Netsanet: የእነ አቶ በቀለ ገርባ መከላከያ የመስማት ሂደት አቃቤ ህጉ እርቦኛል በማለቱ ምክንያት ተቋርጧል። በ ( ጌታቸው ሽፈራው)

Freitag, 18. August 2017

የእነ አቶ በቀለ ገርባ መከላከያ የመስማት ሂደት አቃቤ ህጉ እርቦኛል በማለቱ ምክንያት ተቋርጧል። በ ( ጌታቸው ሽፈራው)

የእነ አቶ በቀለ ገርባ መከላከያ የመስማት ሂደት አቃቤ ህጉ እርቦኛል በማለቱ ምክንያት ተቋርጧል።

አቃቤ ህግ ለሚያቀርበው ጥያቄ ተደጋጋሚ መቃወሚያ የቀረበበት ሲሆን መሃል ላይ "አርብ እንደመሆኑ እኛ ለምሳ  መውጣት ያለብን 5:30 ላይ ነው። የምሳ ሰዓታችን ይከበር" ብሎ ባቀረበው ጥያቄ  መሰረት መጠነኛ ክርክር ተደርጓል። ሌላ አቃቤ ህግ ስለነበር ፍርድ ቤቱ ሌላኛው አቃቤ ህግ ራበኝ ያለውን ተክቶ የሚሰራበት አጋጣሚ ስለመኖሩ ቢጠይቅም ራበኝ ያለው አቶ  አንተነህ  የተሰየመው እሱ ብቻ መሆኑን ገልፆአል።

 " እኔም ከጤናዬ አንፃር ሊታሰብልኝ ይገባል።ጨጓራ አለብኝ። መብላት አለብኝ" ብሏል አቶ አንተነህ።

የቀኝ ዳኛው አቃቤ ህጉ ያነሱት ጥያቄ መስቀለኛ ጥያቄ ሳይጀመር ቢሆን ኖሮ ተገቢ ይሆን እንደነበር  ገልፀው መታገስ እንደሚገባ በመጠቆማቸው  አቃቤ ህጉ " ትክክል ነው። ታግሼ መስራት እንዳለብኝ አውቃለሁ። እዚህ ቦታ ላይ ቆሜ የምሰራው ጤና ሲኖረኝ ነው። ህመሜን እያዳመጥኩ ልጠይቅ አልችልም።" ብሎ የምሳ ሰዓቴ ይከበር የሚለውን ጥያቄ ገፍቶበታል።

አቶ በቀለ ገርባ በበኩሉ "  ይህ ከዚህ ትልቅ  ተቋም የሚጠበቅ አይደለም።  እኛ እየተራብን፣ ብዙ መከራ እያየን ነው ያለነው። ህዝቡም የፍትህ ሂደቱን እንዲያይ ነው። አቃቤ ህግ ከተለየ አካል ትዕዛዝ ሊቀበል ካልሆነ በስተቀር ይህ በምክንያትነት ሊቀርብ አይገባም" ብሏል።

 መሃል ዳኛው" ከዚህ ወንበር ተቀምጠን ትዕዛዝ መስጠት አለብን። ሁለት አቃቤ ህጎች ስላሉ አንዱ ተክቶ ሊሰራ እንደሚችል እንረዳለን። ይህ የትዕዛዝ ጉዳይ አይደለም።" ቢልም ሂደቱ ተቋርጦ ለምሳ ተወጥቷል።
 ይህ የምሳ ሰዓት ይከበር ጥያቄና ክርክር በታዳሚውና ተከሳሾች  ሳቅ የታጀበ ነበር።

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen