Netsanet: የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች መስከረም 23 ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

Dienstag, 23. September 2014

የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች መስከረም 23 ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

blue_party_ethiopia101370869814 (1)በሽብርተኝነት ተከሰው ማዕከላዊ የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ የጋሞጎፋ ዞን አመራሮች መስከረም 23/2007 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ 8፡00 አራዳ ችሎት እንደሚቀርቡ የሰማያዊ ፓርቲ የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ የጋሞጎፋ ዞን ምክትል ሊቀመንበር አቶ ፍቃዱ አበበ እንዲሁም የዞኑ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ኢንጅነር ጌታሁን አርባምንጭ ውስጥ ወር ከ15 ቀን ያህል ታስረው የነበር ሲሆን ወደ ማዕከላዊ ከተዛወሩ ሁለት ሳምንት እንደሆናቸው የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊው ገልጸዋል፡፡
ታሳሪዎቹ በቤተሰብ፣ በኃይማኖት አባትና በጠበቃ እንዳይጠየቁ የተከለከሉ ሲሆን የምክትል ሊቀመንበሩ አቶ በፈቃዱ ባለቤትና አባት እንዳይጠይቁ መከልከላቸውን ኃላፊው ጨምረው ገልጸዋል፡: (ነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ)

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen