Netsanet: የለውጥ ሀይሉ እውነተኛ ከሆኑ ስራቸውን ይስሩ እኛም ስራችን እንስራ:: ማገዝ የሚለውን ቃል አልወደውም ::(በ ርዕዮት አለሙ)

Samstag, 20. Oktober 2018

የለውጥ ሀይሉ እውነተኛ ከሆኑ ስራቸውን ይስሩ እኛም ስራችን እንስራ:: ማገዝ የሚለውን ቃል አልወደውም ::(በ ርዕዮት አለሙ)

በ ርዕዮት አለሙ

የለውጥ ሀይሉ እውነተኛ ከሆኑ ስራቸውን ይስሩ እኛም ስራችን እንስራ:: ማገዝ የሚለውን ቃል አልወደውም :: ምንድን ነው ማገዝ ማለት ለመሆኑ ? እኔ እኮ ኢትዮጵያ ሀግሬን ዲሞክራሲያዊ ለማድረግ ድሮ ያኔ ለትግል ስነሳ ዶር አብይ የሚባል ሰው ከነመፈጠሩም አላውቅም ::

  የ  ትግሌ አላማ እና ግብ ዶር አብይን ለማገዝ አይደለም አይሆንምም... አላማየ ኢትዮጵያ ሀግሬን ዲሞክራሲት የማድረግ ትልቅ ራዕይ ነው:: እኔ ይህ አላማየ እስኪሳካ ትግሌን እቀጥላለሁ:: በዚህ የ ትግል ጎዳና ላይ እያለሁ ዶር አብይ የሚባል ሰው ከ ኢህአዴግ ወጥቶ አይ እየሄድንበት ያለው መንገድ ልክ አይደለም ብሎ ኢትዮጵያን ለመቀየር ከተነሳ  እሽ ጥሩ ...ይህ ከሆነ ትክክለኛ ስሜቱ ደግ ነው::  እኔም ትግሌን እቀጥላለሁ መንገድ ላይ እንገናኛለን:: ነገር ግን እየሆነ ያለው ነገር ይህን አያሳይም::
 
    በ ግልፅ በ አደባባይ ሀገራችን ውስጥ እየተካሄደ ያለው ሀቅ ግን ተስፋ ሰጭ አይደለም ...እንደተባለለትም ወደ ዲሞክራሲ እየሄድን አይደለም...አንድ አንዶች ይህን ጥሬ ሀቅ እያዩ ዶር አብይን ከማገዝ ውጭ ምን ምርጫ አለ ለምትሉ መልሴ ምርጫ ካሳጡ በሗላ ምን ምርጫ አለ ይባላል እንዴ ? እየሆነው ያለው እኮ ምርጫ የማሳጣት ነገር ነው::

     ለምሳሌ አሁን የተፈጠረውን ችግር ከስሩ እንመልከተው:: የ አዲስ አበባ ወጥቶች ለምን ለመደራጀት ተነሱ ብሎ መጠየቅ ደግ ነው?  ሆሮሞሳ ፊንፊኔ በሚል ስም የተደራጁ ወይም እንዲደራጅ ያደረጉ ሰወች እኮ በ አደባባይ የ ጥላቻ ንግግር ሲያደርጉ የነበሩ ናቸው ይህም ይታወቃል:: እነዚህ ሰወች ተሰብስበው ምን ነበር ሲያወሩት የነበረ ? የ ሚያቃቅር የሚያጣላ የምያጋጭ አይደለም ን? እነዚህ ሰወች ተደራጅተው የፍለጉትን እንዲናገሩ እየተደረገ ነው :: እንዲህም እንዲያደርጉ ተፈቅዶላቸዋል::

    በሌላ በኩል ይህን አደጋ የተገነዘቡ የ አዲስ አበባ ወጣቶች የ አዲስ አበባን ወጣት ለማደራጀት ሲሞክሩ አንጠልጥለው እስር ቤት ወረወሯቸው::  እነዚህ ወጥቶች ሄኖክ እና ማይክ ወንጀላቸው ምንድን ነው ?  ወንጀላቸው መደራጀት ነው ተባለ ...

   ይህ ግልፅ መድሎ ነው ! ለ አንዱ መፍቀድ ሌላውን መከልከል ብቻ እንኳ አይደለም  ልትደራጅ ነው ብሎ ማሰር !  እዚህ ውስጥ  የ ዶር አብይ እጅ የለበትም ብሎ ነገር አይጥመኝም... ጥሩ ጥሩውን ለ ዶር አብይ  እንዲህ አይነት ግፍ እና በደሉን ለ ለውጥ ቀልባሾች መስጠት ትክክል አይደለም::

  ሲጀመር የለውጥ ሀይሉ የ ለማ ቲም የሚባለው ቁጥራቸው ስንት ነው እነማን ናቸው የሚባለው ነገር ግልፅ አይደለም::

   ሌላው የሚገርመው ነገር  የ ቤተመንግስቱ የ ወታደሮች ሁኔታ ነው:: በ እለቱ ዶር አብይ ወጥተው ከ ደሞዝ ጋ የተያያዘ ነው አሉን ከዛም ከዚህ በተቃራኒ መረጃ አለን ያሉትን ሰወች ውሸታማሞች አስባሉ::

   አሁን ወጥተው አይ ያን ጊዜ የነገርኳችሁ እውነት አይደለም ሌሎች ያሉት የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ትክክል ነበረ አሉን ::  እንግዲህ ከሁለቱ የቱን እንመን ሲባል ያንም ይህንም እመኑኝ የሚሉት ነገር ነው::  እኔ ያ ነው ይህ ነው የሚል ክርክር ውስጥ አልገባም ነገር ግን ሁለቱንም እመኑኝ የሚሉት ነገር ትክክል አይደለም:: ስለ ሰበታ ለጋጠፎ እና ቡራዮ የተናገሩት ነገር የሚገርም ነው ! እውነት እየመጡ ነበር የሚለው ነገር እንዳለ ሁኖ  ለማስተላለፍ የፈለጉት ነገር ምንድን ነው ብሎ መጠየቅ ግድ ይላል :: እኔ የሚታየኝ ድራማ ነው ለምን እንዲህ አይነት ድራማ ለመስራት ተፈለገ::

  ማሳስቢያ::
ይህን ፅሁፍ የ ፃፍኩት ርዕዮት አለሙ በ ኢሳት እለታዊ ያደርገችውን ውይይት ተመርክዤ ቢሆንም ንግግሩን ወደ ፅሁፍ ሲገለብጥ ትንሽ  ማጣፈጫ ተጠቅሚያለሁ::
CC Eskedar Alemu Gobebo

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen