Netsanet: ዘመቻው በከፊል ተሳክቷል፤ ከተመስገን ጋር ተገናኝተናል

Mittwoch, 18. Februar 2015

ዘመቻው በከፊል ተሳክቷል፤ ከተመስገን ጋር ተገናኝተናል

10996233_545270902279488_5264758968545862187_nዘመቻው በከፊል ተሳክቷል፤ ከተመስገን ጋር ተገናኝተናል
በቅድሚያ ያለፈውን ሳምንት አብራችሁን ለነበራችሁ የበይነ-መረብ ዘማቾችና ወዳጆች ምስጋና ይድረስ፡፡
በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ የምግብ የህክምናና የጎብኚ እግድ የተጣለው ከአንድ ወር በፊት ነበር፡፡ በዚህ የተቆጡ ቤተሰብና ወዳጆች ይህን መንግስታዊ ወንጀል ለማስቆም ይበጃል ያሉትን ሙከራ አድርገዋል፡፡ ለአምስት ተከታታይ ቀናት በበይነ-መረብና በተቋማት ቢሮዎች ላይ የተደረገው አስጨናቂ ህግን የማስከበር ውትወታ የመጀመሪያውን ውጤት አይቷል፡፡ ተመስገንንም በአካል ለማየት ተችሏል፡፡
የሰብአዊ መብት ኮሚሽን መርማሪዎችና በርከት ያሉ አጃቢ ወታደሮች ባሉበት፣ ከወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ ጋር ዛሬ የተገናኘው ጋዜጠኛ ተመስገን ጤንነቱ አደጋ ላይ እንዳለ መረዳት ተችሏል፡፡ ከዚህ ቀደም የነበረው የጀርባ ህመም አላስተኛ ወዳለው እብጠት መቀየሩንና የግራ ጆሮውም መስማት ወደማይችልበት ደረጃ መድረሱ ታውቋል፡፡ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኝ ለዝዋይ ማረሚያ ቤት ያቀረበው ጥያቄም እስካሁን ምላሽ እንዳላገኘ በቦታው ለነበረው ወንድሙ ገልጾለታል፡፡ አያይዞም ያለቀናት በቆየው ያላቋረጠ ዘመቻ ልባዊ ወዳጅነትን፣ ስስትንና ወንድማዊነትን ላሳያችሁ ወገኖች ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ምስጋና አቅርቧል፡፡
መጎብኘት እንደተፈቀደላቸው ከኮሚሽኑ መርማሪዎች በስልክ ማረጋገጫ ያገኙት ወንድሙና አንድ ወዳጁ ቢሆንም ሁለቱም ለመግባት የሚያስፈልገውን ምዝገባ ካሟሉ በኋላ የተመስገን ወዳጅ ተከልክሎ ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ እንዲገባ መደረጉ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen