Netsanet: በሱሉልታ ወረዳ ከወለጋ የመጡ የኦሕዴድ ካድሬዎች ከአማራ ተወላጆች ጋር ተጋጩ።

Donnerstag, 10. April 2014

በሱሉልታ ወረዳ ከወለጋ የመጡ የኦሕዴድ ካድሬዎች ከአማራ ተወላጆች ጋር ተጋጩ።

ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ የፌደራል ፖሊስ በአካባቢዉ ሰፍሮአል::
በትናትናዉ ዕለት ከምሽቱ 12 እስከ 3 ሰዓት በቆየዉ ግጭት 8 ሰዎች ተጎድተዉ ሆስፒታል ገብተዋል። የግጭቱ ምክንያት የአኖሌ ሃዉልት ምርቃት እና በቅርቡ በባህር ዳር በተደረገዉ የመሰላዉ ኢትዮጰያ ጨዋታ በተከሰተዉ የስፖርት ግጭት መበቀል ነዉ ሲሉ የመኢአድ የሱሉልታ ወረዳ ሰብሳቢ አቶ ያለዉ መላኩ ገልፀዋል።
ግጭቱን ያነሱት ከ40 በላይ የሆኑ ከወለጋ በመጡ የኦሕዲድ ካድሬዎች እንደሆኑ ሲታወቅ ከተጎዱት ሰዎች መሃከል ሴቶች ይገኙበታል ግጭቱ ከክልሉ ፖሊስ አቅም በላይ በመሆኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ የፌደራል ፖሊስ በአካባቢዉ ሰፍሮአል። ምንሊክ ሳልሳዊ

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen