Netsanet: አዲስ አበባ፥ ጆን ኬሪ ሦስት የአፍሪቃ ሃገራትን ይጎበኛሉ

Sonntag, 27. April 2014

አዲስ አበባ፥ ጆን ኬሪ ሦስት የአፍሪቃ ሃገራትን ይጎበኛሉ

April 26/2014
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጆን ኬሪ ለአንድ ሳምንት ያህል ሦስት የአፍሪቃ ሃገራትን እንደሚጎበኙ ተገለጠ። የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር መግለጫ ዛሬ እንዳስታወቀው ኬሪ የሚጎበኙዋቸው ሦስት ሃገራት ኢትዮጵያ፣ አንጎላና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ናቸው። ኬሪ የፊታችን ማክሰኞ በሚጀምረው የአፍሪቃ ጉብኝታቸው ሠብዓዊ መብትንና ዲሞክራሲን ማጠናከር ዋነኛ የንግግር አጀንዳቸው እንደሚሆንም የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት አስታውቆዋል። ጆን ኬሪ ጠቅላይ ሚንስትር ሐይለማሪያም ደሳለኝንና የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ቴድሮስ አድሃኖምን አዲስ አበባ ውስጥ እንደሚያናግሩ መግለጫው አትቷል። ንግግሩም በአፍሪቃው ቀንድ ሠላም ለማስፈን ስለሚደረገው ጥረትና ከኢትዮጵያ ጋ ግንኙነቱን ስለማጠናከር እንደሚሆን መግለጫው አክሎ ጠቅሷል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የሠማያዊ ፓርቲ ሦስት ከፍተኛ አመራር አባላት እንዲሁም ስድስት የኢንተርኔት ጦማሪያንን ጨምሮ አንድ ጋዜጠኛ ትናንት አዲስ አበባ ውስጥ መታሰራቸው ተዘግቧል።

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen