Netsanet: የዚህን ሰሞን የመቀሌን ባለስልጣናት ያደፈረሰ ጉዳይ ተከስቷል። ሰላዮች እንደ አሸን ፈልተዋል።

Sonntag, 22. Juni 2014

የዚህን ሰሞን የመቀሌን ባለስልጣናት ያደፈረሰ ጉዳይ ተከስቷል። ሰላዮች እንደ አሸን ፈልተዋል።


‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Tigray‬ ‪#‎TPLF‬ ‪#‎EPRDF‬ ‪#‎Mekelle‬ ‪#‎AddisAbeba‬
የህወሓቶች የውስጥ ቅራኔ ዳግም እንዳያገረሽ ያሰጋል።ABBIN
አዲስ አበባ እና መቀሌ ላይ በተከታታይ እየተካሂዱ ያሉ ስብሰባዎች ውጥረቱ ያመለክታሉ። እያንዳንዱን እንቅስቃሴያችንን የሚከታተሉ እና የሚያጨልሙን ሰላዮች ተመድበውብናል ሲል መቀሌ ያለው የሕወሓት አንጃ አኩርፏል። ከመሃል አገር የፌዴራል መንግስቱን በመቆጣጠር እያሾረው ያለው የሕወሓት አመራሮች ቡድን መቀሌ በሚገነው አንጃ ላይ ሰላዮችን አሰማርቷል ሲሉ በትግራይ ክልል ያሉ የሕወሓት ባለስልጣናት እየከሰሱ ነው፡፤ ይህንን ተከትሎ የተነሳው ኩርፊያ እና አለመግባባት ሕወሓቶችን ዳግም ወደ ቀድሞው ሽኩቻ እና ቅራኔ ውስጥ እንዳይከታቸው ያሰጋል ሲሉ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ጠቁመዋል።
በግንቦት ሃያ በአል ምክንያት ወደ አውስትራሊያ ተጉዘው የነበሩት አለቃ ፀጋይ በርኸ እና ወይዘሮ ቅዱሳን ነጋ ብምካከላቸው በተነሳ አለምግባባት በተለያየ በረራ ወደ አገር ቤት መመለሳቸው የሚታወስ ሲሆን አለቃ ጸጋይ አብረውን በተጓዙ ጭፍሮቹ ያሰልለናል ሲሉ የቡድኑ አባላት ሲናገሩ ተደምጧል። አለቃ ጸጋይ ሰክረው የሰው ሚስት ሊያሽኮርምሙ ሲዳዳቸው በቡጢ መዘረራችው ይታወቃል።

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen