የአካባቢ ስነምህዳር በአጠቃላይ እንዲወድም ተደርጎ ህይወት ያለው ነገር ሁሉ በአጠቃላይ እንዲጠፋ የሚደረግበት ክስተት ሊመጣ እንደሚችል ልናስተውል ይገባል፡፡
የዓለም አቀፍ ወንዞች/International Rivers የተባለው ዓለም አቀፍ ድርጅት ባለፈው ሳምንት ባወጣው ዘገባ መሰረት የጊቤ 3ን ግድብ ለመሙላት በሚል ምክንያት የሚደረገው እንቅስቃሴ በታችኛው የኦሞ ሸለቆ በሚኖሩ ህዝቦች እና በአካባቢው ስነምህዳር ላይ አስከፊ የሆነ ጉዳትን ሊያመጣ እንደሚችል አስጠንቅቆ ነበር፡፡ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የአካባቢውን ስነምህዳር በጠራራ ጸሐይ በማውደም እና በኦሞ ህዝቦች ላይ ኢሰብአዊ የሆኑ ጭራቃዊ ድርጊቶችን በመፈጸም ሰብአዊ መብቶቻቸው ሲደፈጠጡ አይኖቻችንን መጨፈን፣ ጆሮዎቻችንን መድፈን እና ከንፈሮቻችንን መምጠጥ ዋጋ የለውም፡፡ መናገር አለብን፡፡ ድምጻችንን ከፍ አድርገን መጮህ አለብን!
በጋምቤላ ለተፈጸመው የዘር ማጥፋት እና በህዝቦች ላይ ለተፈጸመው የሰብአዊ መብት ረገጣ ወንጀል ኃላፊነቱን የሚወስደው ማን ነው?
በተባበሩት መንግስታት የሮም ስምምነትን በመተላለፍ በጋምቤላ ህዝቦች ላይ የዘር ማጥፋት እና የሰብአዊ መብት ረገጣ ወንጀሎች መፈጸማቸውን ከምንም ጥርጣሬ በላይ ማረጋገጥ ችያለሁ፡፡ የሮም ስምምነት አንቀጽ 15 የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ዋና አቃቤ ህግ የሰብአዊ መብት ረገጣ ወንጀል ተፈጽሟል የሚል ጥርጣሬ ካለ (በICC ዋና አቃቢ ህግ ውሳኔ መሰረት) በተገኘው መረጃ መሰረት ክስ በመመስረት ሰብአዊ መብት ረጋጮችን ወደ ፍትህ አካሉ ማቅረብ እና ምርመራውን መቀጠል እንደሚቻል በግልጽ አስቀምጧል፡፡
በሮም ስምምነት አንቀጽ 6 (c) ሆን ተብሎ ታስቦበት እና ተመክሮበት የሰዎችን ህይወት ለማጥፋት እና የአንድን ማህበረሰብ ኢላማ አድርጎ ለሚፈጸም የዘር ማጥፋት ወንጀል ማረጋገጫ ይፈልጋል፡፡ በአንቀጽ 6 (b) በህዝቦች ላይ ሆን ብሎ የአካል ወይም ደግሞ የመንፈስ ጉዳት ያደረሰ ከሆነ ክስ የመመስረት እና የማጣራት ስራ ሊከናወን ይችላል ይላል፡፡
በአንቀጽ 7 (1) (d) ስር ማጋዝን ወይም ደግሞ ህዝብን ከፍላጎቱ ውጭ አስገድዶ ማስፈር እንደሁም ሌሎችም ኢሰብአዊ የሆኑ ድርጊቶች በአንቀጽ 7 (1) (k) ስር በግልጽ ተቀምጠዋል፡፡
የኢትዮጵያ ህገ መንግስት በአንቀጽ 28 “በሰው ልጆች ላይ ስለሚደርሱ የሰብአዊ መብት ረገጣዎች“ ስለሰብአዊ መብቶች ረገጣ በዓለም አቀፍ ስምምነቶች መሰረት ኢትዮጵያ ያጸደቀችው እና በሌሎችም ህጎች ላይ የተካተቱትን በግልጽ መመልከት ይቻላል… የዘር ማጽዳት ወንጀል በህግ አካሉ ሊታለፍ የሚችል ጉዳይ አይደለም…የኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ አንቀጽ 269 እንዲህ ይላል፣ “ማንም በጦርነትም ሆነ በሰላም ጊዜ ሆን ብሎ ሙሉ ለሙሉ ወይም ደግሞ በከፊል ለማጥፋት በብሄር፣ ብሄረሰብ፣ በጎሳ፣ በዘር፣ በዜግነት፣ በቀለም፣ በኃይማኖት ወይም የፖለቲካ ቡድን ሆን በሎ ካደራጀ፣ ትዕዛዝ ከሰጠ፣ ወይም ደግሞ (a) ግድያ ለመፈጸም፣ የአካል ጉዳት ለማድረስ ወይም ደግሞ በየትኛውም መልኩ አስከፊ የሆነ የአካልም ሆነ አዕምሯዊ ጉዳት ካደረሰ ወይም እንዲጠፋ ከተደረገ… ከ5 እስከ 25 ዓመታት ወይም ደግሞ ከዚህ ለበለጡ ጉዳዮች እስከ እድሜ ልክ እስራት ወይም እስከ ሞት ሊያስቀጡ ይችላሉ፡፡ (አጽንኦ ተሰጥቷል)፡፡“
ከቅርብ ጊዜ በፊት በአደናጋሪ ንግግሩ የሚታወቀው አሻንጉሊቱ ኃይለማርያም ደሳለኝ እንዲህ የሚል ንግግር አሰምቶ ነበር፣ “ያሉን ተቋማት፣ ህጎች እና ደንቦች እንከንየለሽ ናቸው፡፡ ህጉ አይደለም አስቸጋሪ ሆኖ የሚገኘው፣ ሆኖም ግን ዋናው ችግሩ ያለው ከአፈጻጸሙ ላይ ነው፡፡” ከኃይለማርያም ፍልስፍና በመዋስ በኢትዮጵያ የህገ መንግስቱ እና የህግ ሂደቶች ሁሉ ለምርመራ እና የዘር ማጽዳት እና ሌሎችን በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን ለመዳኘት የሚያስችሉ እንከንየለሽ ናቸው፡፡ ህጉ በእራሱ አይደለም ችግር የሚፈጥረው ሆኖም ግን ዋናው ችግር እነዚህን በባዶ ተጽፈው ያሉትን ህጎች ከመፈጸሙ ላይ ነው፡፡ ታዲያ ነገሩ ሁሉ እንደዚህ ከሆነ እነዚህን እንከንየለሽ ህጎች ማን እና ምንድን ነው በአግባቡ እንዳይፈጽሙ የሚያደርገው?!?
ካሩቱሪ በክስረት እሳት ላይ፣
እ.ኤ.አ ጥቀምት 2011 “ካሩቱሪ በእሳት አደጋ ላይ?” በሚል ርዕስ የጋምቤላ ህዝቦችን ቅሬታ በማንሳት ጩኸቴን ያሰማሁ መሆኔን እና በካሩቱሪ እና በድብቁ የዓለም ባንክ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር ገንዘብ ለልማት ተብሎ ቢፈስስም እየታዩ ያሉት በጣም ጥቂት የሆኑ የስራ ዕድሎች፣ ትምህርት ቤቶች፣ ክሊኒኮች ወይም ለመጠጥ አገልግሎት የሚውል ጥቂት የውኃ ፋሲሊቲዎች ብቻ ናቸው፡፡ በዕለቱ መጨረሻ የጋምቤላ ህዝቦች በረዥም የጊዜ አድማስ የደን ውድመት (ደኖችን በማቃጠል መሬትን ለእርሻ ማዘጋጀት)፣ የብዝሀ ህይወት መመናመን፣ የአካባቢ ዝርያዎች መጥፋት እና በአረም እና በተባይ ማጥፊያ መድኃኒቶች ርጭት እንዲሁም በሰፊ ታላላቅ የንግድ እርሻዎች ምክንያት የአካባቢ ብክለት መፈጠሩን በማስመልከት የክርክር ጭብጤን አቅርቤ ነበር፡፡
ባቀረብኩት ትችት ላይ ስለካሩቱሪ ውስን የሆኑ የመፍትሄ ሀሳቦችን ሰንዝሬ ነበር፡፡ በአሁኑ ጊዜ ከእርሻው ጋር በተያያዘ መልኩ ያለውን የመሬት ማግኛ ዘዴ እና የባለቤትነት መብት እርግፍ አድርጎ መተው እና በቀጥታ ከጋምቤላ ገበሬዎች ጋር በመስማማት እና በመግባባት የቀድሞውን አሰራር በዚህ መተካት፡፡ በጋምቤላ ላሉ ገበሬዎች ስልጠና መስጠት እና የበለጠ ውጤታማ እንዲሆኑ የእነርሱን እውቀት በአግባቡ መጠቀም፡፡ በዚህ ዓይነት መልኩ በመስራት ካሩቱሪ የምግብ እህል እና ሌሎችን የግብርና ምርት ውጤቶችን በማምረት ለኢትዮጵያ ገበያዎች በማቅረብ ትርፋማ መሆን ይችላል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በረዥም ዕቅድ የአካባቢውን ስነምህዳር እና የግብርና ምራታማነቱን በመጠበቅ ዘላቂነት ያለው ልማትን ለማምጣት ያስችላል፡፡ ካሩቱሪ የጋምቤላን ፕሮጀክት ኃላፊነት የተንጸባረቀበት፣ ጥንቃቄ የተሞላበት እና ትርፋማ ኢንቨስትመንት ዋና የአፍሪካ ሞዴል አድርጎ ማሳየት እና በሌሎች የአፍሪካ ሀገሮችም በተመሳሳይ መልኩ እየሰራ የሚጠቀምበት ማድረግ ይችል ነበር፡፡
ትችቴን ለማጠቃለል ያህል በደቡብ አሜሪካ ግዛቶች እየተጋዙ አስከፊ በሆነ ሁኔታ በጥጥ እና በትምባሆ ሰብሎች ላይ የእርሻ ስራ ላይ የጉልበት ስራ እንዲሰሩ ይገደዱ በነበሩት የአፍሪካ ባሮች የተቋጠሩትን እንዲህ የሚሉትን ጥቂት የሙዚቃ ስንኞች አስታወሰኝ፡፡
አምላክ ለኖህ ብሎ በሰጠው ምልክት፣
በተንቆጠቆጠው በሰባት ቀለማት፣
በቀስተ ደመና ታምር ባጠላበት፣
እራሱን ለማዳን ከማዕበሉ መቅሰፍት፣
ትዕዛዙን ፈጸመ ህይወት ለማቆየት፣
በዚህች ምስኪን ምድር ዘርን ለመተካት፡፡
ኖህ ለአምላክ ሲገዛ ትዛዙን ሲፈጽም፣
ያ ሁሉ መከራ ከጎኑ ሲል እልም፣
የውኃው ማዕበል ብን ብሎ ሲያከትም፣
በቀጣይነትም እሳት አልነበረም፡፡
ኖህ በሰላም ኖረ ዘርንም ተክቶ፣
በሁሉም አህጉር አህዛብን ዘርቶ፣
እኩይ ምግባራትን እብሪትን አጥፍቶ፡፡
እ.ኤ.አ በ2015 የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ያቀረበው መረጃ ታማኝነት ያለው ከሆነ ካሩቱሪ የ170 ሚሊዮን ብር እዳን ከማሳየት በስተቀር ሊያሳይ የሚችለው ምንም ዓይነት ነገር በእጁ ላይ የለውም፡፡
ቃል ተገብቶለት የነበረው በአስር ሺዎች ሄክታር የሚቆጠረው የፓልም ዘይት፣ የሸንኮራ አገዳ፣ የሩዝ፣ የምግብ ዘይት፣ የበቆሎ እና የጥጥ ሰብል ምርት የት አለ? እንደዚሁም 60,000 ሰራተኞች የት አሉ? እነዚህ ሰራተኞች ሌላ በየትም ሳይሆን በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ መሪዎች የቅዠት ምናብ ውስጥ ይገኛሉ፡፡
አምላክ እ.ኤ.አ በ2011 ለካሩቱሪ በባሮ (ኡፔኖ) ወንዝ ላይ የቀስተደመና ምልክት ሰጥቶት ነበር፡፡ ካሩቱሪ ግን በተሰጠው ምልክት እራሱን ለማዳን አልተጠቀመበትም፡፡ በአሁኑ ጊዜ ካሩቱሪ በኪሳራ እሳት ላይ እየተለበለበ ይገኛል፡፡
ሌሎችም እንደዚሁ የመንደር ምስረታ እና በህዝቡ ላይ እልቂትን የሚያዘንቡ የሰብአዊ መብ ደፍጣጭ አምባገነኖች ምንም ነገር ሳይሳካላቸው ጉምን ዘግነው እንደሚቀሩ ልተነብይላቸው እወዳለሁ፡፡
ቻው፣ ቻው፣ ካሩቱሪያውያን/ት! ሄሎ! ከኢትዮጵያ ከጋምቤላ እንኳን በደህና ወደ ሀገራችሁ ተመለሳችሁ! እንኳን በጤና ወጣችሁ! ጤና ካለ ገንዘብ ይገኛልና! መጀመሪያ ለጤናችሁ!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
የካቲት 17 ቀን 2007 ዓ.ም

አንድነት ሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ማህበርና ከሰማያዊ ሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ማህበር የተሰጠ የጋራ መግለጫ

እንደሚታወቀው የኢህአዴግ አገዛዝ ከጊዜ ወደ ጊዜ ጸረ ዲሞክራሲ አካሄዱ እየባሰበት የመጣና መሠረታዊ መብቶችን ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል መልኩ ማፈኑን አጠናክሮ ቀጥሎበታል፡፡ በቅርቡ በአንድነትና በመኢአድ ፓርቲ ላይ አገዛዙ በሚያዝዛቸው የተቋማት ኃላፊዎች ቀጭን ትዕዛዝ የፓርቲዎቹ ሕልውና ለጥቂት ግለሰቦች ተላልፎ ተሰጥቷል፡፡ ይህ ዓይነቱ ህገ-ወጥ ድርጊት መቼዉም ቢሆን ተቀባይነት አይኖረውም! ለአገራችን የሠላማዊ የስልጣን ሽግግር ከባድ መሠናክል ሊሆን እንደሚችል ሁሉም ይገነዘባል ብለን እናምናለን፡፡ የኢህአዴግ የምርጫ ቦርድ እንዲህ ዓይነቱን ክፉ ስራ ሲወስን የአገራችንን የረጅም ሠላም አይተው ሣይሆን በአገዛዙ ቁንጮ ሰዎች በመታዘዝ በተቋም ስም የሚሠሩት የማደናገር የድንቁርና ተግባራቸዉ አንድ አካል ነው ብለን እናምናለን፡፡ ማህበራችን ይህን ድርጊት እጅጉን ያወግዛል። በመሆኑም ድርጊቱን በጋራ እንቃወማለን።
በምርጫ ቦርድ ስም የተወሰነው ህገ-ወጥ ውሣኔ ምክንያት መላ የአንድነትና የመኢአድ አባላት የፖለቲካ እንቅስቃሴአቸው ተገድቧል፡፡ ይሁን እንጂ ለአገራቸው ካላቸው ፅኑ ፍቅር አኳያ ትግሉን ለማስቀጠል ከሠማያዊ ፓርቲ ጋር አብሮ ለመሥራት የአባልነት ፎርም በመሙላት ትግሉን ቀጥለዋል፡፡ ይህ ዓይነቱ የአባላት ቆራጥ ውሣኔ ሊበረታታና ሞራል ሊሰጠው የሚገባ ነው ብለን እናምናለን! እኛም በሰሜን አሜሪካ የምንገኝ የሁለቱ የድጋፍ ማህበራት ሙሉ በሙሉ ድጋፋችንን እንደምንሰጥ እናረጋግጣለን፡፡
ስለሆነም በሰሜን አሜሪካ የምንገኝ የአንድነትና የሠማያዊ የድጋፍ ማህበራት በጋራ በኮሜቴ ደረጃ ተዋቅረን በዋና ዋና ጉዳዬች ላይ ማለትም በፋይናንስ፤ በእስረኞች ጉዳይ እና በዲኘሎማሲው ዙሪያ ሙሉ በሙሉ በትብብር አብረን እየሠራን የሰማያዊ ፓርቲንና ሌሎች በሃገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ሃይሎችን በጋራ ድጋፍ ለመስጠት ውሣኔ አሣልፈናል፡፡ በቀጣይም በጋራ የኮሚቴ ውይይቶችን እያደረግን ለሰማያዊ ፓርቲ የሚያስፈልጉ የሞራልና የማቴሪያል ርዳታ እንደምንሰጥ እናረጋግጣለን፡፡
የሰማያዊና የአንድነት ሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ማህበራት
የካቲት 19 2007 ዓ/ም

Mittwoch, 25. Februar 2015

በአሰሪዎቾ የታገተችው ኢትዮጵያዊት የሰቆቃ ደምጽ !

ገነት አበበ ሞላ ትባላለች የልጅነት ግዜዎን ሩጣ ያልጠገበች በ አስራዎቹ የዕድሜ ክልል ውስጥ የምትገኝ ኮረዳ ነች። ከዛሬ 3 አመት በፊት ነበር በኑሮ ውድነት የተጎሳቆሉ ቤትሰቦቾን ከደህንነት ለመታደግ በወቅቱ እስከ ገጠር በዘለቀው የአሰሪና ሰራተኛ የደላሎች ዘመቻ ከአርሲ ኮሌ ወረዳ ኩዬ ከተማ ተመልምላ የማይጨበጠውን የአረቡን ዓለም መከራ ለመጋፈጥ፡ተስፋ ሰንቃ ወደ ሳውዲ አረቢያ ያቀናቸው ። በወቅቱ በስው ልጆች ህይወት ዶላር ለማግበስበስ በየአካባቢው በተከፈቱ የአሰሪና ሰራተኛ ኤጀንሲ ደላሎች ከእናቶቻቸው ጉያ ተነጥቀው ለአቅመ ሄዋን ያለደረሰውን እድሜዎቻቸውን ቆልለው ፓስፖርት የወሰዱ ህጻናት ሳይቀሩ በቀን ከስክ 1500 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን የኮንተራት ሰራተኞች የለህይወት ዋስትና ወደ ሳውዲ አረቢያ በጅምላ ይላኩ የነበረበት ወቅት በመሆኑ ወጣት ገነትም ሰው እንደሆነው እሆናለሁ ብላ በፌስታል የተሞሉ ልብሶቾን እንደነገሩ ይዛ ነበር የምተወዳቸውን ወላጆቾኝ በዕንባ የተሰናበተቸው ። አንድም ቀን ከቤት ወጥታ የማታውቀው ገነት አስረክበው ወደ ቀዬያቸው የተመለሱ ወላጆቾ የገነትን ድምጽ ቢናፍቁም ባህር አቋርጣ ሳውዲ ሄደች ከተባለ ወዲህ ወራት ተቆጥረው ዓመት ቢደፍንም ገነትን የበላ ጀብ አልጮህ አለ ።
ወትሮስ ለማን አቤት ሊባል ? « የገነትን ስቃይ ማን ይወቅላት » ክፉ አጋጣሚ ሆኖ በአሰሪዎቾ « ኃይል» ወደ ሚባል ገጠራማ የሳውዲ ግዛት ለስራ የተወሰደችው ገነት ወግ ባህሉ ቋንቋው ባዕድ በሆነባት ሃገር ሁሉም ነገር እንዳሰበቸው እና እንደተነገራት አልነበረም። ታዲያ ገነት ከቤትሰቦቾ ጋር ስትለያይ ሲያነቡ የነበሩት አይኗቾ እንባ እንደቋጠሩ ነበር ፍጹም ከባድ የሆነውን የአረቡን ዓለም የቤት ስራ የተጋፈጠቸው ፡፤ በማለዳው ምናምን ቢጤ ቀማምሳ ለአመታት ተጠርጎ የሚያውቀውን አቧራ የለበስና ቆሻሻ የተከመረበትን ግቢ ከአሰሪዎቾ በምለክት በተሰጣት ተዕዛዝ ስታፀዳና ከ 4 ያላነሱ መኪኖችን ስታጥብ የዋለቸው ። በዚህ መልኩ ለወራት የተዋሃዳትን የአሰሪዎን የቤት ውስጥ ስራ ጨምሮ የማይመለክታትን ከባድ ስራዎች ሁሉ ካጠናቀቀች በኃላ ለሌላ አረብ ተላልፋ እይተሰጠች የቤት ሰራተኛ ለሌላቸው የሰፈሩ አረቦች ሁሉ አገልጋይ ሆናለች ። ገነት እረፍት የላትም እንደ ዘበኛ መኪና በመጣ ቁጠር የግቢ በር ትከፍታለች የአሰሪዎቾን መኪናና ግቢ ታጥባለች ከባድና ቀላል የሆኑ እቃዎችን እስከ 3ኛ ፎቅ ተሸክማ በመውጣት ከአቅሞ በላይ የሆነና የማይመለከታትን ስራ በግዳጅ እንድትሰራ ትደረጋለች። ከቤተሰቦቾ ከተለየች ወዲህ በስልክ ወላጆቾን አጊታቸው የማታውቀው ገነት ከሥራው ክብደት ይልቅ በናፍቆት ከሰውነት ጎዳና የወጣው ስውነቷና የልጅነት ወዝዎ በቁም የተገነዘች ሬሳ አስመስሏታል ፡፡
በአስሪዎቾ ታግት በደል የሚፈጸምባት ገነት ከሚፈፀምባት ግፍ እና በደል እግር ወደ መራት በመሄድ እርሷን ከባርነት ለመታደግ የሞከርቸበትም አጋጣሚ እደነበር ይነገራል። ከዚያ ወዲህ ገነትን ለማግባባት ብዙ ሞክረው እንዳልተሳካላቸው የተረዱት አሰሪዎቾ ገነት ላይ የሚያደርጉትን ክትትል በማጠናከር የስራ ግዳጆዎን ስትጨርስ ባዶ ቤት ይቆለፉባታል። የቤት ሰራተኛ እጥርት የገጠማት ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በአሰሪዎቾ የታገተቸው ኢትዮጵያዊቷ ወጣት ገነት አበበ ለአሰሪዎቾ እያበረከተች ካለው ነጻ አገልግሎት ባሻገር በወር እስከ 3800 በሚደርስ ክፍያ ለሦስተኛ ወገን ተላልፋ በመሰጠት ጥሩ የገቢ ምንጭ እስከ መሆን መድረሷ ይነገራል። ከአንዱ የአረብ መኖሪያ ወደ ሌላው የአረብ መኖሪያ ቤት እይተቀባበሉ ያለ በቂ እረፍት የአረብ አገልጋይ ለመሆን የተገደደቸውን ኢትዮጵያዊት የኮንተራት ሰራተኛ ከማለት ይልቅ በኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት ህጋዊ ፈቃድ አጊቶ በሚንቀሳቀስ አሰሪና ሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ የተሸጥች ባሪያ ማለት ይቀላል።
አዲስ አበባ ውስጥ በተለምዶ ሚክሲኮ አደባባይ አካባቢ ሴብሪን « sebirn » እይተባለ በሚጠራ አንድ ኤጀንሲ አማካኝነት ተዋውላ ህጋዊ በሆነ መንገድ ለስራ ሳውዲ እንደገባች የሚነገርላት ገነት ዛሬም የይደርሱልኝ ይሰቅቃ ድምጾን ታሰማለች ፡፤
አሁን አሁን ለህይወቷ የምትሳሳው ገነት ይገሉኛል በሚል ስጋት በድብደባ ከተጓሳቆለው አካሏዎ ባሻገር ሌሎች ምስጢራዊ በደሎችን ለግዜው ከመግለጽ መቆጠቧን ለልጅቷ ቅረበት ያላቸው ወገኖች ይገልጻሉ። እነዚህ ወገኖች አቤቱታቸውን በጅዳ ለኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ቢገልጹም እስክ አሁን የገነት የሰቆቃ ድምጽ ምላሽ አላገኘም፤
Ethiopian Hagere Jed Bewadi

Dienstag, 24. Februar 2015

አዋራጅ ሰልፎችና ድግሶች እንዲያበቁ ህወሓት ይወገድ!

pg7-logoድግሶችን፣ ወታደራዊ ሰልፎችንና ሀውልቶችን ማብዛት የአባገነኖች ሁሉ የጋራ ባህርይ ነው። ዘረኛውና ፋሽስቱ የህወሓት አገዛዝም በሕዝብ እየተጠላ፣ እያረጀና እየወላለቀ በሄደ መጠን በየተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ደግሶ መብላት፤ ወታደራዊ ሰልፍና የመሣሪያ ጋጋታ ማሳየት እና በየመንደሩ ሀውልት መመረቅ ሙያው አድርጎት ቆይቷል።
የህወሓት ድግሶችና ፌሽታዎች የአገራችን ሀብት ከማሟጠጣቸውም በላይ የመንግሥት ሠራተኞችን፣ የአርሶ አደሮችንና የአነስተኛ ነጋዴዎችን ኪስ እያራቆቱ ናቸው። በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የኦሮሞ ተወላጆች በእስር ቤቶች እየማቀቁ በሚገኙበት ሁኔታ፤ በመቶ ሺዎች የሚገመቱ የአማራ አርሶአደሮች ተፈናቅለው እያለ፤ በጋምቤላና በኦጋዴን ወገኖቻችን ላይ ዘግናኝ የጅምላ ጭፍጨፋዎች እየተደረጉ፤ በአፋር፣ በሲዳማ፣ በቦረና፣ በወልቃይት እና በመላው ኢትዮጵያ ግጭቶች በበዙበት፤ ሕዝብ እያለቀሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት “የብሔር፣ ብሔረሰቦች መብት ተከበረ” እያሉ እነዚህኑ በደል እየደረሰባቸው ያሉ ዜጎችን ማስጨፈር እና ለእነዚህ ጭፈራዎች በርካታ ሚሊዮኖች ብር ማውጣት በእጅጉ ያስቆጫል። እነዚህ ጭፈራዎች ለህወሓት ሰዎች የገቢ ምንጮች መሆናቸው ጥርጥር የለውም፤ ለድሀው ኢትዮጵያዊ ግን መራቆቻዎች ናቸው። ከዚህም አልፎ በዘረኝነት እየተበደለ ያለ ሕዝብ ስለእኩልነት ዝፈን ማለት ክብረ ነክ ተግባር ነው። ዘንድሮ በአሶሳ የተደረገው አገር አቀፍ ድግስ ካለቀ ጥቂት ወራት በኋላ አገራችን በሌላ ዙር የህወሓቶች ድግስ ተወጥራለች።
ሰሞኑን በባህር ዳር በተደረገው የጦር ሠራዊት ሰልፍ እና ሰልፉን ተከትሎ በነበረው የድግሶች ግርግር ከሁሉም በላይ የተሰደበውና የተዋረደው የሠራዊቱ አባል ነው። አዛዦቹ መቶ በመቶ የህወሓት አባላት የሆኑበትን ሠራዊት “የኢትዮጵያ መከላከያ” ተብሎ መጠራቱ ራሱ የሚያሳፍረው ኢትዮጵያዊ ወኔ በልባቸው ውስጥ እየተንቀለቀለና እልህ እየተናነቃቸው ያሉ የሠራዊቱን አባላት ነው። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እንዴት የኢትዮጵያ ጠላቶች በሆኑ የህወሓት ካድሬዎች ይመራል? እንዴት የአስር አለቃ እንኳን ሊሆን የማይገባው የህወሓት ካድሬ “ጄኔራል” ተብሎ ኢትዮጵያዊያን ወታደሮችን እንደ ሎሌው ያዛል? እንዴት አንድ የህወሓት ሎሌ ሹመት ተሰጥቶት እየፏለለ በልምድ፣ በትምህርትና በእውቀት የሚበልጠውን ኢትዮጵያዊ ተንቆ ይዋረዳል? ይህ ቁጭትና እልህ ሠራዊቱ የዘረኛውን ህወሓት ሰልፍ አድማቂ መሆኑ የሚያከትምበት ጊዜ ይበልጥ እንዲናፍቅ የሚደረገው ነው። አልያማ ሰልፍ ያሳመረ ሠራዊት ሁሉ አሸናፊ እንዳልሆነ የታወቀ ነው። በሰልፍ ብዛትና በመሣሪያ ትዕይንት ማሸነፍ ቢቻል ኖሮ የትም አገር አምባገነኖች ባልወደቁም፤ ህወሓት ራሱን ስልጣን ላይ ባልወጣም ነበር።
የህወሓት ምሥረታ 40ኛ ዓመት ድግስም ሌላው የታሪክና የሀብት ውድመት የሚያስከትል ክስተት ነው። የካቲት 11 ቀን 1967፣ ጥቂት ኢትዮጵያዊያን እናታቸውን ኢትዮጵያን ለመግደል ያሴሩበት እና ልጆች በእናታቸው ላይ ቢላዋ የሳሉበት ዕለት በመሆኑ በሀዘንና በሱባኤ እንጂ በድግስና በጭፈራ የሚታሰብ ዕለት አይደለም። ሲነሳ ምንም ይሁን ምን ዛሬ በደረስንበት ሁኔታ ሲገመገም፣ ኢትዮጵያ በታሪኳ ውስጥ ህወሓትን የመሰለ መሠሪና አድርባይ ድርጅት ገጥሟት አያውቅም። እነሆ ዘንድሮም ይኸው አድርባይ ድርጅት የመሪዎቹን የሀብትና ዝና ረሀብ ለማስታገስ ሲል ያልነበረ ታሪክ እየፈጠረ በድግስ ስም ከድሀው ገንዘብ እየሰበሰበ ለሀብታም የህወሓት አባላትና ደጋፊዎች ያሸጋግራል። የድግሶቹ ሁሉ አዘጋጆች፣ እቃ አቅራቢዎችና ተጠቃሚዎች ራሳቸው የህወሓት መሪዎችና አሽቃባጮቻቸው ሲሆኑ ከፋዩ ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው። በህወሓት ድግስ የሚባክነው የሕዝብ ሀብት ስንት ሆስፒታል ይገነባ እንደነበር ስናስብ እና ይህ ሀብት በተገቢው ቦታ ውሎ ቢሆን ኖሮ ዛሬ ስም ብቻ የያዙ ዩንቨርስቲዎቻችንን ትምህርት መቅሰሚያ ማድረግ እንችል እንደነበር ስናሰላ ሀዘናችን ጥልቅ ነው። ህወሓት ለልጅ ልጆቻችን የሚተርፍ ዕዳ እየቆለለ ዳንኪራ ሲረግጥና ሲያስረግጥ ማየትና መስማት ህሊና ሊሸከመው ከሚችል በላይ ነው።
አርበኞች ግንቦት 7፡ የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በህወሓት ወታደራዊ ሰልፍ እና የመሣሪያዎች ትዕይንት የሚረበሽ ድርጅት አይደለም። ይልቁንም በሰልፉ ጨኸት የታፈነው የኢትዮጵያዊ ወታደር ጩኸት ይሰማዋል። ኢትዮጵያዊ ወታደር በአዛዦቹ ላይ ጥርሱን ነክሶ፣ ቂም አርግዞ ሰልፋቸውን እንደሚሰለፍ አርበኞች ግንቦት 7 ያውቃል። አርበኞች ግንቦት 7፣ የሠራዊቱ አባላት ውስጥ ውስጡን እየተሰቃዩ የታዘዙትን መፈፀማቸው መብቃት አለበት ይላል፤ ወይ ተቀላቀሉን፣ አሊያም እውስጡ ሆናችሁ ሥርዓቱን የማዳከም ሥራዎችን ሥሩ። በእናንተ ውርደት የዘራፊዎች፣ ሙሰኖች፣ ጎጠኞችና ዘረኞች ደረት አብጦ መታየት የለበትም።
አርበኞች ግንቦት 7፣ የዘንድሮው የህወሓት 40ኛ ዓመት በዓል የጨረሻው በዓል እንዲሆን፤ ከርሞም ተመሳሳይ አዋራጅ በዓል እንዳናከብር፤ ሠራዊቱ በዘራፊዎች ታዞ የሚሰለፍበት ውርደት እንዲያበቃ ተባብረን ህወሓትን እንቅበር ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

የዚህ ሁሉ እልቂት “ኩሹፍ” ሲገለጥ( አርአያ ተስፋማሪያም)

ጠ/ሚ/ር ሃ/ማርያም፣ ባለቤታቸውና ሌሎች አንገታቸው ላይ ስላጠለቁት በተመለከተ አንድ የቀድሞ አንጋፋ የድርጅቱ ታጋይ በግል ያደረሱኝ መልእክት እንዲህ ሲል ይጀምራል « በታጋዮች ዘንድ “ኩሹፍ” ተብሎ ይጠራል። ታጋዩ ከሞተ በኋላ የሚገነዝበት ጨርቅ ነው። ድርጅቱ አላማ ያለው የመሰለው አብዛኛው ታጋይ ያን ጨርቅ አንገቱ ላይ በማጥለቅ ለመሰዋት (ለመሞት) ቁርጠኝነቱን የሚያሳይበት ነበር። 98 በመቶ የሚሆነው ተዋጊ ያልተማረ ስለነበረ የድርጅቱ አላማና አካሄድ ሊያውቅበት የሚችል አንድም መንገድ አልነበረም። በእሱ ደምና አጥንት ተረማምደው ሲያበቁ የራሳቸውን ድብቅ አጀንዳ አስፈፀሙ። 36 ሺህ የህወሀት ታጋዮችን ገና በጠዋቱ አባረው ለአስከፊ የጐዳና ህይወት ዳረጓቸው። ኢትዮጵያውያን ወንድማማቾችን በብሄር ፖለቲካ እርስ በርስ እንዲናቆሩ እነመለስ የጥፋት ወጥመድ ዘረጉ። “ፓርቲው ወዴት እየሄደ ነው?..ግምገማ መካሄድ አለበት፤ ሙስና ተቀጣጥሏል..” የሚሉ ጥያቄዎችን ያነሱና ከጋንታ እስከ ሬጅመንት አዛዥነት (ኋላ መኮንኖች) ቦታ የነበራቸው 5 ሺህ ታጋዮች ሆለታና ታጠቅ እስር ቤቶች ታጐሩ። አቶ መለስ 36 ሺህ ታጋይ በ84 ዓ.ም ሲያባርሩ «ጓሃፍ ፅረጉለይ..» ማለትም “እነዚህን ቁሻሻ ጥራጊዎች አስወግዱልኝ” ነበር ያሉት። ትእዛዙን ደግሞ ስዬ አብርሃ ተፈፃሚ አደረጉ። ለ5 ሺህ መኮንኖች ደግሞ ያቀረቡት ሰበብ «መፈንቅለ ፓርቲ ለማድረግና እኔን ለመገልበጥ ሲያሴሩ..» የሚል የፈጠራ ክስ በመለስ ዜናዊ ቀረበባቸው። በሆለታ እስር ቤት በ1988 ዓ.ም እንዶድ የተባለ መርዝ ጨቅጭቀው የጠጡ 1 ሺህ 5 መቶ (1,500) መኮንኖች ህይወታቸው ሲያልፍ የሁሉም ሬሳ በአንድ ጉድጓድ በሌሊት እንዲከተት ተደረገ። በታጠቅ ከ1 ሺህ የሚበልጡ በተላላፊ ሳንባ እንዲያልቁ ተፈረደባቸው። የዚህ ሁሉ እልቂት ምስጢሩ ታጋዮቹ “የሃየሎም ግሩፕ” በሚል በነመለስ ስለተፈረጁ ነበር። እነሱን ከጨረሱ በኋላ እሱንም አስገደሉት። ሃቁ ይህ ሲሆን ዛሬ እነሃ/ማርያምና ሌሎቹ ባልዋሉበትና ባልነበሩበት ትግል ያን “ሽኩፍ” አጥልቀው መታየታቸው ያሳፍራል። ለነገሩ በታጋዩ መስዋእትነት የተረማመዱት የዛሬው ሚሊየነሮች አጥልቀው ታይተው የለ!! ታሪክና ጊዜ ይፈርደናል!» ይላል። …በነገራችን ላይ የሆለታና ታጠቅ እስር ቤት የጅምላ እልቂትና ስቃይ በተመለከተ በ1994 ዓ.ም ጥቅምት ወር አንስቶ የአንዳንድ ሟች ታጋዮች ፎቶ በማስደገፍ እንዲሁም በእስር ቤት የፃፏቸውን መልእክቶች በማያያዝ በኢትኦጵ ጋዜጣ በተከታታይ መረጃው ይፋ ተደርጓል።

ኢትዮጵያ ውስጥ ዳኛ ቢኖር – ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም

የጎረቤት ኬንያ ዳኛ ለኬንያ መንግሥት አስፈጻሚው ክፍል ልኩን ነገረው፤ ሕገ መንግሥቱን በመርፌ አስተኝተህ ሕገ መንግሥቱን የሚጻረር ሕግ ለማውጣት አትችልም፤ ስለዚህም የሰነዘርኸውን የጉልበት ሕግ አንሣ፤ አለው፤ ዳኛ አይጥፋ! ሌላ ቢቀር ከጎረቤት ዳኝነትን እንስማ፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ዳኛ ቢኖር ስንት ጋዜጠኛ፣ ስንት የሃይማኖትና ስንት የፖሊቲካ መሪዎች ከየወህኒ ቤቱ ይወጡ ነበር! ሁላችንም እንደልባችን ሳንፈራ፣ ሳንፈራራ በሙሉ ነጻነት ችግሮቻችንን የወያኔን ጭቆና ጨምሮ ለመወያየትና መፍትሔዎችን ለመለዋወጥ የምንችልበት መድረክ፣ ጋዜጣ፣ መጽሔት፣ ራድዮና ቴሌቪዥን በኢትዮጵያ ውስጥ ይኖረን ነበር፤ ስንት ሰው ሥራ ያገኝ ነበር፡፡
ከሁሉም በላይ በየመንገዱ ጠመንጃ የያዘ ሊያስፈራራን የሚሞክር ሆድአደር እያየን፣ እንደዚሁም በየጫካው ያሉትን እያሰብን ሰላማችንን ከምናጣ አበባውን ትተን፣ ሩዙን ትተን፣ የተወደደልንን ጤፋችንን እያመረትን አዲስ ኑሮ ብንጀምር የተሻለ ነበር፡፡
ግን አንድ እንቅፋት አለብን፤ እነዚህ ከየኪዮስኩ እውቀት ገዝተን አዋቂዎች ሆነናል የሚሉት እንትኖች እንመጀመሪያ ችግሩ እንዲገባቸው፣ ሁለተኛ መፍትሔው እንዲገባቸው፣ ሦስተኛ ጉልበትና እውቀት አንድ አለመሆናቸውን ብቻ ሳይሆን በጉልበት እውቀት የማይገኝ መሆኑን ማሳመን በረዶ እየወረደ የስሜን ተራራን መውጣት ነው፤ በረዶ ሳይኖር ወጥቼዋለሁ!
እነዚህን የጉልበት አዋቂዎች — ስለሽማጌሌዎችና አሮጊቶች ሳያስቡ፣ ስለመብራት ኃይል ሳያስቡ፣ ስለውሀ ሳያስቡ ሁሉም በጉልበት ፎቅ ይውጣ የሚሉ! ይባስ ብለው ለእስረኛውም ፎቅ እየሠሩለት ውጣ! ሊሉት ነው!
እነዚህ የጉልበት አዋቂዎች የአበሻ ኑሮ፣ ቡናው፣ ሙቀጫው፣ ምጣዱ፣ በርበሬው፣ ቁሌቱ፣ ቄጤማው፣ ዶሮና በግ ማረዱ፣ ኧረ ስንቱ! ሳይገባቸው ቻይና በነገራቸው የሚያውቁትን የሚረሱ ማን ያስተምራቸው! እናውቃለን ስለሚሉ እንዴትስ ይማራለ? በእውነት ለመማር ቢፈልጉስ ስንት ዓመት ሊያስፈልጋቸው ነው! እግዚአብሔር እንሱንም እኛንም በምሕረቱ ይጎብኘን! የሚያስተምር ጎረቤት አያሳጣን!

Sonntag, 22. Februar 2015

«አፋን ኦሮሞ ስለማትናገሩ በኦሮሚያ መወዳደር አትችሉም» – ምርጫ ቦርድ

Tesfayeአቶ ምርቱ ጉታ ዋቅጅራ የአንድነት ፓርቲ የምስራቅ ቀጠና አደራጅ ነበሩ። የአዳማ ናዝሬት አንድነት ሊቀመንበርም ሆነው ሰርቷል። አቶ ተስፋዬ ዋቅቶላ የአዳማ አንድነት የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ ነበሩ።
ገዢው ፓርቲ ሕወሃት ፣ የአንድነትን ፓርቲ ሕጋዊነት ላደራጀው የተለጣፊው የትግስቱ ቡድን ሲሰጥ ፣ አቶ ምርቱ፣ አቶ ተስፋዬና በርካታ የአንድነት አባላት ሰማያዊ ማሊያ ለብሰው ትግሉን ቀጠሉ፡፡ በሰማያዊ ፓርቲ ሥር ለመወዳደር፣ አቶ ምርቱና እና አቶ ተስፋዬ ዋቅቶላ በአዳማ አንድ ምርጫ ጣቢያ ለመመዝገብ ይሄዳሉ። ከብሔራዊ ቋንቋው ውጪ የክልሉን ቋንቋ ካልተናገራችሁ መመዝገብና ለምርጫ መወዳደር አትችሉም በመባላቸው ፣ በአገራቸው ለምርጫ የመመዝገብ መብታቸው ተነፈገ።
አዳማ ናዝሬት ኢትዮጵያዉያን ዘር፣ ቋንቋ፣ ኃይማናቶ ሳይለያያቸው በሰለም ፣ ተሰምማተው የሚኖሩባት ከተማ ናት። አዳማ/ናዝሬት የፍቅር ከተማ ናት። በዚያ የተወለዱ ወገኖች ራሳቸውን የሚያስተዋዉቁት ትግሬ፣ ጉራጌ፣ ኦሮሞ ብለው አይደለም። ናዝሬቶች ነን ብለው ነው። በዚያ ያለው ህዝብ አፋን ኦሮሞ ይናገራል፤ አማርኛ ይናገራል። ቋንቋ ከመግባቢያ መሳሪያነቱ ዉጭ አዳማዎች አይተቀሙበትም። ሆኖ ህወሃት ቋንቋን በመጠቀም አንዱ ተጠቃሚ ሌላው ተጎጂ እንዲሆን በማድረግ፣ ለአንዱ ሰጥቶ ለአንድኑ በመንፈቅ፣ መቃቃርና ልዩነቶች እንዲመጡ ለማድረግ ፣ በናዝሬት/አዳማ የዘር ግጭት እንዲፈጠር ለመቀስቀስ ደፋ ቀና እያለ ነው።
ሕወሃት መርዛማ ፖለቲካውን ይኸው ላለፉት 24 አመታት ሲረጭ ነው የቆየው። የኦሮሚያ ክልል ሕግ መንግስትም ፣ በፌዴራል ሕገ መንግስቱ የተቀመጠዉን የዜጎች የመምረጥና የመመረጥ መብት በመናድ፣ ኦሮሚያ የኦሮሞዎች ብቻ እንደሆነች፣ የኦሮሚያ የክልሉ ቋንቋ አፋን ኦሮሞ ብቻ እንደሆነና በኦሮሚያ ለመመረጥ አፋን ማወቅ እንደሚያስፈልግ ይደነግጋል። በኦሮሚያ የሚኖሩ ከ20 በመቶ በላይ የሚሆኑ ሌሎች ብሄረሰቦች ፣ ኦሮሞ ነን የሚሉ ግን አፋን ኦሮሞ በደንብ የማያወቁ ኦሮሞዎች፣ የመመረጥ መብታቸውን ሙሉ ለሙሉ በወረቀት ላይ ያለው የኦሮሚያ ሕግ መንግስት ይጨፈልቀዋል።
በዚህም መሰረት አፋና ኦሮሞ መናገር በደንብ አትችሉም በመባላቸው፣ እነ ምርቱ ጉቱን ተስፋዬ ዋቅቶሎ የመመረጥ መብታቸዉን አጥተዋል።
ይሄ ዘር እየሉ ዜጎችን የመከፋፈል ተግባራት፣ በጥናትና ከማእከል በመመሪያ የሚደረግ እንደሆነ ብዙ መረጃዎች ያስረዳሉ። ለምሳሌ በቅርቡ የኢሕአዴግ አመራር አባላት ባደረጉት ግምገማ፣ የደቡብ ክልል አስተዳዳሪ የነበሩት አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ፣ የአማርኛ ተናጋሪዎች (አማሮች የሚሏቸውን) ከክልሎ በግፍ እንዲወጡና እንዲባረሩ ባደረጉበት ጊዜ፣ መመሪያ ከአቶ መለስ ዜናዊ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል።
በግምገማው ወቅት «አማራን ባስወጣህበት የደቡብ ክልል መስተዳደር ጊዜህ ለክልሉ ነዋሪዎች ነፍጠኛ ከኛ ይወገዳል ብለህ ተናግረሃል” በሚል ከብአዴን ተወላጆች አስተያየት ሲሰጥ» አቶ ሽፈራው ” ከጠ/ሚኒስትሩ የተሰጠኝን ተልእኮ ነው በአግባቡ የተወጣሁት፣ ሌላ አልጨመርኩም አላስወጣሁም” በማለት ነበር የመለሱት።
ገዢው ፓርቲ በ እቅድ የዘር ከፋፋይ ፖለቲካውን ብዙ ገንዝበ መድቦ ለማሳፋፋት ቢሞክርም፣ የአዳማ/ናዝሬት ህዝብ ለመርዛማው የዘር ፖለቲካ እጅ አልሰጠም። በአስተሳሰቡ መጥቆ ሄዷል። አሁንም ፍቅሩን እና አንድነቱን ጠብቆ፣ እስላም ክርስቲያን ፣ አማራ ፣ ኦሮሞ ሳይባባል፣ ተስማምቶ በሰላም እየኖረ ነው። የአገዛዙ የከፋፍለህ ግዛ የጥላቻ ፖለቲካ እየተሸነፈ ነው። ፍቅርና ኢትዮጵያዊነት እያሸነፈ ነው።