Netsanet: በአዲስ አበባ ዩኑቨርሲቲ የ3ኛ ዓመት የሲቪል ምህንድስና ተማሪና የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው ወጣት ዮናስ ከድር የዩኒቨርስቲ ፈተናውን እንዳይፈተን በፖሊስ ተከለከለ::

Dienstag, 29. April 2014

በአዲስ አበባ ዩኑቨርሲቲ የ3ኛ ዓመት የሲቪል ምህንድስና ተማሪና የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው ወጣት ዮናስ ከድር የዩኒቨርስቲ ፈተናውን እንዳይፈተን በፖሊስ ተከለከለ::

April 28/2014
በአዲስ አበባ ዩኑቨርሲቲ የ3ኛ ዓመት የሲቪል ምህንድስና ተማሪና የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው ወጣት ዮናስ ከድር የዩኒቨርስቲ ፈተናውን እንዳይፈተን በፖሊስ ተከለከለ::
ዮናስ ሰማያዊ ፓርቲ ለጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ከሌሎች የፓርቲው አባላት ጋር በቅስቀሳ ላይ እያለ ባሳለፍነው ሳምንት በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን የዩኒቨርስቲ ፈተና እንዳለበትና በፖሊስ ታጅቦ ሄዶ መፈተን ህጋዊ መብቱ መሆኑን ለፖሊስ ቢገልፅም እንዳይፈተን ተወስኖበታል::
በአንድ ወቅት ፕ/ር መስፍንን ሳዋራቸው ስለ ትምህርት እንዲህ ብለውኝ ነበር
"በመማሬ ካገኘሁት ጥቅም መካከል ዋነኛው የኢህአዴግ አባል ከመሆን መዳን ሲሆን ያጋጠመኝ ደግሞ እስር ነው"
ልክ ብለዋል ፕ/ር የምሁር ቤቱ በመሀይማን በሚመራው እስር ቤት ነው

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen