Netsanet: “የይቅርታ ልብ ያስፈልገናል” – አዲሱን ዓመት በማስመልከት በስደት ከሚገኘው ሲኖዶስ የተላለፈ መልዕክት

Freitag, 12. September 2014

“የይቅርታ ልብ ያስፈልገናል” – አዲሱን ዓመት በማስመልከት በስደት ከሚገኘው ሲኖዶስ የተላለፈ መልዕክት

holy sinod excileበፓትሪያሪክ አቡነ መርቆርዮስ የሚመራው ቅዱስ ሲኖዶስ አዲሱን ዓመት በማስመልከት ባስተላለፈው መልዕክት አዲሱን ዘመን አዲስ መፍትሄ የምንፈልግበት ዘመን ልናደርገው ይገባል አለ። ቅዱስ ሲኖዶሱ ለዘ-ሐበሻ በላከው የአዲስ ዓመት መግለጫው “ብዙዎቻችን በልዩነቶቻችን ምክንያት በጥላቻ ስሜት ውስጥ ነን። ለዚህ የይቅርታ ልብ ያስፈልገናል። የቀድሞ አባቶቻችን በይቅር ለእግ ዚአብሔር ላይ የተመሰረተ ይቅርባይነት ብዙ ለውጥ ያመጡ ነበር። ‘በቀል የኔ ነው ያለውን አምላካዊ ቃል መሰረት አድርገው ጥላቻን ሳይውል ሳያድር ከመካከላቸው እያስወገዱ አንድነታቸውን ጠብቀው ኖረዋል” ብሏል።

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen