Netsanet: ቀላል የስነልቦና ጦርነት ስልቶች:  ማግለል፣ ማድነቅ እና ማብራራት ( ዶ /ር ታደሰ ብሩ) 

Dienstag, 2. Mai 2017

ቀላል የስነልቦና ጦርነት ስልቶች:  ማግለል፣ ማድነቅ እና ማብራራት ( ዶ /ር ታደሰ ብሩ) 

ቀላል የስነልቦና ጦርነት ስልቶች:  ማግለል፣ ማድነቅ እና ማብራራት

ማግለል – የህወሓት፣ የብአዴን፣ የኦህዴድና የደኢህዴን እንዲሁ የአጋር ድርጅቶች ቀንደኛ አባላትን፤ ግፈኛ የፌደራል ፓሊስ አባላትን፣ በየመንደሩ እያነፈነፉ ያሉት ጆሮ ጠቢዎችን፣ ጭንቅላት የለሽ ፓሊሶችን፣ ፍርደ ገምድል ዳኞችን፣ ሀሰተኛ አቃቢያነ ህግ፣ ካድሬ መምህራንን፣ የመንደር ለፍላፊ ውሸታም ካድሬዎችን፣ አድርባይ “አርቲስቶችን”፣ “ልማታዊ ጋዜጠኞችን” ማግለል፣ መጠየፍ፣ ማራቅ፣ መናቅ፣ ማዋረድ፤ በእነሱ ላይ ማፌዝ፤ ድንቁርናቸውን፣ ሆዳምነታቸውንና አድርባይነታቸውን  የሚገልፁ የቅሌት ስሞችን ማውጣት እና ማሰራጨት። 
ማድነቅን – ለነፃነት ሲሉ ዋጋ የከፈሉ እና እየከፈሉ ያሉ ዜጎችን ማድነቅ፤ አርዓያነታቸውን ማጉላት፤ ማበረታታት፤ ሁለተናዊ ድጋፍ መስጠት። 
ማብራራት – የሥርዓቱ አገልጋዮች አድርባይነት ከዚያም አልፎ ወንጀለኝነት በማስረጃዎች አስደግፎ ይፋ ማድረግ።   ስለ ሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች፤ ሰለ ሀብት ዘረፋ፣ ስለ ሙስናን፣ ስለ መሬት ቅርምት፣ የባለስልጣኖች ሀብት ማሸሽን በሀሪቱ ከተንሰራፋው እና እያደገ ከመጣው ድህነት ጋር እያነፃፀሩ ማቅረብ። አስከፊ ስለሆነው የእስረኞች አያያዝ በሀቅ ላይ የተመሠረቱ ጽሁፎችን በጋዜጦች፣ ሬድዮና ቴሌቪዥኖች መሰል መገናኛ ብዙሀን እንዲሰራጭ ማድረግ።

https://netsanetlegna.wordpress.com/2017/05/02/%e1%89%80%e1%88%8b%e1%88%8d-%e1%8b%a8%e1%88%b5%e1%8a%90%e1%88%8d%e1%89%a6%e1%8a%93-%e1%8c%a6%e1%88%ad%e1%8a%90%e1%89%b5-%e1%88%b5%e1%88%8d%e1%89%b6%e1%89%bd-%e1%88%9b%e1%8c%8d%e1%88%88%e1%88%8d/

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen