Netsanet: በፒያሳው ቦንብ ፍንዳታ ዋና አቀናባሪው ተስፋዬ ገ/አብ መሆኑን ያውቃሉ? (ሊያነቡት የሚገባ) (በአለማየሁ መሰለ )

Montag, 24. November 2014

በፒያሳው ቦንብ ፍንዳታ ዋና አቀናባሪው ተስፋዬ ገ/አብ መሆኑን ያውቃሉ? (ሊያነቡት የሚገባ) (በአለማየሁ መሰለ )

Image
ለዛሬ የማቀርበው መረጃ ተስፋዬ ገብረአብ እንደ ሸፋን ከሚጠቀምበት የደራሲነት እናየጋዜጠኘነት ስራ ባሻገር ለማመን በሚያዳግት ይሰራ የነበረውን የወንጀል ድርጊት ፍንትው አድርጎ ያሳያል።ከዚህ በታች አባሪ ተደርጎ የተያያዘው በእጅ የተጻፈ መረጃ፣በእጄ ላይ ካሉ መረጃዎች መሃከልትኩረቴን የሳበው ነው።እንደምትመለከቱት በራሱ በተስፋዬ ገብረአብእጅየተጻፈነው።ከሌሎችመረጃዎች ለየት የሚያደርገው ደግሞ፣እንደሌሎች መረጃዎች በፎቶኮፒ እጄ ላይ የቀረሳይሆን፣ዋናው(ኦርጅናል)መሆኑ ነው። ምክንያቱም በቀጥታ ወንጀል የተጻፈበት ሆኖ ስለታየኝ ነው።ከእጅጽሁፉ ላይ እንደምትመለከቱት፣መኩሪያ መካሻ ከተባለ ግለሰብ ጋር ድብቅ(ህቡእ) ስራ ለመስራትጀምረው ነበር።እንደኔ ግምት የኤርትራ መንግስትን ጥቅም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያስፈጽማልብለው ያሰቡትን ተልእኮ ለመፈጸም አሲረው ነበር፡፡እንደ መረጃው ከሆነ መኩሪያ መካሻ የተባለውግለሰብ ከፒያሳው ቦንብ ፍንዳታ በኋላ ፈርቶ ይሁን ሌላ ባይታወቅም፣ከተስፋዬ ጋር ያለውን
ግንኙነት አቋርጧል።የፒያሳው የቦንብ ፋንዳታ ብሎ የተገለጸው ደግሞ ሌላ ሳይሆን በ2002 እኤአበትግራይ ሆቴል ላይ የደረሰው ፍንዳታ ነው።የእጅ ጽሁፉን ሙሉ ይዘትና ለአንባቢ ይመች ዘንድ የተየብኩትን ይመሳከር ዘንድ እንደሚከተለው
አቅርቤዋለሁ።አሰሪ መሆንና በቀጥታ ከእሳቱ ጋር መጋፈጥ ልዩነት አላቸው መኩሪያ መካሻ የተባለው ሰው ጥሩ ጀምሮነበረ።ፒያሳ ላይ ቦምብ ሲፈነዳ ከእኔ ጋራ ያለንን ግንኙነት አቁዋረጠ።በጣም ጉዋደኛየ ነበር ለስራውስል ሰዋሁት። ጉዋደኛንመሰዋቴ ትልቅ ነገር አይደለም።ህይወታቸውን የሰዉ፣ክቡር ዜጎች ያሉበት ሃገርሰው ነኘና። እዚህ ላይ በትክክል ማሰብ እችላለሁ።አስቃቂውን ስሜቴን ግን ለመግለጽ ያህል ነው።ያሸማቅቁሃል ሲሳካልኝ በደስታ መጠጣት፣ሲከሽፍብኝ በንዴት መጠጣት፣ልምድ አደረግኩት።ደረጀደስታ እራሱ ከገፋፋኝ በሁዋላ መልሶ በኢትኦጵያ የማምን ኢትዬጵያዊ ነኝ ሲለኝ ምን እንደሚሰማገምቱት።
ሚኒስትር የነበረው ደስታ ወልደማርያም ጋር ለዘላለሙ ተለያይቻለሁ።እነዚህ ሰዎች ለወያኔ ነግረው ምንያስፈጽሙብኝ ይሆን የሚል ስጋት አለብኝ።ያድዋን ወረዳ ያበላሸው ………… የደረሰበትን ታሪክእያሰብኩ መሰቃየቴን አልተውኩም።ከብብቱፈልቅቄ ካስቀረዋቸው መረጃዎች ከዚህ በታች እንደምታዩት በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ላይየኢትዬኤርትራ ጦርነት በሁዋላ እሱም እንዳለቆቹ እንዳቄመ ነው የምናየው።እስከጦርነቱ መጀመሪያ ድረስግን፣የህወሃት አባልነቱን ግዴታ ለመወጣት በአለቆቹ ታዞ ይሁን በራሱ ተነሳሽነት የአማራንና የኦሮሞንህዝብ ለማጋጨት ነበር ስራዬ ብሎ የተያያዘው።አሁን ደግሞ በኤርትራ የመረጃና ደህንነት መስሪያቤትፕሮጀክት ተቀርጾለት የትግራይ ህዝብንም የትኩረታቸው መነሻና መድረሻ አካተው በተቀረው የኢትዬጵያህዝብ ለማስጠላትና ለማሸማቀቅ፣የተስፋዬ ገብረአብን ብእር እንደዋነኛ መሳሪያ እየተጠሙበት እንደሆነበግልጽ ማየት ይቻላል።ከላይ እንደገለጽኩት መስሪያ ቤቱ በሃገራችን ህዝቦች መሃል ያለውን መተማመን እና አንድነት ለማትፋትፕሮጀክት ተቀርጽለት ከፍተኛ በጀት ተመድቦለት በዚህ ግለሰብ ኣማካኝነት እየተፈፀመ የከረመው እና
ሊፈፀም እየቴሰረ ያለው ሤራ እንደሚከተለው ይሆናል፥፥አጠቃላይ የግቡ አላማ የኢትዮጵያን አንድነት ማዳከም ነው፥፥ ስልታዊ አካሄዳቸው ድግሞ አንዱንብሄረሰብ ከሌላኛው ጋር እርስ በእርስ እንዳይማመኑ በማድረግ በመሃላችን አንድ ሃገራዊ አጀንዳና እሴትእንዳይኖረን ማድረግ ነው፥፥
ለዚህ ማጠናከሪያ የሚሆነው፣የአማራ፣የኦሮሞ እና የትግራይ ብሄረሰቦችን ለምሳሌ ያህል ብንወስድአንድ የኦሮሞ የዘር ሃረግ ያለው ግለሰብ፣አማራ ከሆነ ግለሰብ ጋር አብረው በጓደኝነት፣በጋብቻሊኖሩ የሚችሉበት የግኑኝነታችው መሰረት አንድና አንድ ብቻ እንዲሆን ነው የሚፈለገው፡፡ ያምየትግሬ ጥላቻ ነው።በተቀረው ሁለቱ ግለሰቦች የጋራ የሆነ ሃገራዊ አጀንዳ እና እሴት ቀርጸውስለዲሞክራሲ፣ፍትህ፣ልማትና የሰብአዊ መብት መከበር እንዲሁም ሌሎች ሃገራዊ አጀንዳዎች
እንዲያግባቧቸው ፈጽሞ አይፈለግም።የወዳጅነታቸው መሰረት አንድ ብቻ እንዲሆን ነውየሚፈለገው፣እርሱም የትግሬ ጥላቻ ብቻ ነው። በሌላኛውም መአዘን የትግራይና ኦሮሞ ብሄርተወላጆች የወዳጅነታቸውና ያብሮነታቸው መሰረት መሆን ያለበት፣የአማራ ጥላቻ ብቻ እንዲሆንነው እቅድ ወጥቶለት ከፍተኛ ገንዘብ ተመድቦለት በተግባር ላይ እንዲውል እየተደረገ ያለው።ይህንን ለምሳሌ አነሳን እንጂ ሁሉም የሃገራችን ብሄሮች በተገኘው አጋጣሚና እድል በዚህ መልክበጎሪጥ እንዲተያዩ በማድረግ እንደሰው ወይንም እንደ ኢትዬጵያዊ ማሰብ አቁመን ሳንፈልግበመረጥነው የብሄር ማንነታችን ላይ አትኩረን ስንኩላን እንድንሆን የተሸረበ ሴራ አካል ነው።እዚህጋ በኤርትራ የደህንነትና መረጃ መስሪያቤት ሙሉ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ በመታገዝ
የተስፋዬ ስነ-ጽሁፍ የበኩሉን የማናከስ ሚና በመጫወት ሃገራችንን ወደማያባራ ጦርነትና እልቂትለመክተት የራሱን ሚና እየተጫወተ ይገኛል።ሁለት አመት ለሚቆጠር ጊዜ ቤቴ አስጠግቸው ሲኖር ከሚያደርጋቸው የስልክ ልውውጦች
እንደተረዳሁት ከሆነ በተስፋየ ገብረአብ ስም ይወጡ የነበሩ ጽሁፎች በአብዛኛው ማለት ይቻላልከኤርትራ የመረጃና ደህንነት መስሪያቤት የፕሮፓጋንዳ መልእክቶች እንደነበሩ ህያው ምስክር ነኝ።ይህ ማለት ተስፋየ በጋዜጠኝነት ወይንም በደራሲነት ሽፋን የመረጃ መስሪያቤቱ የፕሮፓጋንዳማስተላለፊያ መሳሪያ በመሆን ለኤርትራን ብሄራዊ ጥቅም የሚውል ስራ ይሰራ የነበረ መሆኑን
አስረጂ ነው።ለምሳሌ ከደህንነት መስሪያቤት የላኩለትን ምንም ለውጥ እንዲደረግበት ሃሳብሲያቀርብ፣እነሱም ሃሳቡን ሳይቀበሉት ሲቀሩ በር ዘግቶ በስልክ ሲጨቃጨቅና ሃሳቡ ሲሸነፍበተደጋጋሚ መስማቴን አስታውሳለሁ።እንደ እኔ እምነት ከሆነ ራሱ የኢትዬጵያ መንግስት እያራመደ ያለው የተንሸዋረረና የከረረ የዘርማንነትን ብቻ ማእከል ያደረግ የፖለቲካ ስርአት፣ከውጪ ሊመጣ ለሚችል እንዲህ አይነትየማጋጫት ወይንም ሃገር የማፍረስ ጣልቃገብነት በር እንደሚከፍት ለመተንበይ አዳጋች አይሆንም።ወደ ነጥቤ ልመለስና ከላይ በጠቀስኩት መሰረት፣አማራን ከተለያዩ የሃገሪቱ ብሄሮች ጋር እንዴትሲያላትምእንደነበረ፣ ዳኛ ወልደሚካኤል መሸሻ ጋር በክፍል አንድ ሪፖርታችን ላይ በሰፊውሄደንበታልና አሁን አልመለስበትም። ከዚህ በታች ደግሞ የትግራይ ብሄር አባል በሆኑ ግለሰቦች ላይማህበራዊ ፤ የስነልቦና የአካል ጥቃት መፈጸሙ፤ የሱ መጽሃፍ ስኬት ውጤት እንደሆነ ለኤርትራየመረጃና ደህንነት መስሪያቤት የቅርብ ተጠሪው ለሆኑት አቶ ዓለም እንዲህ በማለት በጽሁፍየፋክስ መልእክት ረቂቅ (ድራፍት ) ያስተላልፍ እንደነበረ መረዳት እንችላለን፡

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen